Thursday, April 30, 2015

ግብፅ፤ በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውን የአይ.ኤስ.አይ.ኤስ መቀመጫ ለመደምሰስ ዝግጅቷን አጠናቀቀች

የግብፅ መንግስት በምስራቃዊ ሊቢያ ዴርና ከተማ የከተመውን አይ.ኤስ.አይ.ኤስ አሸባሪ ኃይል ለመደምሰስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የወታደራዊና የደህንነት መረጃዎችን በማጠናከር የሚዘግበው ዴብካ ፋይል ድረ ገጽ ይፋ አደረገ።

ግብፅ ከፍተኛ መጠን ያለው የምድር ጦር እና አየር ሃይሏን በማቀናጀት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውን የአይ.ኤስ.አይ.ኤስ አሸባሪ ኃይል ለመደምሰስ እና ምስራቅ ሊቢያን ለመቆጣጠር የግብፅ ወታደራዊ ሃይል በተጠንቅ መሆኑ ታውቋል።

ግብፅ ይህን ወታደራዊ ዘመቻ የምታከናውነው ፕሬዚዳት አብዱል ፈታህ አል-ሲሲ በደረሳቸው የሀገር ውስጥ ደህንነት መረጃ ሲሆን የደህንነት መረጃዎቹ እንደሚያሳዩት በምስራቅ ሊቢያ የከተመው የአይ.ኤስ.አይ.ኤስ አሸባሪ ቡድን በግብጽ ብሔራዊ ደህንንት ላይ አደጋ መጋረጡን ነው። ይህም ሲባል፣ የእስልምና መንግስትን ለመመሥረት ያቀዱት እነዚሁ አሸባሪዎች በአንዳንድ የግብፅ ከተሞች ሰርገው መግባታቸው ተረጋግጧል። እንዲሁም በግብጽ ጦር ሰራዊት ውስጥም መስረጋቸው የደህንነት መረጃዎች አሳይተዋል።

የአይ.ኤስ.አይ.ኤስ አሸባሪ ቡድን በበኩሉ የግብፅ እንቅስቃሴ ስላሰጋው ከኢራቅ እና ከሶሪያ አሸባሪ ሃይሎችን እያመጣ ወታደራዊ እቅሙን እያጠናከረ እንደሚገኝ ለማወቅ መቻሉን ዘገባው ያሳያል። ከሶሪያ የሚንቀሳቀሰው ሃይል በአየርና በሜዲትሪያን ባሕር ወደሊቢያ የሚገባ ሲሆን፣ ከኢራቅ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪ ሃይል በሲናይ ፔኒንሱላ በኩል እንዲሁም በነዳጅና በሃሺሽ አዟሪዎች እገዛ በሲውዝ ካናል ግብፅ አድርገው ምስራቅ ሊቢያ እየገቡ ነው።

ዴብካ ፋይል እንደሚለው ግብፅ በሊቢያ ላይ ወረራ ለመፈጸም መዘጋጀቷ በአሜሪካ መንግስት የአጀንዳ ቅደም ተከተል ቁጥር አንድ ቦታ መያዙን አስነብቧል። ይህም በመሆኑ የአሜሪካው የሲ.አይ.ኤ. ዳሬክተር ጆን በርናንስ ያለረተጠበቀ ጉብኝት በካይሮ አድርገዋል። ከግብፅ ፕሬዝደንትም ጋር ውይይት መቀመጣቸው ታውቋል። ግብፅ በሊቢያ ላይ ልትከፍተው ላሰበችው ወረራ ማምራሪያ የጠየቁት የሲ.አይ.ኤ.ው ዳይሬክተር ከግብፅ መንግስት ዋስትና ያለው መግለጫ ቀርቦላቸዋል። ይሄውም፣ ፕሬዝደንት ኤል ሲሲ በሰጡት የዋስትና ማረጋገጫ ላይ እንዳሉት የግብፅ ጦር ሰራዊት ሊቢያ ውስጥ ገብቶ የመቆየት ፍላጎት የለውም። ጂሃዲስቱን ካሸነፉና ጦር መሳሪያውንም ካስፈቱት በኋላ በምስራቅ ሊቢያ በሚገኘው ቱብሩክ ከተማ ላለው የሊቢያ ጦር አሳልፈው እንደሚሰጡት አስታውቀዋል። የቱብሩክ ከተማ አስተዳደር የተመሰረተው በሊቢያ የፓርላማ አባሎች ሲሆን፣ ቲሪፖሊ በፅንፈኛ ሃይሎች እጅ በመውደቋ ምክንያት ነበር ወደዚህ ከተማ ሸሽተው የመጡት፡

