Tuesday, April 30, 2013

  አገር አድን ዘመቻ


ጀግኖች አባቶቻችን የሀገራችንን አንድነትና ሉአላዊነት ለቀጣዩ ትውልድ ያስረከቡት በአንድነት ሆነው በመነሳት፣ውድ ሕይወታቸውን ገብረው ባደረጉት ክቡር መሰዋእትነት ነበር። በየአመቱ የምንዘክረው የአደዋ ሰማዕታት ቀን ከብዙዎቹ አንዱ የሆነ ታሪካዊ ምስክራቸው ነው፡፡ ይህ ትውልድ ደግሞ ሀገራችን ዛሬ በጎጠኛው ወያኔ ከወደቀችበትና ከደረሰባት አደጋ የማውጣት ታላቅ መስዋዕትነት ይጠበቅበታል፡፡
የታሪክ ባለአደራ ነንና ሀገራችን ሊበታትኗት ከተነሱት ከሃዲዎችና ጎጠኛ ኃይሎች ሴራ በድል ለመወጣት ቆርጦ በመነሳት ኢሕአፓ እነሆ የሀገራችን ሉአላዊነት እንዳይደፈር መድብለ ፓርቲ እውን እንዲሆን፣ ሕዝባዊ መንግሥት እንዲቋቋም፣ የእምነትና የሃሳብ ነጻነት እንዲከበር፣ ኢትዮጵያዊያን በሰደት እንዳይሰቃዩና ከሃገራቸው እንዳይፈናቀሉ፣ ሕዝቡ ማብቂያ ለሌለው ጦርነት ማገዶ እንዳይሆን፣ ገበሬው ለሚያርሰው መሬት ባለቤትነት መብቱ እንዲከበር በመታገልና በማታገል ላይ ይገኛል። ትግሉን ለማጠናከርና ውጤት እንዲያፈራ ለማድረግ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም በበለጠ በኢሕአፓ ጎን በመሰለፍ ሁለንተናዊ ትብብርና ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ሁለገቡን ትግል ለማፋፋምና አገር አጥፊውን ወያኔ ላንዴና ለመጨረሻ ለማስወገድ ገንዘብ አንዱ መሳሪያ ነው፡፡ ያለገንዘብ የሚገባደድ ትልምና እቅድ የለም። ኢሕአፓ ሁለገብ ትግሉን ለማፋፋምና ለማጠናከር ሀገር አድን ዘመቻ ግብረ ኃይል አቋቋሞ በዚህ ግብረ ኃይል አማካይነት የገንዘብ ድጋፍና እርዳታ በያካባቢው እያሰባሰበ ይገኛል። የሀገራችን ችግር መፍትሄ ፈላጊዎች እኛው ኢትዮጵያውያን ብቻ መሆናችንን ማመን ጥሪውን መቀበልና የተቻለንን ሁሉ በማድረግ አገራዊ ግዴታችንን መወጣት አማራጭ የሌለው ግዴታችን ነው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቱን ተገፎ፣ በመላ ሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና የኑሮ ዋስትና ጠፍቶ፣ የሥራ እድልና የማህበራዊ ኑሮው እያሽቆለቆለ በሄደበት፣ ከድንቁርና፣ ከድህነት ያልተላቀቀው ወገናችን ስቃይ እየባሰ በሚታይበት፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎቶች ለጎጠኞች ብቻ በሆነበት፣ ፍትህና እኩልነት በጠፋበት ማንኛውም ሀገር ወዳድ ዜጋ ይህን ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል ትግሉን የድል ተስፋ ለማድረግ ደጋግሞ ኢሕአፓ ጥሪውን ያቀርባል።
ሕዝባችን ከዚህ ከጎጠኛ ወያኔ ቡድን ለመላቀቅ እየከፈለ ያለውን መሰዋዕትነት ከንቱ ሆኖ እንዳይቀርና የታሪክም ተጠያቂዎች እንዳንሆን በአንድነት በመነሳት ትግሉን በተቻለን መጠን እናጠናክረው። “ድር ቢያብር አንበሳን ያስር”
እንደሚባለው ሁላችን ተባብረን በአንድነት ከተነሳን ሀገራችን ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወያኔ ጎጠኛ ቡድን
እናላቅቃታለን

በመጨረሻም የሀገራችን ሉአላዊነት፣ የሕዝቧ የሥልጣን ምንጭነት በሕግ የሚረጋገጥበት፣ በእኩልነት ላይ የተመሰረተ
የሕዝብና የሀገር አንድነት የሚጠበቅበት፣ የእምነትና የሃሳብ ነፃነት የሚከበርበት፣ በሕዝቡ ነፃና ርቱአዊ ምርጫ የሚካሄድበት ለማድረግ የማንኛውም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሃላፊነትና ግዴታ እንዳለበት በማመን በሀገራችን ላይ አንጃቦ ያለውን አደጋ ለመቋቋም ሁላችንም በአንድነት በመነሳት የገንዘብ እርዳታ በማድረግ ትግሉን ለድል እንድናበቃው እነሆ ኢሕአፓ ጥሪውን ሳይሰለች ደጋግሞ ያቀርባል።

የምታደርጉትን የገንዘብ እርዳታ ከታች ከተጠቀሱት መንገዶች ውስጥ በሚያመቻችሁ መሆናችሁን በትህትና እንገልጻለን፡
1. በአካባቢያችሁ ላለ የኢሕአፓ አገር አድን ዘመቻ ግብረሃይል አባላት በቀጥታ በመስጠት
2. ለ EPRP ብሎ check/money order በEPRP P.O. Box 73337 Washington DC 20056 በመላክ
ለበለጠ መረጃ: –  202- 291-4217  ይደውሉ ወይም በ espic@aol.com ኢሜል አድራሻ ይጻፉ

ኢትዮጵያ በታጋይ ልጆችዋ ነፃ ትወጣለች
የኢሕአፓ አገር አድን ዘመቻ ግብረሃይል

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)
ETHIOPIAN PEOPLE’S REVOLUTIONARY PARTY (EPRP)

      Posted By.Dawit Demelash

ወያኔን ያሸማቀቀና መላው ዓለምን ያነጋገረው የኖርዎይ የተቃውሞ ሰልፍ በውሻ እና በሂልኮፕተርም ጭምር የታጀበ ነበር


Monday, April 29, 2013

ኢህአዴግ በኖርዌይ ገንዘብ ማሰባሰብ ተሳነው

oslo
በስደት አገራቸውን ለቀው የወጡ ሰዎች ያለመሰለል መብት አላቸው። በህግም የተደነገገ ነው። ከለላ የሰጣቸውም አገር ይህንን የመከላከልና የመቃወም ግዳጅም አለበት። ከለላ ያገኙ ስደተኞችም ሆኑ ከለላ እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ወገኖች ስለመሰለላቸው ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ ከቻሉ ህጉን ጠቅሰው የመከራከር መብት አለቸው። ለመብታቸው ሲከራከሩ በመደራጀት ቢሆን ይበልጥ ውጤታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ አውሮፓ በስደት ያሉ ቀድሞ የውጪ ጉዳይ የዲያስፖራ ኢንጌጅመንት ዳይሬክቶሬት ዲፓርትመንት ኤክስፐርት ይናገራሉ።
እኚሁ ሰው እንደሚሉት ከ1997 ዓ ም ምርጫ በኋላ በአቶ መለስ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተቋቋመው ይህ ዲፓርትመንት ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለወቅቱ የውጪጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍን ሪፖርት ያቀርብ ነበር። በጁላይ 2003 ስድስት አባላትን በመያዝ የተቋቋመው ዲፓርትመንት “ብዙሃን አድፋጭ” ዲያስፖራ ወይም “silent majority” የሚባሉትን ለመማረክና በስደት ውጪ አገር የሚኖሩትን የተቃዋሚ ድርጅት ዋና ደጋፊዎችንና አመራሮችን የሚከታተል ቻፕተሮች አሉት።
የአገዛዙ ደጋፊ ለሚባሉት ዲያስፖራዎች የቀረጥ ነጻ መብት በመስጠት፣ መሬት በማደል፣ በማህበራት በማደራጀት ቢቻል መታወቂያ በመስጠት፣ “ለአገር ግንባታ ደጋፊ ማድረግ” በሚል ሽፋን በያሉበት አገር ከኤምባሲ ጋር ግንኙነት እንዲፈጥሩ በማድረግ የተዘረጋው መዋቅር የአውሮፓውን የክትትል ስራ በግንባር ቀደምትነት እንዲመራ የመደበው የብራስልስ ኤምባሲን ነው። በቤልጂየም ኢትዮጵያ ኤምባሲ ካውንስለር በመሆን የሚያገለግሉት የቀድሞው የህወሃት ታጋይ ይህንኑ የአውሮፓ የክትትል ቻፕተር እንደሚመሩት የሚያስረዱት የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰራተኛ የቻፕተሩን ጠርናፊ “አቶ መለስ በታመሙበት ወቅት ብራስልስ ሆነው አስፈላጊውን ሁሉ ሲያደርጉ የነበሩ የስርዓቱ ታማኝ ሰው ናቸው” ሲሉ ይገልጹዋቸዋል።
በጥቅማ ጥቅም ዲያስፖራ ውስጥ ሆነው የክትትል ስራ በመስራት በያሉበት አገር ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር ግንኙነት በመፍጠር ስርዓቱን የሚያገለግሉ ስለመኖራቸው በውል የሚናገሩት እኚሁ ሰው “ስርዓቱን ሸሽተው ጥገኛነት የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ስለ አገዛዙ የሚሰጡት መረጃ ስለሚያንገበግባቸው ዲያስፖራው ውስጥ ያለውን እንቅስቃሴ ለማኮላሸት ከፍተኛ በጀት ይመደባል። በዚሁ በጀት እጅግ ቀረቤታ ላላቸው ደጋፊዎቻቸው በሚኖሩበት አገር ተራ የጉልበት ሰራተኛ የሚያገኘው ክፍያ ተሰልቶ ይከፈላቸዋል” በማለት አገሩን፣ ቤተሰቡን፣ ንብረቱን፣ ቤተዘመዱን ጥሎ የሸሸውን ዜጋ እየተከታተሉ ሪፖርት ስለሚያቀርቡት ክፍሎች ይናገራሉ።
ሰፊ ማብራሪያ ያቀረቡት እማኝ የኢህአዴግ ደጋፊዎች የልማትና ድጋፍ ማሰባሰቢያ መድረኮችን በማመቻቸት ታማንነታቸውን እንደሚያሳዩ የሚገልጹት የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ባልደረባ “ይህ አሰራር የተኮረጀው ከቻይና ነው። የተለያዩ አገር አሰራሮችና የደህንነት መዋቅሮች የተጠኑ ቢሆንም የ  ቻይናው የተመረጠው ለስራውና ኢህአዴግ ለሚፈልገው አደረጃጀት አመቺ ሆኖ በመገኘቱ ነው” ሲሉ የመዋቅሩን ተፈጥሮ ያስረዳሉ።
ከሳምንት በፊት በኖርዌይ ስታቫንገር፣ ዛሬ ኤፕሪል 28/2013 ደግሞ በኦስሎ ስለተካሄደው የቁጣ ተቃውሞ አስተያየት የሰጡት እኚሁ ሰው “ኢህአዴግ ሊገለኝ ነው በማለት ሸሽተው ጥገኝነት የጠየቁ ወገኖች ከመንግስት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም። ሊኖራቸውም አይችልም ማስረጃ በማሰባሰብ ጉዳዩን ወደ ህግ ማቅረብ ይቻላል” ባይ ናቸው።
“ተሰደን አገር ለቀን ወጣን። አገራችን እንዳንኖር ተደረግን። በስደት በምንኖርበት አገር ድረስ መጥተው ገንዘብ ሊጠይቁን ማሰባቸው ይገርማል። እንደዚህ ገንዘብ የተጠሙበት ምክንያት ምን ይሁን? ኢህአዴግ አገሬ እንዳልኖር አደረገኝ፣ ህይወቴ አደጋ ላይ ነው በሚል ከለላ የጠየቀ ሰው እንዴት መንግስት ደጅ ይቀርባል። ይህ እኮ ህገወጥ ነው። ወንጀል ነው። ከለላ የሰጠው አገርም ሆነ ዋናው የስደተኞች ህግ አይደግፈውም” በሚል አንድ ጥግ ይዘው የሚነጋገሩና የሚወያዩም አጋጥመውኛል።
መከላከያው አክራሪንና አልሸባብን ይደመስሳል በሚል የማይነጥፍ ገበያ አላቸው። መሬት ይሸጣሉ። ንግዱን ተቆጣጥረውታል። ኢንቨስትመንቱን በጃቸው አድርገውታል። አስመጪና ላኪነቱን የግላቸው አድርገውታል። ባዕድ ሃይል የማያደርገውን የከፋ ተግባር እንመራዋለን በሚሉት ህዝብ ላይ ይፈጽማሉ። አገሪቱን በዘርና በጎሰኝነት አስተሳሰብ መርዝ በክለው እርስ በርስ እያጫረሱ ምድሪቱን የበቀል ቡቃያ አድርገዋታል። ታዲያ እነዚህ ሰዎች በየትኛው ሞራላቸው ነው ስደት የሚለበልባቸውን ዜጎች ሰብስበው ገንዘብ የሚጠይቁት? የሁሉም ጥያቄ ነው።
በተጠቀሰው ቀን ለአባይ ግድብ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ለማካሄድ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አጭር የስልክ መልዕክት (የኤስ ኤም ኤስ) ጥሪና በተለያዩ አደረጃጀቶች ጥሪ ተበትኖ ነበር። ኦስሎ የሚኖሩ የስርዓቱ ሰለባዎች ራሳቸውን አደራጅተውና ግብረኃይል አቋቁመው በስብሰባው ለመገኘት ዝግጅታቸውን አስቀድመው እንዳከናወኑ በስፍራው የነበሩ ለጎልጉል ዘጋቢ አመልክተዋል።
እንደተባለው ጠዋት ረፈድ ፈድ ሲል በስቶኮልም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰው ስብሰባውን ለመምራት ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ያዘጋጁት መድረክ ላይ ለመቀመጥ Radisson Blue Scandinavia Hotel ሲደርሱ የጠበቃቸው ሌላ ነበር። በስብሰባው ለመገኘት የሚያስችል “የዜግነት” መብት ያላቸው ወገኖች ስብሰባውን ለመካፈል ጠየቁ። “አትገቡም” ሲባሉ ተቃውሟቸውን ከቁጣ ጋር አሰሙ። ባለስልጣኑ ማሽላ እያረረ ይስቃል እንደሚባለው ፈገግታ በማሳየት በምሬት በሚወርደው የተቃውሞ ቃል መገረፋቸውን ለመደበቅ ሞከሩ። ንዴታቸውን ለመደበቅ ሲታገሉ ጭራሹኑ ስብሰባውን ማድረግ በማይችሉበት ደረጃ ተቃውሞው ስለጨመረ ለአባይ ግድብ ብር ለማሰባሰብ የተወጠነው የኦስሎው ውጥን ስታቫንገር እንደሆነው ተኮላሸ። ፖሊስ ስብሰባው ሊካሄድ እንደማይችል አረጋገጠ።
በኖርዌይ ከሚታተሙትና ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ዜና ካሰራጩት መካከል፣ ቬጌ የሚባለው ጋዜጣ አስራ አንድ ሰዎች ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል በሚል መታሰራቸውን አስነበበ። በስፍራው ቁጣቸውን የገለጹ ወገኖች ሳያስፈቅዱ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል በሚል ጋዜጣው የእስሩን ምክንያት ፖሊስን ጠቅሶ አስፍሯል። በስፍራው የተገኙም ሆኑ የዚህ ሪፖርት አቅራቢ እንደታዘበው ዜጎች አስቀድመው የጠየቁት በስብሰባው ላይ እንሳተፍ የሚል የዜግነት ጥያቄ ነበር። በጥያቄያቸው መሰረት ወደ ስብሰባው ቦታ ለመግባት ሳይችሉ መከልከላቸው እንደ ዜጋ የሞራልና የማንነት ጥያቄ በመሆኑ ቁጣቸው ከስርዐቱ ተፈጥሮ ጋር ተዳምሮ የነደደ ነበር።
ከፍተኛ ቁጥር የነበረው የፖሊስ ሃይል አስራ ሁለት ተሽከርካሪዎችን አሰልፎ የቁጣውን ሰልፍ “ለመቆጣጠር” እንደቻለ፣ የሰለጠኑ ውሾችና ከሆቴሉ በቅርብ ርቀት ሄሊኮፕተርም ተዘጋጅቶ እንደነበር ቬጌ አስነብቧል። የጎልጉል ሪፖርተር ባሰባሰበው መረጃ አባይ ቢገደብ የሚጠሉ ወገኖች የሉም። ቅድሚያ ሊከናወኑ የሚገባቸው ጉዳዮች እንዳሉ ግን ይስማማሉ። ቅድሚያ አፈናውና ያለ ህዝብ ውክልና በጠመንጃ ከህዝብ ጫንቃ ላይ መንሰራፋት ሊቆም ይገባዋል። የመብት ገደብም ሊቆም ግድ ነው። ይህ ሲሆን ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ገንዘብ የሌለው በጉልበቱ አድርግ የተባለውን ያደርጋል። አገርም በዜጎቿ ፍላጎትና እኩል ተሳትፎ ያለ ስጋት ትለማለች።
የታሰሩት ሰዎችን በተመለከተ ይህ ሪፖርት እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ ስለመፈታታቸው የተሰማ ነገር የለም። በሳምንት ጊዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ጠንካራ ሊባል የሚችል ተቃውሞ ያጋጠመው ኢህአዴግ፣ በኖርዌይ ተመሳሳይ ፕሮግራም ለማካሄድ ባይሞክር እንደሚሻለው ገለልተኛ ነን የሚሉ ወገኖች ተናግረዋል። አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ወቅት በኖርዌይ የገጠማቸው ተቃውሞ የከፋ እንደነበርና የመጡበትን ጉዳይ በወጉ ሳይጨርሱ መመለሳቸውን ያስታወሱት እነዚሁ ክፍሎች “አሜሪካ በዲቪ የተጓዙ ደጋፊዎች ሊኖሩ ይችላሉ። አውሮፓ ግን በትምህርት መጥተው የቀሩ ካልሆኑ በስተቀር ኢህአዴግ በግልጽ ሊደግፉት የሚችሉትን አባላት ለመግኘት አይቻለውምና አባይን እንደጀመረው ከቻይና ተበድሮ ቢያጠናቅቀው ይመረጣል” ብለዋል። ኢህአዴግ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች፣ በሳዑዲ አረቢያ፣ በዱባይ፣ በደቡብ አፍሪካ ተመሳሳይ ተቃውሞ እንደገጠመው በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ የሚታወስ ነው። (ፎቶ: VG)

          Posted By.Dawit Demelash

Sunday, April 28, 2013

Adopted against her will: One woman shares her story

Tarikuwa Lemma Exposed the Selling of Ethiopian Kids


What would you do if you arrived in a foreign country ready to study on an educational exchange and only to discover you had been “adopted” by a family that thought you were an orphan?
It may sound like a nightmare, but it happened to Tarikuwa Lemma, who told her story on Sunday’s Melissa Harris-Perry. Lemma came to the United States from Ethiopia for what she and her family thought was an educational exchange program when she was 13-years-old; after she arrived, she was told she had been adopted.
Once she learned what her adoption meant for her future, Lemma felt “a lot of grief and anger.”
“I didn’t want a new family because I had a family in Ethiopia,” said Lemma, who will start her freshman year at college in the fall. The family that tried to adopt Lemma and her two younger sisters changed their names and even stopped them from speaking their native language.
Adoption is a multi-billion dollar industry, rife with corruption and dissemblance, and in recent years it has morphed into an evangelical movement.
“There is so much emphasis on and enthusiasm for adoption in the United States,” said journalist Kathryn Joyce, author of “The Child Catchers.” “When adoption agencies prey on families’ desire to ‘help’ children they believe to be in need, there have been lies and misinformation seeded in from the very beginning” of the adoption process.
How can the adoption process be reformed? Is it even possible to do so? Watch the full discussion on MHPshow.com and watch the show every Saturday and Sunday at 10:00 AM ET