አሜሪካ ሙሉ ለሙሉ ግብፅ ሊቢያን ለመውረር ያደረገችውን ዝግጀት ባትደግፈውም፣ ፕሬዝደንት ኤል ሲሲ ግን በሀገራቸው ላይ የተደቀነውን የአሸባሪዎች አደጋን ለመዋጋት ቁርጠኛ አቋም መውሰዳቸው ተዘግቧል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41050

Wednesday, April 29, 2015

የወያኔ አፓርታይድ መንግሥት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ ከ100 በላይ ሰዎችን ለመክሰስ ምርመራ ማጠናቀቁን አስታወቀ


ሰማያዊ ፓርቲ መንግሥት ከስም ማጥፋት ዘመቻ ይታቀብ አለ
በኢትዮጵያውያን ላይ የአይኤስ አሸባሪ ቡድን የፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ ለማውገዝ ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በተደረገው ሠልፍ ላይ፣ ሆን ብለው ብጥብጥ ያስነሱትና ሁከት እንዲፈጠር ያደረጉት፣ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና
አባላት መሆናቸውን ማረጋገጡን የፌዴራል ፖሊስ ገልጾ፣ ክስ እንዲመሠረት ለዓቃቤ ሕግ ማስተላለፉን አስታወቀ፡፡ በክሱም የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንና አባላትን ጨምሮ ከ100 በላይ ሰዎች ተካተዋል፡፡
የፌዴራል ፖሊስ ጄኔራል ዳይሬክተር አቶ አሰፋ በዩ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ተዘጋጅተውና ልምምድ አድርገው፣ በንብረትና በሰው ሕይወት ላይ አደጋ ለማድረስ፣ የፖለቲካ እንቅስቃሴንና መላውን ዓለም ያሳዘነውን ሐዘን ሽፋን በማድረግ ሁከት ለመፍጠር ተዘጋጅተው የነበረ ቢሆንም፣ ሊከሽፍ መቻሉን አስረድተዋል፡፡
በወቅቱ ከ1,000 በላይ የሁከቱ ተሳታፊዎች በቁጥጥር ሥር ውለው የነበረ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ዳይሬክተሩ፣ ያለምክንያት በግርግሩ ውስጥ ከመገኘት ባለፈ ምንም ዓይነት ዝግጅትም ሆነ ሌላ ዓላማ የሌላቸውን በመለየት፣ በዕለቱ በየክፍላተ ከተማቸው በተደረገ ማጣራት አብዛኛዎቹ ተለቀው 100 ያህሉ ብቻ ታስረው እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ከተደረገባቸው ተጠርጣሪዎች መካከል ረብሻውን በዋናነት በማቀጣጠል፣ በማደራጀትና በመምራት ከ20 በላይ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በዋነኛነት ተሳትፊ መሆናቸው መረጋገጡን አቶ አሰፋ ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ አባላትም እንዳሉ አክለዋል፡፡
ብጥብጡን ተቀላቅለው ንብረት ለማውደምና በሰው ሕይወት ላይ አደጋ ለማድረስ ተዘጋጅተው የነበሩ አክራሪዎችም እንደነበሩ የገለጹት አቶ አሰፋ፣ በአጠቃላይ ከ100 በላይ በሚሆኑ ሁከትና ብጥብጥ ፈጣሪዎች ላይ ክስ እንዲመሠረት የሚያስችል ምርመራ መጠናቀቁን አስረድተዋል፡፡
በወቅቱ በተከሰተው ብጥብጥና ሁከት በፖሊስ አባላት ላይ በተደረገ የድንጋይ ውርወራ 41 የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ጉዳት እንደደረሰባቸው የጠቆሙት ጄኔራል ዳይሬክተሩ፣ በተለይ አምስት አባላት ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡ ሦስት የሠልፉ ተሳታፊዎችም ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቀዋል፡፡
መንግሥት በፖሊስ በተደረገው ምርመራ የብጥብጡ ዋና ምክንያትና አቀነባባሪ ሰማያዊ ፓርቲ መሆኑ መረጋገጡን ያስታወቀ ቢሆንም፣ ሰማያዊ ፓርቲም በበኩሉ የመንግሥት ፕሮፓጋንዳ በእሱ ላይ በዋናነት ያነጣጠረው ከምርጫው ለማስወጣትና ያለማንም ተቀናቃኝ ለማሸነፍ መሆኑን ገልጿል፡፡
ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በአሸባሪው የአይኤስ ቡድን በሊቢያ በግፍ በተገደሉ ኢትዮጵያውያን ምክንያት በመስቀል አደባባይ የተጠራው ሠልፍ በግጭት እንዲጠናቀቅ ያደረገው ሰማያዊ ፓርቲ ነው ለሚለው ውንጀላ መንግሥትን ወቅሶ ከእንዲህ ዓይነት ስም ማጥፋት ዘመቻው እንዲታቀብም ጠይቋል፡፡
ፓርቲውን ይህን ያስታወቀው ሚያዝያ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡
በዕለቱ መግለጫውን የሰጡት የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ፣ የሕግ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደና የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ እያስፔድ ተስፋዬ ናቸው፡፡
‹‹ማንኛውም ክስተት ከምርጫው ጋር ተያያዘም አልተያያዘም የምርጫ ወቅት እስከሆነ ድረስ፣ ከምርጫው ጋር የሚያገናኛቸው በርካታ ጉዳዮች ይኖራሉ፤›› በማለት ከተቃውሞው ሠልፍ በኋላ የተፈጠረውን ክስተት፣ መንግሥት ፓርቲውን ለማጥቃትና ለማዳከም እየተጠቀመበት እንደሆነ አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡
‹‹ከምርጫው ጋር በቀጥታ የሚያገናኘው ነገር በመኖሩ ፓርቲው ጉዳዩን በሕግ የሚያየው ይሆናል፤›› ያሉት አቶ ዮናታን፣ ፓርቲው ስሜን አጠፉ ያላቸው ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ክስ ለመመሥረት እየተዘጋጀ እንደሆነ አክለው ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የፓርቲው ኃላፊዎች በመግለጫው ወቅት እንዳስታወቁት፣ ሚያዝያ 18 ቀን 2007 ዓ.ም. ምሽት የሁለት ሰዓት ዜና ላይ የፌዴራል ፖሊስ ሰባት ሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና ከ20 በላይ አባላትን ማሰሩን አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ ‹‹ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው፤›› በማለት ተቃውመዋል፡፡
በፌዴራል ፖሊስ የቀረበው የታሰሩ የአባላቱን ቁጥር ከመቃወም ባሻገር፣ ‹‹በአሁኑ ጊዜ በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ቁጥር ስድስት ብቻ ነው፤›› በማለት ፓርቲው አስታውቋል፡፡ ‹‹እነዚህ ስድስት እስረኞች የፓርቲው አባላት እንጂ አመራሮች አይደሉም፡፡ ስለዚህ የረቡዕ ዕለቱን ሠልፍ ተከትሎ ፓርቲው የታሰረበት አንድም አመራር የለም፤›› በማለት ገልጿል፡፡
ፓርቲው ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. አውጥቶት በነበረው መግለጫ ስምንት ያህል አባላቱ መታሰራቸውን መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን፣ በመግለጫው ወቅት በቁጥጥር ሥር ውለው ከነበሩት አባላት መካከል ቀጨኔ አካባቢ ወረዳ 9 ታስሮ የነበሩት አቶ ብሩክ የኔነህ የተባሉ የፓርቲው አባል መለቀቃቸው ተገልጿል፡፡ አቶ ብሩክ ፍርድ ቤት ቀርበው የ12 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸው እንደነበርም እንዲሁ ተገልጿል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከሠልፉ መጀመር ሰዓታት አስቀድሞ አባላቱ መታሰራቸውን የገለጸው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ‹‹በሠልፉ ላይ ለተፈጠሩት ማንኛቸውም ድርጊቶች ፓርቲውን ተጠያቂ ማድረግም በእጅጉ መሠረተ ቢስ ነው፤›› በማለት ተቃውሟል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም፣ ‹‹በፌዴራል ፖሊስና በመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን አማካይነት ተደጋጋሚ የስም ማጥፋት ዘመቻ እየደረሰ ይገኛል፤›› ብሏል፡፡
መንግሥትና የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ከዚህ እኩይ ተግባራቸው የማይታቀቡ ከሆነ፣ የሰማያዊን ስም በሐሰት በማጠልሸት ሥራ ላይ የተሰማሩ የመንግሥት ተቋማትንና ግለሰቦችን በሕግ ፊት ለማቆም ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ ፓርቲው አስታውቋል፡፡
http://satenaw.com/amharic/archives/6593