        Posted By.Dawit Demelash

ዛሬም የወያኔ ቦንድ ሽያጭ በኖርዌ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ከሸፈ


Saturday, April 27, 2013

የኤርትራ አየር መንገድ ወደ አውሮፓ እንዳይበር ታገደ

28 April 2013 ተጻፈ በ       



የኤርትራ አየር መንገድ ከበረራ ደኅንነት ሥጋት ጋር በተያያዘ ወደ ማንኛውም የአውሮፓ አገር እንዳይበር የአውሮፓ ኅብረት አገደ፡፡

የአውሮፓ ኅብረት በየዓመቱ ዓለም አቀፍ የበረራ ደኅንነት ሥርዓትን በአግባቡ አላሟሉም የሚላቸውን አየር መንገዶች ወደ አውሮፓ የአየር ክልል እንዳይበሩ የሚከላከል ሲሆን፣ የአየር መንገዶቹን ስም ዝርዝር ያሳውቃል፡፡ የስም ዝርዝሩም የአውሮፓ ኅብረት የበረራ ደኅንነት ጥቁር መዝገብ በመባል ይታወቃል፡፡

ኅብረቱ በቅርቡ ያወጣው የበረራ ደኅንነት ጥቁር መዝገብ የኤርትራ ብሔራዊ አየር መንገድ የሆነው የኤርትራ አየር መንገድ “ኤር ኦፕሬተር ሠርቲፊኬት” ቁጥር “AOC” No 004 የዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት መለያ ቁጥር “ERT” የተመዘገበውና ናስኤር ኤርትራ የተባለው አየር መንገድ “AOC” No 005 የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት መለያ ቁጥር “ኤንኤኤስ” ወደ ማንኛውም የአውሮፓ አገር እንይይበሩ መታገዳቸውን ይጠቁማል፡፡ መዝገቡ በኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ፈቃድ የተሰጠው ሌላ ማንኛውም አየር መንገድ ወደ አውሮፓ መብረር እንደማይችል ያሳያል፡፡

እ.ኤ.አ. በ1991 የተመሠረተው የኤርትራ አየር መንገድ በ2003 ዓ.ም. በተከራየው አንድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን ሥራ የጀመረ ሲሆን ወደ ሮም፣ ካይሮ፣ ጅዳ፣ ዱባይ፣ ፍራንክፈርት፣ ካራቺ፣ ኬፕታውንና ካርቱም ሲበር ቆይቷል፡፡ አየር መንገዱ ከአስመራ ወደ አሰብና ምፅዋ ይበራል፡፡

የኤርትራ አየር መንገድ አንድ ኤርባስ 319-200፣ ሁለት ኤርባስ 320-200 እና አንድ ቦይንግ 767-200E አውሮፕላኖች ተከራይቶ ይሠራል፡፡

በበረራ ደኅንነት ሥጋት ምክንያት የአውሮፓ ኅብረት በጥቁር መዝገቡ ውስጥ ካሰፈራቸው አየር መንገዶች 100 ያህሉ የአፍሪካ አየር መንገዶች ሲሆኑ፣ ከእነዚህም መካከል 42 ያህሉ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ የሚገኙ ናቸው፡፡ ከአንጎላ 13፣ ከጎረቤት አገር ሱዳን 12 አየር መንገዶች በአውሮፓ ኅብረት ጥቁር መዝገብ ውስጥ ሰፍረዋል፡፡ ከኢትዮጵያ በጥቁር መዝገቡ ውስጥ የገባ አንድም አየር መንገድ የለም፡፡

 Posted By,Dawit Demelash
50 Ethiopian immigrants sentenced to lengthy jail term with hard labor in Zambia
The Horn Times News 26 April 2013
Getahune Bekele-South Africa

Although the word “hard labour” sounds brutal and primitive, Zambian magistrate Shadreck Chanda was merciless in passing judgment when he sent 50 destitute Ethiopians to jail for entering the landlocked nation illegally on 29 March 2013.
Victims of human smugglers...Kembatta Ethiopians flocking south in search of better life…
Victims of human smugglers…Kembatta Ethiopians flocking south in search of better life…
The Ethiopians aged 11 to 37 were caught by Zambian police at Nakonde Border post, according to the Post online website, an online Zambian paper April 21st  edition.
The magistrate who failed to show compassion to the juveniles, ordered all 50 including the well known human smuggler Sisay Asefa to serve a one-and-half-year imprisonment with hard labour or to pay fine of KR 400.00.
“The government of Zambia would not allow or tolerate people entering the country without proper papers.” Chanda told the stranded Ethiopians, victims of a well organized TPLF sponsored human smuggling gang operating between Johannesburg and Addis Ababa.
“I would have only deported you to Ethiopia but that the offence committed is serious as it borders on national security.” The Zambian magistrate added warning the Ethiopians that if they repeat the same offence, the court would not be lenient towards them.
The original charge sheet alleges that the Ethiopians didn’t inform an immigration officer upon entry as required by Zambian law.
Meanwhile the Horn Times is working to expose a multimillion dollar smuggling ring operating from GP Street in central Johannesburg involving unscrupulous Kenbatta slave traders, immigration officials and TPLF diplomats.

        Posted By.Dawit Demelash

Tuesday, April 23, 2013


“ማፈናቀሉ የሚካሄደው በመንግሥት ትዕዛዝ ነው፤ ወደ ክስ እናመራለን”

“በቤኒሻንጉል የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ እርሻ አላቸው”
Justice Gavel


በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ2000 ሺህ በላይ ትግሬዎች ባለይዞታ መሆናቸውንና ማንም ሳይነካቸው በሰላም እንደሚኖሩ፣ በቶጎ ወረዳ ከስልሳ በላይ ነባር የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ የእርሻ መሬት ወስደው በባለሃብት ደረጃ እንደሚገኙ የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አስታወቁ። ከሌሎች ብሔረሰቦች ተለይቶ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ያለውን የአማራ ብሔረሰብ በድጋሚ ለማስወጣት መታቀዱንም በመረጃ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።
በቦታው በመገኘት አስፈላጊውን መረጃ እንደሰበሰቡ ለአሜሪካ ሬዲዮ የገለጹት የመኢአድ ስራ አስፈጻሚ በክልሉ ከሚኖሩት የተለያዩ ብሔረሰቦች ተለይቶ የአማራ ብሔረሰብ እንዲፈናቀልና እንዲሰቃይ የሚደረገው በማዕከላዊ መንግስት ትዕዛዝ እንደሆነም አመልክተዋል።
መኢአድ ያሰራጨውን መግለጫ ተከትሎ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ማብራሪያ የሰጡት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ ድርጊቱ በበታች የቀበሌና ወረዳ አመራር አካላት ተፈጽሟል መባሉን ተቃውመዋል።”ሰዎቹ እንዲወጡ ሲታዘዝ ያ ሁሉ ወታደር ከየት መጣ?” በማለት የጠየቁት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ በርካታ የወያኔ ሰዎች በቦታው እያሉ አማራው ተለይቶ እንዲፈናቀል የበታች ባለስልጣናት በራሳቸው ውሳኔ ይህን ሊያደርጉ እንደማይችሉ ተናግረዋል። በማያያዝም በርካታ ተጨባጭ ማስረጃ ስለተሰባሰበ ጉዳዩን ወደ ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ባላቸው የተለያየ መስመር ፍርድ ቤቱ የሚቀበላቸውን ማስረጃዎች በማጣራት አስፈላጊ መረጃዎችን እንዳሰባሰቡ የገለጹት ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል፣ “የሰውና የቪዲዮ መረጃ አለን። የመንግስት ወታደሮች ህዝብ ሲደበድቡ፣ መኪና ተገልብጦ ሰዎች ሜዳ ላይ ሲሰቃዩ፣ በግድ ሲፈናቀሉ … የሚያሳይ ተጨባጭ ማስረጃ አሰባስበናል። ወደ ክስ እናመራለን” በማለት መናገራቸውን የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ (ቪኦኤ) አመልክቷል።
የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል በበኩላቸው የመንግስት ባለስልጣኖችና ካድሬዎች በኩምሩክ ሕዝብ በመሰብሰብ ማነጋገራቸውን ይጠቅሳሉ። እሳቸው እንዳሉት ህዝቡ “ለምን በዘራችን ሳቢያ ይህ ሁሉ ስቃይ ይደርስንባል?” በማለት ጠይቆ ነበር። የሰበሰቧቸው ባለስልጣናት “ክልሉ የናንተ አይደለም ውጡ” ሲሉ  እንደመለሱላቸው የጠቀሱት የስራ አስፈጻሚ አባል፣ በሌላ በኩል የተፈጸመው ህገ ወጥ የዘር ማጥፋት ተግባር የመንግስት እጅ ያለበት እንዳይመስል ለክልሉ ነዋሪዎች “አማራን አታስጠጉ፣ ከአማራ ጋር አትብሉ፣ ከአማራ ጋር አትጠጡ፣ ቤት አታከራዩ፣ ይህን ማድረግ ወንጀል ነው” በማለት መንገራቸውንና በዚሁ መነሻ ህዝቡ በክልሉ ያሉ አማሮች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ጥያቄ እንዲያቀርቡ መመሪያ መሰጠቱን አመልክተዋል። ይህ የሚሆነውም ጥያቄው ከህዝብ የመጣ እንደሆነ ለማሳየት እንደሆነም አስታውቀዋል።
ahmed
የቤኒሻንጉል ፕሬዚዳንት አህመድ ናስር
በዘር፣ በሐይማኖትና በአመለካከት አንድን ማህበረሰብ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት መሞከር፣ ማሸማቀቅ፣ ሴቶችን መድፈር በዘር ማጥፋት እንደሚያስጠይቅ ያመለከቱት የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል፣ “ይህ ሁሉ ተፈጽሟል” በማለት ድርጅታቸው በዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት ከድምዳሜ መድረሱን ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ክልል ፕሬዚዳንት ለሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ስህተት መሰራቱን ማመናቸውና ድርጊቱን የፈጸሙት ኪራይ ሰብሳቢ የወረዳና የበታች አመራሮች እንደሆኑ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በተመሳሳይ ለስራ ፈረንሳይ አገር በነበሩበት ወቅት ለጀርመን ሬዲዮ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ፕሬዚዳንቱ ተፈጸመ ስላሉት ስህተት “የማውቀው ነገር የለም። አልሰማሁም። እኔ የማውቀው ደን ጨፍጭፈው በሃይል መሬት የያዙ መፈናቀላቸውን ነው” ብለዋል። ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም ቀደም ባሉት ሳምንታት ከቤኒሻንጉል የተፈናቀሉትን ዜጎች አስመልክተው በሰጡት አስተያየት ወንጀሉ የዘር ማጥፋት ስለሆነ ክስ መመስረት እንደሚቻል አመልክተው ነበር።
መኢአድ በበደኖ፣ በአርባ ጉጉ፣ አረካ ቀደም ሲል የተፈጸሙትን የዘር ማጥፋት ወንጀሎች አያይዞ ለክስ እንደሚጠቀምበት አመልክቷል። በጥያቄና መልሱ ወቅት ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል “የተፈናቀሉት ተመልሰዋል። ለምን አትተውትም” በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ጋዜጠኞች እንደነበሩ የቪኦኤው የአዲስ አበባ ዘጋቢ ጠቆም አድርጎ አልፏል።