Saturday, April 25, 2015

በጎማ ዱላው ፌቷን መቷት፣ ወድቃም ደበደቧት – አይ ጭካኔ

አቶ ሬድዋን ሁሴን በቴሌቭዝን ቀርበው፣ በረእቡ ሰልፍ ፖሊስ ምንም አይነት ድብደባ አልፈጸም በማለት በይፋ ተናግሯል። ሆኖም ሰዉዬው የተነገሩት ፍጹም ዉሸት መሆኑን ሁላችንም የምናውቀው ነው። ቪዲዮዎች፣ ፎቶዎች እስከ አፍንጫችን ተበትነው አይተናል።

ታዲያ አንድ የመንግስት ባለስልጣን (ያዉም ሚኒስቴር) በቴሌቭዥን አይን ያወጣ፣ ያፈጠጠ ዉሸት አይሉት የዉሸት ዉሸት፣ በዚህ መልክ ሲናገሩ የዚህን መንግስት ትንሽነትና መበስበስ አይሳይምን ? አንድ ወቅት ኢትዮ ዛጎል የሚባለው ብሎገር ( ሰምናወርቅ) የጻፈው ነገር ታወሰኝ። “They are certified liers” ነበር ያላቸው። ዳቦ ጋጋሪውች ዳቦ እንደሚጋጋሩ፣ ታኪስ ነጂዎች ታክሲ እንደሚነዱ certified liers የሆኑት ደግሞ ስራቸው መዋሸት ነው። እንግዲህ እንደዚህ አይነት ሰዎች ናቸው እየገዙን ያሉት !!!


ልጅ እያለሁ፣ አስታወሳለሁ። አንድ ቀን አንዱ ሴት ሲመታ አይቼው፣ እንዴት ሴት ተመታለህ ብዬ ተደባድቤ ነበር። ሌላ ልጅ ተጨምሮ ልክ ነበር ያገባነው። እህቶቻችንን ፊታቸውን በጎማ ዱላ መምታት. ከወደቁም በኋላ መደብደብ ምን አይነት ጭካኔ ነው ? እንግዲህ የሕወሃይ ኢትዮጵያ ይች ናት !!!

ፍሬሕይወት ትባላልች ። የአዲስ አበባ ነዋሪ ናት።ረእቡ ስለተፈጠረው ሁኔታ፣ ስለደረሰባት ግፍ የሚከተለዉን ጽፋለች:-

ይህ ማስታወሻ የተጻፈው በሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም “መንግስታችን” በጠራው የአይ.ሲ.ስ የአሸባሪ ቡድን በኢትዮጲያውያን ወንድሞቻችን ላይ የፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ ተቃውሞ ሰልፍ ላይ ስለደረሰብኝ ነገር ነው፡፡

በዚሁ ዕለት ከእህቴ ጋር በመሆን የተቃውሞ ተካፋይ ለመሆን ወደ መስቀል አደባባይ ሄደን ነበር…ሆኖም ብዙም ሳንቆይ የነበረው ድባብ ጥሩ ባለመሆኑ ወደ ቤታችን ተመለስን፡፡ ሰልፉ ከተበተነ፤ አካባቢው ጭር ካለ በኋላ ተመልሰን ወጣን፡፡ የነበርነው ደምበል አካባቢ ሲሆን በወጣንበት ሰዓት ምንም አይነት ግርግር የሌለ፤ ምንም አይነት ሩጫ፣ ድንጋይ ውርወራም ሆነ ተቃውሞ አልነበረም፡፡ እኛም ነገሮችን ቃኝተን ወደ ቤታችን በተረጋጋ ሁኔታ በመመለስ ላይ ሳለን፣ በድንገት ከየት እንደመጣ ያላየነው የፌደራል ፖሊስ መኪና አጠገባችን መጥቶ ፣ “ቁሙ” ሲለን ሁላችንም እግሬ አውጪኝ ብለን ለመሸሽ ሞከርን…ዕድል የቀናው ሮጦ አመለጠ፤ እኛ ግን አልቻልንም ነበር፡፡