             Posted By.Dawit Demelash

Sunday, April 21, 2013

በኖርዌይ የተደረገው የወያኔ ገቢ ማሰባሰቢያ አዳራሽ ተቃዋሚዎቹ ተቆጣጠሩት!! video
Ethiopians in Norway raised Ethiopian flag
በኖርዌይ የሚታተመው አፍተንብላደ( Aftenbladet)ጋዜጣ እንደዘገበው ለአባይ ግድብ በተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ የወያኔ ባንዲራ ተሰቅሎ የነበረ ሲሆን ተቃዋሚው  ባንዲራውን በመሸፈን ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ባንዲራ  ሲሰቅል የሚያሳይ ዘገባ ይዞ በፎቶ ወቷል። ወደ ኖርዌይ ትጉዛ ተዋርዳ የተባረረችው የወያኔ ዲፕሎማት ጀሌ በስዊዲን ወይዘሮ መብራት በየነ ሲደነግጡ ታይተዋል::
ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት ጭቅጭቅ ነበር። ተቃዋሚዎች አይገቡም በማለት የተጀመረው መክፈቻ በኋላ ላይ ግን ፖሊስ ከመጣ በኋላ እንዲገቡ ተፈቀደ ። ስብሰባው በጥያቄ ተጀምሮ ነበር። ተቃዋሚዎቹ ጥያቄውም እንዲ በማለት ጀመሩ፥
1 በመጀመሪያ እስከዛሬ እናንተ ከገባችሁ ጅምሮ ለገደላችሁት ሰዎች የህሊና ፀሎት ይደረግ በማለት ነበር የተጠየቀው በመቀጠል
2 እስከዛሬ እናንተ ያደረጋችሁትን የዘር ማጥፋት በአማራ፣ በኦሮሞ እንዲሁም በሕዝባችን ላይ የተደረገው ነገር ሳያንስ ዛሬ ደግሞ በአማራው ላይ የዘር ማፅዳት ዘመቻ እየፈፀማችሁና እየገደላችሁ እዚህ መጣችሁ ገንዘብ መጠየቅ ለኛ ድፍረት ነው በማለት በስብሰባው አዳራሽ በጩወትና በመፈክር ተናወጠ የወያኔ የስዊዲን አገር ቆንፅላም እንዲሁም ጀሌዎቹም በመፍራት አዳራሹን ለተቃዋሚዎች በማስረከብ ለቀው ወተዋል ! ።
ሌባ ነው ሌባ ወያኔ ሌባ በማለት የተጀመረው በመፈክር በጭወትና በዝማሪ አዳራሹ ተደበላልቋል!
ከገንዘብ በፊት ነፃነት ይቅደም!
ከገንዘብ በፊት ሰብኣዊነት ይቅደም!
ኢትዮጵያ አገራችን የደፈረሽ ይውደም! በማለት ተቃዋማቸውን ሲያሰሙ ነበር።
 የወያኔ/ ህውሃትና ጀሌዎች በአለም ላይ የሚያደርጉት የአባይ ገቢ ማሰባሰብያ በየአለማቱ ተቋውሞ እየደረሰበት ይገኛል።
በደቡብ አፍሪካ የተጀመረው ገቢ ማሰባሰብያ ሳይሳካ እንደውም ወያኔ የተከራየውን አዳራሽ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በማስወጣት ያሳዩትን ጀግንነት ቀጥሎ በሌሎች አገርም በአሜሪካ፣ በሳውዲ አረቢያ( ጅዳ) ፣በጀርመን ተቀጣጥሎ በቀጠለበት ሁናቴ በኖርዌይ ከፍተኛ የሆነ ተቋውሞ ደርሶበታል ።
በኖርዌይ የተጀመረው ገቢ ማሰባሰብያ ስብሰባ በመቃወም ወያኔ የተከራየውን ገቢ ማሰባሰብያ አዳራሽ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በማስወጣት የወያኔን ባንዲራ በማውረድ የኢትዮጵያን ትክክለኛውን ባንዲራ በመስቀል በማውለብለብ ወያኔዎችንና ጀሌዎችን በማባረር አዳራሹን ተቃዋሚዎቹ ተቆጣጥረውታል ። በአለማቱ ያሉቱ የወያኔ ቅጥረኛ አምባሳደር ተብዬዎች አንገታቸውን ያስደፋና እንደ ቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስተራቸው አንገትን አስደፍቶ፣አስደንግጦ ወደ መጡበት ያስመለሰ ነበር።አዳራሹ ውስጥ የነበሩት ተቃዋሚዎች ሙሉ በሙሉ ይበልጣሉ።ታሪክ በውጪ ባሉ ኢትዮጵያዊያን እየተሰራ ይገኛል!
 ኢትዮጵያውያን አንድነታቸው ተጠናክሯል ። የወያኔ የመገነጣጠል አላማ ስትራቴጂ የወደመበት ሆኗል።የሕዝቡም አንድነት የታየበት ነበር።ይህ በእንዲህ እንዳለ በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍም ሚያዚያ 18 2013 መካሄዱ ይታወሳል።
ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ በመሆን በመዘመርና በመፍክር ብሶታቸውን አሰምተዋል።
ተቃዋሚዎቹ በአንድነት በመሆን ያሰሙት ቃል ነበር
(( ገና ይቀጥላል ሁላችንም ነፃ እስከምንወጣ ድረስ ))
ሞት ለአንባገነን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!


                Posted By.Dawit Demelash

Breaking News: Ethiopians in Norway Chased TPLF Ambassador

Norway police stopped meeting in Tasta Bydelshus

Source: Aftenbladet
The police came out with three cars and six policemen and stopped a meeting of Tasta bydelshus where the atmosphere was becoming so very irritably among the more than 300 Ethiopian origin attendees.
The 300 attendees were Ethiopian asylum seekers or people with Ethiopian background. The police feared that it would get completely out of control when people in the audience went to the hard verbal confrontation against two representatives from the Ethiopian Embassy in Stockholm who had called for and chaired the meeting.Breaking News: Ethiopians in Norway Chased TPLF Ambassador
The police gave the first message that all protesters to leave the meeting while the two embassy people and their potential supporters can be seated. This denied the attendees protesters, and several feared it would come to an open confrontation between police and people in the audience. Then, specific efforts manager Øyvind Sveinsvoll of Rogaland police to stop the meeting and clear the room.
It was a wise decision, said several of those present protesters. They did not want the two embassy people should be left as “victors” while they were evicted.
- Our goal was to stop the meeting. We managed, says one of them to Eve magazine.
Had to isolate embassy people
The atmosphere was tense that the police chose to isolate the two embassy people from the rest of the participants. TheyBreaking News: Ethiopians in Norway Chased TPLF escorted them out to a private car that carried them away from the area. The 300 attendees were then drop out of the courtroom.
There was general consul at the Ethiopian Embassy, ​​Abay Mebrat Beyene, who would chair the meeting with embassy secretary. The main theme was collecting money in the Ethiopian exile to a very controversial prestige project for the regime in Ethiopia.
Mass demonstrations abroad
The Ethiopian authorities have tried to keep similar “recovery meetings” both in South Africa, Saudi Arabia, the U.S. and Germany, and each time meetings have ended in massive demonstrations against human rights violations in Ethiopia. People imprisoned without trial, free elections are abolished, freedom of speech likewise, newspapers are state controlled and hundreds of journalists imprisoned.
Not voluntary payment
Several took the floor during the meeting and said this was not a voluntary fundraising. Those who did not pay the money, you could expect problems when they contacted the embassy to obtain a passport or ID papers.
Gearing up for the Oslo-riot
Saturday’s meeting was the first of its kind in Norway. And exiled Ethiopians came in separate buses from Oslo, others came from Steinkjær, Otta, Stord and Bergen to demonstrate in Tasta bydelshus against the regime in Ethiopia.
28th April, the Ethiopian Embassy in Stockholm holds a similar meeting in Oslo.
- We are going to fill the buses with protesters, said several of those present to Eve magazine.