ከመኪናው ሮጦ የወረደ አንድ ፌደራል ፖሊስ በጎማ ዱላው ፌቴን መትቶኝ ወደቅሁ….ወድቄም ለወንድ ልጅ እንኳ የማይሰነዘር ምትን ደጋግሞ አሳረፈብኝ….በወቅቱ አብሮኝ የነበረ ወንድሜ ሮጦ ያመለጠ ሲሆን እህቴ እና እኔ ተይዘን ጫማችንን እንድናወልቅ ተደርጎ፣ ከደምበል እስከ ስቴዲየም በባዶ እግራችን እንድንሄድ ተደረገ…….በትንሿ ስቴዲየምም አስቀመጡን፡፡ አብረውን ከነበሩት ሰዎች መካከል ሕፃናትን የያዙ እናቶች ነበሩበት፡፡ ይዘውን ለነበሩት የፌደራል ፖሊስ አባሎች ሁኔታውን ልናስረዳ ብንሞክርም…ብናለቅስም እነርሱ የምናወራውን ለመስማትም ሆነ የሰሙትን ለመረዳት የሚችል ጆሮ እና አዕምሮ አልነበራቸውም…..ልጅ የያዙ እናቶች ልጆቻችንን ከትምህርት ቤት አውጥተን እየተመለስን ነው…እኛ ምንም አላደረግንም እባካችሁ ልቀቁን ቢሉ የሰማቸው አልነበረም፡፡

እኔ እና እህቴም “ከቤታችን መውጣታችን ነው….ምንም አላደረግንም። ለምን ተያዝን ?” ብንልም እንኳን ልንግባባ ይቅርና እራሳቸው ደብድበው ያሳበጡትን ፊቴን “ድንጋይ ስትወረውሪ ነው ፊትሽ ያበጠው” በማለት ጭራሽ ወንጅለውኝ ቁጭ አሉ፡፡
በዚህ መሀል እህቴ እራሷን ስታ ወደቀች….እሷን ለማዳን አብረውን የነበሩ ወንዶች ልጆች ይዘዋት ሊወጡ ቢያስቡም “እንዴት ?” በማለት እነርሱን ደብድበው ለእርሷም ምንም አይነት እርዳታ ሳይሰጡ ቀሩ፡፡ ይህ አረመኔ እና ጨካኝ ልባቸው ይራራ እንደሆን በማለት በለቅሶ ብንለምናቸው…ስለ አንድ ሀገር ልጅነታችን…ስለ ኢትዮጲያዊነታችን ብናነሳ….ሰብዓዊነት እንዲሰማቸው ብንለምን ምንም እንዳልተፈጠረ….”አሸባሪዎች ናችሁ” በማለት ለ5 ሰዓታት አሰሩን፡፡



እኛም ከአሁን አሁን ወደ እስር ቤት ተወሰድን ወይም ራርተው ከተማችን ተለያይተን እንድንቀመጥ ተደረገ፡፡ በዛም የየወረዳው የወጣት ሊግ ተብዬዎች መጥተው “አሸባሪውን” ከደጋፊው ለይተው እንዲያወጡ ተጠየቁ….እኛን ያተረፈን አልነበረም…እንደማያውቁን…ከዚህ በፊት ስናሸብር እንደኖርን ተደርገን ሳንመረጥ ቀረን፡፡ በኋላም በሰው ሰው ባለስልጣን ዘመድ ተፈልጎ በዚህ በዚያ ተብሎ ተለቀቅን፡፡ ሀገር አለኝ ብዬ አስብ ነበር አሁን ግን ለአይሲስ ካለኝ ጥላቻ ባልተናነሰ “መንግስታችንን” ጠልቼዋለሁ…. ህሊና የሌላቸው ወታደሮቻችንን ጠልቼአቸዋለሁ፡፡ እኔስ በቤተሰቦቼ ርብርብ ወጣሁ የእነዚያ እናቶች እና ሕፃናት ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን? አሁንም በዚህ ሁኔታ የታሰሩ ወገኖቻችንስ? እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን….ጸሎቴ ከእናንተ ጋር ነው!!! 

ውይ ውይ ኢትዮጲያ…..