Saturday, April 20, 2013

በኖርዎይ ለዓባይ ግድብ ገንዘብ ለማሰባሰብ የተጠራው ስብሰባ ተበተነ


ዜና በጨዋታ፤ …አማራ ኦሮሞ እስላም ክርስቲያኑ… ባንድ ላይ ተባብረው በ…ያዲግ ጨከኑ

  

524625_10151537859584373_1860470982_nየቃላት መፍቻ… “…ያዲግ” የተባለው ኢህአዴግ በትክክል መጥራት ሲያቅተን ነው አሉ…!
“ኢህአዴግ እና ኢጣሊያን ዋነኛ የሚታወቁበት የአገዛዝ ስልት ከፋፍሎ የመግዛት ስልት ነው፡፡” እያሉ ምሁራኖች ይተነትናሉ፡፡ እኛም ኢህአዴግ ችርቻሮ ትወዳለች ብለን ብዙ ጊዜ ተናግረናል፡፡ በተደጋጋሚ እንዳየነው …ያዲግ ስታጠቃ እየነጠለች ነው፡፡ ሙስሊሙን ለብቻ፣ ክርስቲያኑን ለብቻ፣ ቆለኛውን ለብቻ፣ ደገኛውን ለብቻ፣ አማራውን ለብቻ ኦሮሞውን ለብቻ…
ታድያ ከሆነ ጊዜ በኋላ ይሄ ችርቻሮ ብዙ ያዋጣ አይመስለኝም፡፡ ክርስቲያኑ በሙስሊሙ ጥቃት አብሮ “ተክቢር” ሲል አሮሞው በአማራው ጥቃት አርማውን ይዞ “አሌሊ…” ሲል አማራው በኦሮሞው ጥቃት “ዘራፍ ወንዱ” ብሎ ሲነሳ እያየን ነው፡፡ … ይቺን ነው መሸሽ አሉ አብዬ መሸሻ ብለን እንቀጥላለን…
ዛሬ ሚያዝያ 12/2005 ዓ.ም በኖርዌይ ወይዘሮ መብራት በየነ የሚመሩት “የወዲህ በሉ” ቡድን ከስደተኞች ብር ወዲህ በሉ ለማለት ስብሰባ ጠርቶ ነበር፡፡ በስብሰባው በርካታ ኢትዮጵያውያን ቢገኙም፤ ለመንግስት ገንዘብ አለሰጡም… ለተወካዮቹ ሃርድ ሰጥተው አባረሯቸው እንጂ!
ኢትዮጵያውያኑ ያለ ኮከብ የሚያበራውን የኢትዮጵያ ባንዲራ እና መንግስት አሸባሪ የሚለው የኦነግንአርማ የያዙ ሲሆን ከያዙት መፈክር ውስጥ ደግሞ በቤኒሻንጉል ክልል የተደረገውን የአማርኛ ተናጋሪዎችን መባረር፣ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደረገው የእምነት ነፃነት ግፊያ የሚያወግዙ ይገኙበታል፡፡ “ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም” ም ተብሏል፡፡
ይህንን ሁሉ ውግዘት ቁጭ ብለው ሲኮመኩሙ የቆዩት ዲፕሎማት ወይዘሮም ምንም አማራጭ አለነበራቸውም … ካላችሁማ እመለሳለሁ እንጂ ምን አደርጋለሁ… ብለው ባዶ ቦርሳቸውን ሲመለሱ አልደብቃችሁም አንጀቴን በልተውታል፡፡
ዜናውን ከማብቃቴ በፊት ርዕሳችንን እንደግማታለን
አማራ ኦሮሞ እስላም ክርስቲያኑ
ባንድ ላይ ተባብረው በ…ያዲግ ጨከኑ… ኑ ኑ  ኑ… ብለንም የገደል ማሚቶ እናበጅለታለን!



    
    Posted By.Dawit Demelash

Friday, April 19, 2013


Protest rally in Oslo, Norway: Against the recent forceful eviction of Amharas

Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration
Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration opposing the recentevictions of ethnic Amharas from different parts of Ethiopia and demanding freedom in Ethiopia.
The demonstrators in their huge numbers showed their anger and frustration walking through the main street in Oslo and chanting slogans denouncing the barbaric act of the TPLF regime and demanding democracy and regime change in Ethiopia.
The participants in the demonstration were different organizations, political parties, supporting organs, civic organizations, religious groups and independent individuals reflecting Ethiopians unity and colorfulness!
The demonstrators have also meet the representative of the Norwegian parliament –Stortinget, and delivered their appeal.
In this demonstration Ethiopians in Norway not only showed their solidarity with all victims of TPLF in Ethiopia, but also confirmed their determination to confront any activities what so ever done in Norway by TPLF in the name of Ethiopian people!
             Posted By.Dawit Demelash

ኢህአዴግን በጓሮ ድርድር የጠየቀበት ሰነድ ተተረጎመ!

“የመሬት ነጠቃ” ዜጎችንና የተፈጥሮ ሃብት እየበላ ነው
cover 6

April 18, 2013 06:41 am 


በልማትና ኢንቨስትመንት ስም ኢህአዴግ ለውጪና ለራሱ ሰዎች እየቸበቸበ ያለውን መሬት አስመልክቶ የኦክላንድ ተቋምና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በጋራ ያዘጋጁት ጥናታዊ ዘገባ አማርኛ ትርጉም በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ ይደረጋል ተባለ። የመሬት ነጠቃ ዜጎችን እያፈናቀለና ውድ የተፈጥሮ ሃብትን እየበላ ነው።
እመራቸዋለሁ ለሚለው ህዝብና አገር ደንታ የሌለው ኢህአዴግ፣ በመረጃ ለሚያጭበረብራቸው ዜጎች የተሟላና የተመጣጠነ ዘገባ እንደሚያቀርብ የተነገረለት ይህ ሰነድ በአማርኛ ተተርጉሞ ይፋ እንደሚሆን የገለጸው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ዴስክ ነው።
የጋራ ንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ዴስክ በተለይ ለጎልጉል በሰጠው መረጃ በጥናቱ ሰለባዎች፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት፣ ኢንቨስተሮች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክፍሎች፣ የቅርብ ምስክሮች፣ የተለያዩ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የተገኙ መረጃዎች፣ መንግስት ራሱ ይፋ ያደረጋቸው መረጃዎችና ለጥናቱ አስፈላጊ የተባሉ አኻዞች ተካተውበታል።
በዚሁ መሰረት ኢህአዴግ በልማትና በኢንቨስትመንት ስም “ጥቅም ላይ ያልዋለ መሬት” በማለት ለንግድ ማቅረቡና፣ ይህም በመደረጉ አገሪቱ ውስጥ ልማት እንደሚስፋፋ የሚሰብከው ስብከት ያለ አንዳች ማስተባበያ እርቃኑን የሚያስቀረው ሪፖርት በዋናነት የተዘጋጀው መረጃ ለጠማው ህዝብ እንደሆነ ዴስኩ አስታውቋል።
አገራቸውን፣ መሬታቸውንና መንግስትን አምነው የሚኖሩ ዜጎችን በገንዘብ በመለወጥ ያፈናቀለውና እያፈናቀለ ያለው ኢህአዴግ፣ ምትክ የሌላቸውን እድሜ ጠገብ የተፈጥሮ ደኖች ጨፍጭፏል፤ አቃጥሏል፤ አውድሟል። ሰፊ መሬት ምድረ በዳ አድርጓል። ያለ አንዳች ምክርና ውይይት ዜጎችን አፈናቅሎ ለመከራ ዳርጓል። ንብረታቸውንና ማሳቸውን እንደ ባዕድ በዶዘር ጠርጎባቸዋል። ለመቃወም በሞከሩ ወገኖች ላይ የባዕድ ወራሪ ሃይል ይፈጽመዋል ተብሎ የማይገመት ወንጀልና መከራ አድርሷል። የጋራ ንቅናቄው የሚዲያ ዴስክ እንዳለው ኢህአዴግ ይህንን ሁሉ ሲፈጽም ጎን ለጎን ዜጎችን በመረጃ እያጭበረበረና እያስራበ በመሆኑ አሁን ይፋ የሚደረገው ሪፖርት ታላቅ ፋይዳ ይኖረዋል።
ለጋሽ ድርጅቶች፣ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብና አበዳሪ ድርጅቶች አቋማቸውን እንዲመረምሩ ለማስቻል ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑንን ያወሳው የጋራ ንቅናቄው “የመሬት ወረራው መቆሚያ የሌለው፣ እንዲያውም በቀጣይነት የሚከናወን በመሆኑ ይፋ የሚደረገው ይህ መረጃ አገር ቤት ገጠር ሳይቀር ዘልቆ እንዲገባ ለማድረግ ዝግጅቱ ተጠናቋል” በማለት አስረድቷል። ይሁን እንጂ መረጃው እንዴት እንደሚሰራጭ ዝርዝር ማብራሪያ አላቀረበም።
ወደፊት ጥናትና ምርምር የሚያካሂዱ ተቋማትም ሆነ ግለሰቦች ሊጠቀሙበት እንዲችሉ ተደርጎ በዝርዝር የቀረበው ይህ ሪፖርት፣ በእንግሊዝኛው ጥቅል ጥናት ውስጥ በሰባት የአፍሪካ አገራት ተከፋፍሎ የተዘጋጀ ሲሆን ወደ አማርኛ በተቀየረው ትርጉም ውስጥ ሙሉ ትኩረት የተደረገው በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ እንደሆነ ተመልክቷል።
congress briefings
አቶ ኦባንግ በም/ቤቱ ውይይት ወቅት ማብራሪያ ሲሰጡ
“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በሦስት ዓቢይ ምዕራፎችና በበርካታ ንዑሳን ክፍሎች ተከፋፍሎ የተዘጋጀው ከ110 ገጽ በላይ የሆነው የአማርኛው ጥናታዊ ሪፖርት “የሰከነው” ትግል ውጤት እንደሆነ የመረጃ ዴስኩ አስታውቋል። በቅርቡ የጋራ ንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ህንድ በመሄድ ያነሳሱት የትግል አብሮነት ስሜት ያነሳሳ ነበር፡፡ ከሁለት ቀናት በፊት ደግሞ ሰኞ ዕለት በአሜሪካው ምክርቤት ለውይይት በመሬት ነጠቃ ጉዳይ ላይ የቀረበውና ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠውን ይህንኑ የመሬት ነጠቃ ጉዳይ በምክርቤት ተገኝተው ገለጻ ከሰጡት መካከል አቶ ኦባንግ አንዱና ዋንኛው መሆናቸውን የሚዲያ ክፍሉ ጨምሮ አስታውቋል፡፡ ይህም ለመሆን የቻለውና ጉዳዩ በከፍተኛ ደረጃ ተደማጭነት እያገኘ የመምጣቱ ሁኔታ ከፍተኛ ድል እየሆነ ከመምጣቱ የተነሳ ኢህአዴግ የሚተማመንባቸውንና ከፍተኛ የገንዘብ ምንጭ የሆኑ አገራትንና ተቋማት እጅ የማስጠምዘዝ ሁኔታ ሊያስከትልበት እንደሚችል በመገንዘብ ካድሬዎቹን በየቦታው በማሰማራት ከፍተኛ የውስወሳ ዘመቻ እያካሄደ እንደሚገኝ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ በዚህ ረገድ የጋራ ንቅናቄው እጅግ ከፍተኛ ሥራ ላይ የተጠመደ መሆኑን ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡
የጋራ ንቅናቄው አክሎ በሰጠው ማሳሰቢያ አደራም አስተላልፏል። በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ የሚደረገው ይህ ጥናታዊ ሪፖርት ምንም እንኳ የጋራ ንቅናቄው ንብረትና የኮፒ ራይት ያለው ቢሆንም “ሪፖርቱን ለማራባትና ለማሰራጨት የሚፈልጉ ሁሉ ለሪፖርቱ ባለቤትና አዘጋጆች ጨዋነት የተሞላው እውቅና ሊሰጡ ይገባል” ሲል ጥሪውን አቅርቧል። በማያያዝም በሚቻላቸው መንገድ ሁሉ ሪፖርቱን ለማራባት ለሚተባበሩ ወገኖች ከወዲሁ ምስጋናውን አቅርቧል። ሪፖርቱ እንዲደርሳቸው ለሚፈልጉ ሁሉ በኢሜል ለመላክ ፈቃደኛ በመሆኑ በሚከተለው አድራሻmedia@solidaritymovement.org ጥያቄ ቢያቀርቡ እንደሚተባበር አመልክቷል። የመሬት ነጠቃን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የሚያካሂደውን እቅድን መሰረት ያደረገ ትግል አጠንክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል።
      Posted By.Dawit Demelash

Thursday, April 18, 2013


ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ የተመለሱ የአማራ ተፈናቃዮች በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ ታወቀ

ሚያዚያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሀይል ተፈናቅለው በፍኖተሰላም እና ቻግኒ ከተሞች ሰፍረው የነበሩ ከ8 ሺ ያላነሱ የአማራ ተወላጆች ኢትዮጵያውያን ባሳደሩት ጫና ወደ መጡበት አካባቢ እንዲመለሱ ቢደረግም፣ በአካባቢው ያጋጠማቸው ያልጠበቁትና በህይወት የመቆየታቸውን ነገር አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጸዋል።
መሬት ያላቸው ተወላጆች ተመላሽ ተፈናቃዮችን ስራ ለመቅጠር ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሰርተው ለማደር ተቸግረዋል። የዞን እና የወረዳ ባለስልጣናት የአካባቢው ሰዎች ተፈናቃዮችን ስራ እንዳይቀጥሩዋቸው ቅስቀሳ በማድረጋቸው ሰዎቹ ለመቀጠር አለመቻላቸውን ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮች ይገልጻሉ።
የተፈናቃዮችን ችግር ያባባሰው ደግሞ መንግስት የሰጣቸው የምግብ ዱቄት የጤና ችግር ማስከተሉ ነው።  ብዙዎቹ ተፈናቃዮች በተቅማጥ በሽታ እየተሰቃዩ መሆኑን ይናገራሉ። በአካባቢው ያለው መለስተኛ የጤና ተቋም በአማካኝ ከአራት ሰአት የእግር ጉዞ በሁዋላ የሚገኝ ሲሆን፣ በእግር ተጉዞ ህክምና ለማግኘት እንኳ የገንዘብ ችግር አጋጥሟቸዋል።  አርሶአደሮች እንደሚሉት ለበሽታ የዳረጋቸው ጊዜው ያለፈበት የተበላሸ ዱቄት ስለተሰጣቸው ነው።
የተለያዩ ተፈናቃይ አርሶአደሮችን አነጋግረን ለመረዳት እንደቻልነው ተፈናቃዮቹ ባለቡት ቦታ ስራ ለመጀመር ካልቻሉ ወደ መጡበት ቦታ ለመመለስ ፍላጎት አላቸው። አርሶደአሮቹ ንብረታቸው በሙሉ በዝርፊያ ያጡ በመሆኑ እንደ መጀመሪያው ጊዜ የትራንስፖርት ከፍለው ወደ መጡበት ቦታ መመለስ አይችሉም።
በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ህጻናት የትምህርት እድል አጥተው ጊዜያቸውን በከንቱ እያሳለፉ መሆኑንም ለማወቅ ተችሎአል።
በጉዳዩ ዙሪያ የፌደራል መንግስቱ ባለስልጣናትን አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር የሆኑት አቶ ብርሀነ ገብረክርስቶስ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት የአማራ ተወላጆች ህገ ወጥ የመሬት ወራሪዎች በመሆናቸው መፈናቀላቸውንለጀርመን ድምጽ መግለጻቸው ይታወሳል። የራዲዮ ጋዜጠኛዋ ” የክልሉ መንግስት እኮ ተሳስተን ነው ያፈናቀልናቸው በማለት መግለጫ ሰጥተዋል የሚል ጥያቄ ሲቀርብላቸው ” ተፈናቃዮቹ መመለሳቸውን አላውቅም” በማለት የሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት አለ እንዴ? የሚል ጥያቄ በማስነሳት እያወያየ ይገኛል።
       Posted By.Dawit Demelash


ኢሕአግ ሰራዊት በዋልድባ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ


የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር (ዜና)
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በዋልድባ አካባቢ ልዩ ስሙ ሰቋር እና አምቦ ጠበል በተባለ ቦታ በተከታታይ ሁለት ቀናት ከወያኔው የፈጥኖ ደራሽ ጋር ባደረገው የፊት ለፊትEthiopian People Patriotic Front ውጊያ በጠላት ላይ ወታደራዊ የበላይነትን በመቀዳጀት አኩሪ የአርበኝነት ጀብድ ፈፅሟል።
የግንባሩ ሰራዊት በዋልድባ ልዩ ስሙ ሰቋር በተባለ ቦታ በሚያዚያ 8-2005 ዓ.ም የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ መመኪያ በሆነው የፈጥኖ ደራሽ ላይ በከፈተው የማጥቃት እርምጃ 21 የጠላት ወታደሮችን በመግደል 25 ያቆሰለ ሲሆን፣ በተመሳሳይ በሚያዚያ 9-2005 ዓ.ም በዋልድባ ልዩ ስሙ አምቦ ጠበል በተባለው ቦታ ውጊያው የተካሄደ ሲሆን በዚሁ እለትም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት 25 የጠላት ወታደሮችን ገድሎ 39 በማቁሰል ከፍተኛ ድል የተቀዳጀ ሲሆን፣ በዚሁ አውደ-ውጊያ ላይም የተለያዩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያዎችንም ከመሰል ጥይቶቻቸው ጋር ማርኳል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በሁለት ተከታታይ ቀናት ባደረጋቸው አውደ-ውጊያዎች ላይ በድምሩ 46 የፈጥኖ ደራሾችን ከጥቅም ውጭ በማድረግና 64 በማቁሰል የግንባሩ ሰራዊት የተሰለፈበትን ሐገራዊ ተልዕኮውን በመፈፀም በጠላት ላይ ከፍተኛ የሕይወትና የንብረት ኪሳራ በማድረስ አኩሪ የአርበኝነት ጀብድ ፈፅሟል።
የግንባሩ ሰራዊት ጥቃቱን በፈፀመበት አካባቢ የሚኖሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችም ስርዓቱ በሚያራምደው የግፍ አገዛዝ ከፍተኛ ምሬትና ተቃውሞ እያሰሙ ሲሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትም የጀመረውን ወታደራዊ የማጥቃት እርምጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን አስተዋፅዖ በማበርከት ሐገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ወደ ግንባሩ ሰራዊት እየተቀላቀሉ እንደሚገኙም ታውቋል።
    Posted By.Dawit Demelash