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40878

ሕወሓት የሚያስተዳድረው መንግስት በአ.አ ጨርቆስ አካባቢ በርካታ ወጣቶችን አፍሶ ወዳልታወቀ ሥፍራ ወሰደ


አይሲኤል በኢትዮጵያውያኑ የፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ በመቃወም ሰልፍ የወጡት የአዲስ አበባ ሰዎች መካከል በተለይ የጨርቆስ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ወጣቶች ዛሬ በጠዋቱ ሲታፈሱ መዋላቸውን ለዘ-ሐበሻ ከአዲስ አበባ የደረሰው መረጃ ጠቆመ::

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የለውጥ መነሳሳት ስሜትን በሰሞኑ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ የተመለከተው ሕወሓት መራሹ መንግስት በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛል ያሉት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ቀጣዩን የውሸት ምርጫ ካለምንም ኮሽታ ለማሳለፍ ሲል ወጣቶችን በማሸበር ላይ ይገኛል ብለዋል::


ሕወሓት የሚያስተዳድረው መንግስት ዛሬ በጨርቆስ አካባቢ ከአንድ መቶ የማያንሱ ወጣቶችን አፍሶ የወሰደ ሲሆን የት እንደደረሱ ለማረጋገጥ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40863

Thursday, April 23, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታድነው መታሰራቸው ታወቀ • 500 በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ታስረዋል

(ነገረ ኢትዮጵያ) መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰልፈኛው ‹‹መንግስት በዜጎቻችን ላይ ለተፈፀመው አረመኔያዊ እርምጃ በቂ ምላሽ እየሰጠ አይደለም›› በሚል ባሰሙት ተቃውሞ በርካቶች ተደብደበው ከተሳሩና ሰልፉ ካበቃ በኋላ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቸው በሚል በርካቶች እየታደኑ መታሰራቸውን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

ሰልፉ ካበቃ በኋላ ታድነው ከታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መካከል ብሩክ የኔነህ ማታ 12 ሰዓር ላይ የተያዘ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አራዳ መምሪያ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ዜና ከሰልፉ በኋላ ከ500 በላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተይዘው አራት ኪሎ አካባቢ በሚገኘው 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ታስረው እንደሚገኙ ተማሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡


በሌላ በኩል ጠና ይታየው፣ ይድነቃቸው አዲስና እስክንድር ጥላሁን የተባሉት የሰማያዊ ፓርቲው ዕጩዎች ሌሊት 6 ሰዓት ላይ ከአባላት ተለይተው መፈታታቸውን አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40800

Wednesday, April 22, 2015

መንግስት በአ.አ የጠራው ሰልፍ ወደ ተቃውሞ ተለወጠ * ሴቶች እና አዛውንቶችን ሳይቀር ደብደበ * አስለቃሽ ጭስ ተተኮሰ * የሕዝቡ ቁጣ አልበረደም

የአይ ኤስ አይ ኤስን ጭካኔ ለመቃወም ሰልፍ የወጡ ኢትዮጵያውያን አገራቸው ውስጥ ሌላ ጭካኔ ገጥሟቸዋል

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ለፖለቲካ ጥቅም ማግኛ ሲል የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ወደ ተቃውሞ ተለወጠ:: ማንኛውም ሕዝብ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርግ የሚከለከለው ኢሕአዴግ ሕዝብን ወዳጅ መስሎ ቢቀርብም በመስቀል አደባባይ ዳግም ሕዝብን በመደብደብ ዳግም ራሱን ማዋረዱን ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ አመልክቷል::

በዛሬው ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ ሕዝቡ ተቀላቅሎ በመግባት ተቃውሞውን በመንግስት ላይ ያሰማ ሲሆን “እኛን ከምትደበድቡ አይሲስን ደብድቡ” “ወታደር ዳርፉር ከምትልኩ ሊቢያ ላኩ” እያለ ተቃውሞውን አሰምቷል:: “ወኔ የሌለው የሃገር ሸክም ነው” እያለ ተቃውሞውን ያሰማው የአዲስ አበባ ሕዝብ ከደህንነቶች ጋር ግብግብ የገጠመ ሲሆን በዚህም በርካታ ወጣቶች በፌደራል ፖሊሶች ተይዘው መታሰራቸው ታውቋል::


የአዲስ አበባ ኤግዚብሽን ማዕከልን እንደ እስር ቤት በመጠቀም ስርዓቱ በርካታ ወጣቶችን ያሰረ ሲሆን በቆመጥ ሴቶችን እና አዛውንቶችን ሳይለይ ቀጥቅጧል:: አስለቃሽ ጭስ በመጠቀምም ተቃውሞውን ለማብረድ ጥሯል::

በጨርቆስ፣ መስቀል አደባባይ፣ ተክለሃይማኖት እና ሌሎችም አካባቢዎች ተቃውሞው እንደቀጠለ ይገኛል::

በሰልፉ ላይ ንግግር ለማድረግ የመጡት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሊናገሩ ሲሉ ሕዝቡ በጩኸት ተቃውሞውን
‹‹ውሸት ሰለችን ሰለችን!››
‹‹ዋ! ዋ! ዋ!››
‹‹ታርዷል ወገኔ!››
‹‹መንግስት የሌለው እዚህ ብቻ ነው!›› ሲል ተቃውሞን ከመግለጹ በተጨማሪ ጆሮውን በመያዝና ፊቱን በማዞር ቁጣውን ገልጿል ሲል ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመልክቷል::


ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው የመንግስት ፌደራል ፖሊሶች አሁንም በአራቱም አቅጣጫ ህዝቡን እየተከታተለ እየደበደበና እያሰረ ነው፡፡ በርካታ አዛውንቶችና ወጣቶች ራሳቸውን ስተው ወድቀዋል፡፡

ከተበተነው ህዝብ መካከልም ፖሊስ የተቃውሞው መሪ ናቸው በሚል ወጣቶችን እየነጠለ ማሰር ጀምሯል፡፡ በሰልፉ ላይ ተሳታፊ የነበሩት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ዕጩዎች እየታሰሩ መሆኑ የተሰማ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ የሆነው ይድነቃቸው አዲስን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና አባላት ታስረዋል፡፡


በኢትዮጵያውያን ላይ የጭካኔ እርምጃ የወሰደው አይ ኤስ አይ ኤስ ላይ እርምጃ አልወሰድክም፣ ለዜጎች ትኩረት አልሰጠህም በሚል ተቃውሞ የገጠመው መንግስት በኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ ጭካኔ እየፈፀመ መሆኑ የራሱን የስር ዓቱን ደጋፊዎች ሳይቀር አሳዝኗል::


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40745

Sunday, April 19, 2015

ሕወሓት የሚመራው መንግስት በአይሲኤስ የተገደሉ ኢትዮጵያውያንን ካደ * “የተገደሉት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን አላረጋገጥኩም” አለ

ሁሌም በዜጎቹ ጉዳይ ከበዳይ ወገን ጋር አብሮ በመሰለፍ ዜጎቹን የሚያዋርደው የሕወሓት የሚያስተዳድረው የኢሕ አዴግ መንግስት በሊቢያ አይሲኤስ የገደላቸውን 28 ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ማረጋገጫ አላገኘሁም አለ::
ሕወሓት የሚመራው መንግስት ባወጣው መግለጫው “አይሲኤስ የተባለው አለም ዓቀፍ አሸባሪ ቡድን በሊቢያ በሚኖሩ ስደተኞች ላይ ፈፅሜያዋለሁ በሚል በቪዲዮ ያሰራጨው ዘግናኝ የግድያ ተግባር የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚያወግዝ ሲገልጽ” ስደተኛ እንጂ ኢትዮጵያውያን ማለት አልፈቀደም::

ሕወሓት የሚመራው መንግስት ዜጎቹን በመካድ በአቶ ሬድዋን ሁሴን በኩል የሰጠው መግለጫ ላይ እንዲህ ይላል:-
“በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 11 ቀን 2007 ዓመተ ምህረት የተለያዩ አለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ባሰራጩት ዘገባ አይ ኤስ የተባለው አሸባሪ ቡድን ግድያ የፈፀመባቸው ስደተኞች ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ ቢገልፁም በግብፅ ካይሮ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ግን ስደተኞቹ ኢትዮጵያውያን ስለመሆናቸው ማረጋገጫ እንዳልሰጠም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

አሸባሪው ቡድኑ ለህልፈት የዳረጋቸው ዜጎች ኢትዮጵያውያን ቢሆኑም ባይሆኑም መንግስት በንፁሃን ላይ የሚፈፀም ይህን መሰል አፀያፊና ዘግናኝ የሽብር ድርጊት አጥብቆ ይኮንናል ብለዋል፡፡