ታላቋ ትግራይን” የመመስረት የ 21 ዓመታት ጉዞ



በ1968 ዓ ም ባወጣው ማንፌስቶ ህወሓት “ታላቋን ትግራይ” ከኢትዮጵያ ገንጥሎ የራሷን ሪፐብሊክ እንድትመሠረት የማድረግ ግብ ነድፎ እንደነበር የግንባሩ መስራች አባላትThe 1976 TPLF Manifesto TPLF’s “Republic of Greater Tigray” የመሰከሩት ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያዊነቱ በሚኮራው የትግራይ ሕዝብ ማንፌስቶው ተቀባይነት እንደማያገኝ የሕወሓት መሪዎች ሲረዱ ትተነዋል ብለው ቢያውጁም እነመለስና ስብሀት ግን ለ 21 ዓመታት ሲፈፅሙት የኖሩት ያን ግብ ለማሳካት ነበር። ዋና ዋናወቹን ክንውኖች እንመልከት፦
1ኛ. ህወሓት ጫካ እያለ የሰራውን “የታላቋን ትግራይ” ካርታ እውን ለማድረግ ከጎንደርና ከወሎ ሰፋፊ ለም መሬቶችን በማንአለብኝነት በመውሰድ ወደትግራይ ከለለ። ኢትዮጵያን በዘር ሸነሸነ፤ ኢትዮጵያዊያንን በዘር በመከፋፈል ስለ አንድነታቸው ሳይሆን ስለልዩነታቸው እያሰቡ እንዳይተባበሩ ለማድረግ ተጣጣረ፤ በኢትዮጵያዊነት ላይም ዘመተ።
2ኛ. ሕወሓት ባረቀቀው አዲስ ህገ መንግስት “የራስን ዕድል በራስ መወሰን እስከ መገንጠል ድረስ” የሚል አንቀፅ አስገባ፤ በአንቀፅ 39 ላይ ተቃውሞ ሲነሳ መለስ ንዴቱን መቆጣጠር ተስኖት በቁጣ መልስ ይሰጥ እንደነበር እናስታውሳለን።
3ኛ. በትግራይ ውስጥ ታላላቅ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፤ ይህ ዕቅድ በመጀመሪያዎቹ 10 ዓመታት በአብዛኛው የተከናወነ ሲሆን ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በስፋት ሲሰራ ቆይቷል። በሁመራ የሚመረተው ጥጥ ለአድዋ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች በጥሬ ዕቃነት ሲያገለግል ሰሊጡ ደግሞ ወደውጭ እየተላከ የወያኔ መሪዎችን የዶላር ክምችት በማድለብ ላይ ይገኛል። ሞሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ደግሞ ምርቱን ወደ ሱዳን ይልካል፤ መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ በበኩሉ የተሽከርካሪ ገበያውን ለመቆጣጠር እየተጋ ይገኛል።
4ኛ. ሁለቱን ታላላቅ ጎሣዎች ማለትም ኦሮሞውንና አማራውን ማዳከም፤ ሕወሓት ገና ጫካ እያለ ኢትዮጵያን ለማዳከምና ለመበታተን በአማራው ሕዝብና በኦርቶዶክስ ክርስትና ሀይማኖት ላይ መዝመት እንዳለበት የነደፈው ግብ እንደነበርና አሁንም እየተገበረው እንዳለ ወንድማችን አቶ ገብረመድህን አርአያ በየጊዜው ሲያስታውሰን ቆይቷል። ባለፉት 21 ዓመታት ወያኔ በተለይ የአማራ ተወላጆችን ሲረሽን፣ በገደል ሲወረውር፣ ከቤት ንብረታቸው ሲያፈናቅል ኖሯል፤ አሁንም ይህን እኩይ ዓላማውን ቀጥሎበታል። እጅግ በርካታ የኦሮሞ ምሁራንና ተማሪዎችን መግደል፣ በአሸባሪነት መክሰስና በእስር ቤት ማጎሩንም ቀጥሏል።
5ኛ. ትግራይን በኃይል አቅርቦት ራሷን ማስቻል፣ በመጀመሪያ ወያኔ ጭስ አባይ ቁጥር 2 ብሎ ከሰራው የኃይል ማመንጫ የሚነሳ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እስከ ትግራይ ዘረጋ፤ የአባይ ውሀ የተጠለፈው ፏፏቴው ከመድረሱ በፊት ስለሆነ ወደጭስ አባይ የሚጎርፈው ሀገር ጎብኝ በእጅጉ ቀነሰ፤ ከዚያም የተከዜን ኃይል ማመንጫ ገነባ፤ አሁን ደግሞ በመቀሌ አካባቢ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታ በፈረንሳይ ኩባንያ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
6ኛ. ትግራይ የራሷ ወደብ እንዲኖራት ማድረግና ከወደብ የሚያገናኛት የባቡር ሀዲድ መዘርጋት፣ ከጥቂት ወራት በፊት አቶ ኃይለ ማሪያም ደሳለኝ በታጁራ ወደብ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠው ተመልሰዋል፤ በመለስ ዕቅድ መሠረት ያ ወደብ በቀጥታ በባቡር መስመር የሚገናኘው ከትግራይ ጋር ነው።
7ኛ ትግራይን በማዕድን ሀብት ማበልፀግ፣ እስካሁን ድረስ በትግራይ የማዕድን ፍለጋ በስፋት ሲካሄድ ቆይቷል፤ በቅርቡ የተገኘው የወርቅ ማዕድን ለወያኔ ተስፋ ሰጪ ሆኗል፤ በግዙፉ የኤፈርት ኩባንያ የሚካሄዱ የማዕድን ፍለጋ ፕሮጀክቶች እየተበራከቱ ነው።
8ኛ. የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በሕወሓት ኩባንያዎች ቁጥጥር ሥር ማድረግ፤ ባለፉት 21 ዓመታት ከሕወሓት ጋር ንክኪ የሌላቸውን ነጋዴዎች ከገበያ በማስወጣት ወያኔ የሀገር ውስጡንና የውጭውን ንግድ ተቆጣጥሯል። በይፋ ጤፍ ወደውጭ እንዳይላክ ቢያውጅም የራሱ ነጋዴዎች በኮንትሮባንድ ጤፍ ወደውጭ እየላኩ የጤፍ ዋጋ እጅግ እንዲንር አድርገዋል፤ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን በልቶ ማደር እያቃተው ነው።
ስለዚህ ወያኔ እስከቻለ ድረስ በስልጣን ላይ ተቀምጦ ኢትዮጵያን ለመግዛት፣ ከስልጣን ቢባረር ትግራይን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል መሠረቱን ጥሎ አጠናቋል። በዘረኝነት መርዝ እስከእለተሞቱ ተለክፎ የነበረው የመለስ “ራዕይ” ይህ ነበር፦ ኢትዮጵያን መበታተን፣ አማራውን ማዳከምና ማጥፋት፣ ሌሎች ብሔረሰቦችን እርስ በእርስ ማናከስ፣ “ታላቋ
ትግራይ” ን መመሠረት። ይህን የዘረኝነትና ፀረ ኢትዮጵያዊነት “ራዕይ” ነው እናስቀጥላለን የሚባለው።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

    Posted By.Dawit Demelash 

TPLF/EPRDF Nefarious Deeds That Will Blow Your Mind - Ethnic Cleansing



By Ewnetu Sime

We are witnessing unprecedented hatred to Amhara ethnic group under Tigrai People’s Liberation Front (TPLF)/ Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Party (EPRDF) ethno-centric dictatorial rule. As soon as TPLF/EPRDF came to power in 1992, the regime and supporters began to brutalize the Amhara ethnic group in particular. A well-coordinated support with extremist loyalist to the TPLF/EPRDF regime incited conflict in Arba Gugu, Hararghe area against the Amhara ethnic group. The houses of Amhara were burned with people inside, people were killed thrown over the cliff, people of hacked to death in broad day light, robbed, bodies mutilated by regime supporters., Some of the lucky ones fled to Addis Ababa, other took shelters in nearby towns. Ethnic cleansing was conducted in unprecedented scale. In 2012, poor farmers of Amhara ethnic group from the southern part of Ethiopia were expelled. People were made homeless; similarly, in 2013 Amhara ethnic group from Benishangul-Gumuz area forceful evicted. TPLF/EPRDF’s ethnic dictatorship anti-Amhara policy claimed many lives in many parts of Ethiopia. Sadly, the TPLF/EPRDF's leaders and associated tugs are getting away with ethnic cleansing crimes. To-date no one is charged for it.
It is evident that as Derg came to power in 1974, they ruled the whole country in terror and brutality. Derg’s regime was faced with resistance and gravely weakened and finally defeated by TPLF/EPRDF and Eritrea Peoples Liberation Front (EPLF) guerrilla warfare. TPLF/EPRDF guerrilla movement transformed to large scale by recruiting fighters partly by intimidation of the Tigeran peasants, and finally able to mobilized thousands of fighters. They disseminated in their fighters propaganda of hatred to other ethnic and continuing to exhibit parochialism even after they assumption of power. Before TPLF enter Addis Ababa they quickly formed EPRDF to get a cover as an Ethiopian force. The TPLF claims in its propaganda that they fought Derg dictatorship for the pursuit of liberty or ideals of democracy has been revealed as carefully crafted deceptions. It is not too surprising that it is done to stay in power by coercion enforced by viscous Agaiz private armies that are recruited from one minority ethnic and secret police organization to continue their tyrannical rule.
As we briefly look back why the Weyane’s/TPLF revolt started we found that primarily reason was a conflict with the local authority to protect economic interest within Ethiopia. However, in mid-1970’s the Weyane intelligesta has shifted from the regional problem to call secession from the centralized Ethiopia state. For this reason, since the guerrilla years the Tigrian identity and historical heritage to Ethiopia has been deliberately and systematically reinvented by their leaders to mislead others. The rich and long Ethiopians history and nationalism has been distorted.
Their leaders have no love for Ethiopia or compassion for people except for their interest that is driven in creating non-viable ethnic states and provoking ethnic conflicts.
It is well to remind ourselves, their supreme leader Meles Zenawi made statements in public that Ethiopia flag is a piece of rug, proud to be pure gold ethnic, has done treachery acts about Assab, the Algerian agreement etc. all these originated from dogmatic ethnic political beliefs.
Furthermore, as TPLF/EPRDF’s seized the power, they implemented the divide and rule strategy under disguise of ethnic rights ideology. It quickly adopted a new constitution “the right of ethnic/nationalities Rights” under Article 39, 46 and 47. Of course, these articles objective are to divide and rule at same time to erode the eighty nationalities unity and diversity that coexisted side by side for generations. Even though active social interaction and intermarriage among nationalities is always a given fact.
The recent forceful eviction of members of the Amhara people from Benishangul-Gumuz area is indeed a direct implementation of the TPLF/EPRDF’s ethnic policy. They have a wrong belief that creating ethnic conflict is the foundation of their strength to stay in power. As demonstrated with above few facts, they are deliberately creating ethnic conflict as one of the tactics to stay in power.
We cannot afford to remain as onlookers where ethnic cleansing encouraged by regime. As stated by many scholars the international laws is applicable for this type of crime, and TPLF/EPRDF leaders can be charge by ethnic cleansing. This cannot be seen as a long shot. The role of Ethiopians, at least in USA, has to demand through available avenues such email/letters/on line petition, etc. to our senators, congressmen/women to expose the ongoing ethnic cleansing act. We should always keep in mind that the Opposition political groups, independents journalist, other concerned citizens risked all they had, their families, friends, homes, etc. all these sacrifice is for glimmering hope of a better life for all Ethiopians.
We should support them by intensifying campaign in exposing their ethnic cleansing that blow our minds, and put in its own coffin as seen in past world history. Ethnic cleansing is barbarous and heartless. As it said in the past, if you care about Ethiopia do not remain idle, get involved and make your voice be heard. It will take a massive effort, discourse, dialogue, and to get Ethiopia back on its feet and to make it home again for all Ethiopians.

         Posted By.Dawit Demelash

ከፍንጂ ማምከኛ ድርጅት በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሀብት ተዘረፈ



ሚያዚያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በአፍሪካ ውስጥ ካሉ ሶስት የፈንጅ አምካኝ ድርጅቶች መካከል በአገልግሎት ዘመኑም ሆነ በተግባሩ በግንባር ቀደምነት ስሙ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ፈንጅ አምካኝ ድርጅት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ እንደፈርስ መደረጉን ተከትሎ፣ ከተለያዩ የውጭ አገራት በእርዳታ ከተሰጠው በመቶ ሚሊዮኖች ከሚቆጠር ገንዘብ በተጨማሪ፣ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶቹ በወታደራዊ መኮንኖች እንዲዘረፍ መደረጉን የውስጥ ምንጮች ገለጹ።
አብዛኞቹ የድርጅቱ ከባድ መኪናዎች እና ሌሎች ንብረቶች በወታደራዊ አዛዦች መወሰዳቸውን የገለጡት ምንጮች ጉዳዩ ያሳሳበው የጸረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ቢጀምርም ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ምርመራውን አቋርጣል።
ከ100 እስከ 150 ሚሊዮን የሚጠጋ ገንዘብ መዘረፉን የገለጡት ምንጮች፣ ከዝርፊያው ጋር እጃቸው አለበት የተባሉት መኮንኖች በዘረፉት ገንዘብ ከፍተኛ ህንጻዎችን እያስገነቡበት መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአንድ የመምሪያ ሀላፊነት ቦታ ላይ የነበሩ ሰው ድርጅቱ  ከአውሮፓ እና ከአሜሪካ መንግስት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እየተደረገለት በጥሩ ሁኔታ ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ፣ በድንገት የተወሰኑ ወታደራዊ አዛዦች በድንገት ተመካክረውና በቂ ጥናት ሳይደረግበት ከ7 መቶ በላይ ሰራተኞችን በማባረር እንዲፈርስ አድርገውታል ብለዋል። ወታደራዊ አዛዦቹ የተወሰኑ ቁሳቁሶችን ለፌደራል ፖሊስ ያስረከቡ ቢሆንም፣ አብዛኛውን ንብረት ያለጠያቂ በመከፋፈል መውሰዳቸውን እኝሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።
ከ3 ወራት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው የነበሩት የድርጅቱ ሰራተኞች ሰሚ አጥተው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውንም እኝህ ባለስልጣን ገልጸዋል።
ድርጊቱ በህወሀት ታማኝ ጀኔራሎች መካከል የጥቅም አለመግባባት ፈጥሮ እንደነበርም ታውቋል።
በኦሮሚያ ክልል ፍቼ ከተማ  የነበረው  ጽህፈት ቤት ፈርሶ በአሁኑ ጊዜ ሌላ ጽህፈት ቤት መቀሌ ውስጥ እንዲከፈት መደረጉንም እኝሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
በኢትዮጵያ ውስጥ ከላይ እስከታች የሚገኙ ባለስልጣናት የሚፈጽሙት ሙስና በአገሪቱ ውስጥ የሚታየውን የኑሮ ውድነት ከማባባስ በተጨማሪ በህብረተሰቡ ውስጥ ያለው የኑሮ ልዩነት እንዲሰፋ እያደረገው ነው።
ለገዢው ፓርቲ ቅርብ የሆኑ ሰዎች በአንድ ጀምበር ሚሊየነር የሚሆኑበት አሰራር በመጨረሻ አገሪቱን እንደሚጎዳ ብዙዎች አስተያየት ይሰጣሉ።
ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ የተባለው ተቋም ባለፉት ስምንት አመታት ከኢትዮጵያ ከ 180 ቢሊዮን ብር በላይ ተዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች መከማቸቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሌላ በኩል ግን አገሪቱ ከቻይናና ከህንድ የተበደረችውን ገንዘብ ሳይጨምር 150 በሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ የውጭ እዳ አለባት።
ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች እና የመንግስት ባለስልጣናት በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች የሚገነቡዋቸውን አንዳንድ ህንጻዎች በፎቶ ግራፍ በማስደገፍ ማቅረባችን ይታወሳል።
ኢህአዴግ በ9ኛው ጉባኤ ሙስናን ለመዋጋት ቃል መግባቱ ይታወሳል።
         Posted By.Dawit Demelash

Wednesday, April 17, 2013


The Rulers of Ethiopia Should Face Justice for Crimes They Committed Against Amharas in Ethiopia

One may ask why rulers commit genocide, crimes against humanity, and ethnic cleansing on the very people they rule. Although nothing would justify, heinous rulers always provide bizarre and incomprehensible justifications. The tyrants in Ethiopia, for example, sayAmharas were evicted because they cut trees. For them cutting trees is enough reason to commit ethnic cleansing and crimes against humanity.  As the world knows, these kinds of despicable crimes have been committed in Rwanda, Liberia, Sudan, Ethiopia and other countries. The star actors of genocide and crimes against humanity in Rwanda, Liberia and Sudan are already facing justice. The tribal and racist-primitive rulers who have been committing ethnic cleansing and crimes against Amharic speaking people (the Amharas) for the last 22 years in Ethiopia are still leaving lavish lives at the expense of the resources of their victims-the Amharas.
Would you please listen to these verses, Emama Ethiopia?
“My country, Ethiopia
  You are fool, deceivable
You feed your murders
While you starve your martyrs!”
No single spot exists in the mountains, plains, low lands, deserts, jungles, rivers and lakes, where Amharas did not spill their blood to protect the national integrity and sovereignty of Ethiopia. A lot has been said about the battle of Maqdala, Adwa, Mychew, and The Five-Year War with Facist where Amharas gave their chest for bullets and their whole body for mustard gas in order to transfer a proud and free country to us.  Let’s just gaze at the very near past. It was the Amhara peasants who broke the back bone of invader Siad Barre. It was the Amhara militia who protected our natural sea ports until mama Ethiopia’s neck and breasts were butchered by her traitor children. What is the gladiator Amhara getting in return now? Systematic discrimination, frequent eviction, endless displacement, repeated ethnic cleansing, chronic crime against humanity, and genocide?
One of the leading Ethiopian online news papers on Ethiopian affairs, Ethiomedia, covered on its March 17, 2013 front page, that 59 uprooted Amharas were killed by car accident in Benishngul Gumuz, western Ethiopia while they were forcefully evicted after their property was confiscated. [1]  Similarly the Ethiopian Satellite Television, an independent news outlet, reported that more than 3, 000 people were evicted from Benishangul area. [2]   These crimes were also discussed in the Voice of America Amharic program.[3]  The evicted people and the deaths include children and pregnant women. Mind you, the victims only crime was being born Amhara.  Dr. Yakob Hailemariam, one of the Lawyers who investigated the Rwandan Genocide, call this act of the TPLF lead government ethnic cleansing. [4]
In this 21st century human traits such as age, gender, and ethnicity are protected human characters. In civilized societies (at least in theories), discriminating based on these protected traits is illegal and immoral. However, concepts such as legality and morality are not found in the dictionaries of the barbaric tribal rulers of Ethiopia. Unfortunately, the ruling party’s fundamental policy in Ethiopia dictates cadres to organize people based on ethnicity and the language they speak. Furthermore, this backward policy (The Wild-animals’  law as the distinguished scholar professor Mesfin woldemariam calls it)promotes the different ethnic groups to discriminate each other based on human nature such as race, language, religion and so on. The Amharas, who are mainly against this uncivilized jungle law,  have been the prime victims of this brutal and retarded policy since the racist Tigrai People Libration Front (TPLF) took power through a Trojan horse- the Ethiopian Democratic Libration Front (EPRDF).
The Amharas are the second largest ethnic group in the country. Some, in fact, argue that Amhara could be the largest group in the nation if counted in unbiased manner. Ancient and modern history teaches that this population group existed with other ethnic groups in Ethiopia and the surrounding East African countries since humans started to live as society on this earth. However, the Amharas have never claimed certain regions of Ethiopia as their own sole state. Unfortunately, TPLF created a segregated area called Amhara killil (Killil -a local term for segregation) for these groups of people.
Many including former members of TPLF have stated  that TPLF leaders have been labeling the  Amharic speaking people as their  enemies since they organized themselves as communist Guerilla fighters in the early 70’s.[5]  The crimes committed against Amharic speaking people since this rebel group (formerly labeled as terrorist group by USA) took power are the practical applications of this former communist Guerilla fighters’ racist-jungle manifesto.
As mentioned above, systematic discrimination of Amhara has been on the making for more than two decades. As soon as the TPLF took power in 1991, it cleansed more than 42 intellectuals (almost all of them Amharas) from the teaching positions at Addis Ababa University.[6]  It established a unique and effective contraception programs in the Amhara communities to reduce the number of births. No sane Amharic Speaking individual with viable conscience is allowed to take key positions in the government. Those individuals who claim to represent the Amharas in the government are either non-Amharas or Amharas who sell out their soul and conscience to money and other ephemeral advantages.
About two years after the TPLF took power, thousands of Amharic speaking people including women and children were massacred in the eastern part of the country called Bedeno.[7]   It needs an outstanding historical film maker to document how these unfortunate people were thrown away from the top of the cliff as high as 100 meters. It takes Schindler’s List film director to document the suffering of the children of these victims.  It takes the skill of a horror film maker to produce how women were repeatedly raped in front of their husbands during this crime against humanity. Similar crimes have been committed against Amharic speaking people in Central, Southern, Western and Northern Ethiopia.   Such kinds of atrocities were relatively abated by the formation of the All Amhara People Organization. Unfortunately, this organization’s leader, Professor Asrat (the first surgeon in the country), was incarcerated and died because he was denied access to medical care by TPLF lead government.
As a continuation of “cleanse the Amharas motto”, thousands of Amharic speaking people were forced to leave from Gura Ferda (southern Ethiopia) in 2012.[8]    These unfortunate people were forced to leave their houses and other property behind and no one really knows who exactly has robbed their possessions.  Many have suffered and died during this disgraceful ethnic cleansing.  Only God and the victims know about what happen to the cleansed victims who are not dead at this point. The officials who systematically conducted theses dreadful crimes still hold higher positions in the States and Federal Government. Such is the case in the current Ethiopia-you commit wicked crime, you get promotion.
Besides being forcefully evicted from their homes at the different regions of the country, Amharas also roam to different parts of the world even to the failed state Somalia to escape the systematic discrimination and ethnic cleansing. During this mass migration, Amharas die every day in hundreds from various causes such as flood, wild animals, hunger, diseases, etc. Still among those who are able to escape and live in the foreign land, many die of slavery and suicide.
In summary, Amharas were not born Amharas by choice. Their ethnicity or language is their protected identity. Above all, the evicted Amharas fathers’ and forefathers’ have spilled their blood in every corner of Ethiopia to defend the sovereignty and pride of our nation. The land currently cultivated by Indian, Chines and Arab traders is enriched with Amhara’s blood and flesh.  Despite this glorious history of their ancestors, Amharas have been discriminated and cleansed by TPLF lead government which is composed of disloyal and treacherous individuals who sold out our sea access and fertile land. This act of the narrow-minded TPLF government is not just totally immoral but absolute crime that should not happen in 6000 BC let alone in 21st century.  If the TPLF lead rulers continue the ethnic cleansing of Amharic speaking people with this rate, Amharas will be endangered species in the near future. Therefore, those people who have direct or indirect participation in systematic discrimination, evicting, and ethnic cleansing of the Amharas or any other ethnic group should face justice as soon as possible. Lawyers and Judges (especially of Ethiopian origin) have professional, moral, ethical, historical and national responsibility to force these horrendous criminals face justice.
   Posted By.Dawit Demelash