በግልጽ ኢትዮጵያውያንን የመሰሉ ሰዎች ታርደውና ተገድለው ባህር ላይ ተጥለው መንግስት ገና ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን አላረጋገጥኩም ማለቱ ዜጎቹን በመካድ የታወቀው የሕወሓት መንግስት ዳግም እርቃኑን ቀርቷል:: በቅርቡ እሳዑዲ አረቢያ በየመን እና በደቡብ አፍሪካ በዜጎቹ ላይ ክህደት የፈጸመው ይኸው አምባገነን መንግስት በሊቢያ የሚገኙ ዜጎቹን መካዱ ብዙዎችን አሳዝኗል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40631

Friday, April 17, 2015

በደቡብ አፍሪካ እየተፈጸመ ያለውን ስደተኞችን የማጥቃትና ማሳድድ ወንጀል በመቃወም ሰልፈኞች ድምጻቸውን ሲያሰሙ ዋሉ


 በደቡብ አፍሪካ የውጪ ሀገር ዜጎች ላይ የተፈጸመው ጥቃት ያስቆጣቸው በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን ደርጊቱን ለማውገዝ በደርባን ታላቅ ሰልፍ ማድረጋቸውን የአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን እና የውጭ አገር ዜጎች በሰልፉ ላይ ተገኝተዋል። “የውጪ ሀገር ዜጎችን ማጥቃትና ማሳድድ ይቁም!” የሚል መፈክር ያነገቡት የደርባን ነዋሪዎች፤ በጥቃት ፈጻሚዎቹ ላይ ተቃውሟቸውንና ቁጣቸውን ገልጸዋል።

ሰልፈኞቹ ትናንት በደርባን የተፈጸመውን ድርጊት ከማውገዝ ባሻገር ለውጪ ሀገር ዜጎች ያላቸውን አጋርነት በይፋ አረጋግጠዋል።.

ሰሞኑን በደርባን በተፈጸመው ጥቃት በትንሹ 5 ሰዎች መገደላቸውንና የበርካታ ሰዎች ሱቆች መዘረፋቸውን ቢቢሲ አመልክቷል። ከሟቾቹ ውስጥ ሶስቱ ኢትዮጵያውያን ናቸው።


በደርባን የሚገኙ ኢትዮጵያኖች ራሳቸውን ከጥቃት ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰዱ ነው። በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ወኪል ወደ ደርባን በማቅናት ኢትዮጵያውያኑን ማነጋገሩን የደሰረን መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያውያን በወገኖቻቸው ላይ የደረሰውን ጥቃት የማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም እያወገዙት ነው።

በደርባን የተፈጸመው እርምጃ በጆሃንስበርግም ይደገማል የሚል የስልክ መልእክት ተላልፎአል በሚል፣ በከተማዋ የሚገኙ የውጭ አገር ነዋሪዎች ሱቆች ተዘግተው አርፍደዋል።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2008 ዓመተ ምህረት በውጪ ሀገር ዜጎች ላይ በተፈጸመ ተመሳሳይ ጥቃት 62 ሰዎች እንደተገደሉ መዘገብቡ አይዘነጋም።

የዙሉ ንጉስ የውጪ ሀገር ሰዎች ሻንጣቸውን ሸክፈው ወደሀገራቸው መሄድ አለባቸው በማለት ያደረጉት ንግግር ለጥቃቱ መጀመርና መባባስ ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ተመልክቷል። እርሳቸው ግን ለችግሩ ተጠያቂ አይደለሁም በማለት አስተባብለዋል።

ጥቃቱ መፈጸሙን ተከትሎ ማላዊ ዜጎቿን ከደቡብ አፍሪካ በማውጣት ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን፤ ዚምባቡዌም ድርጊቱን በይፋ በማውገዝ በውጪ ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እንዲቆም ጠይቃለች።



http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40558

Related Posts:

Thursday, April 16, 2015

በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት እና የአየር ሃይል የበረራ አስተማሪዎች ታሰሩ

ሚያዝያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሰሞኑን ከፍተኛ የደህንነት ሃላፊዎች  ያስተላለፉትን ድንገተኛ ትእዛዝ ተከትሎ በፌደራል ፖሊስ አባላት የእጅ ስልኮችና የኢሜል አካውንቶች ላይ በተደረገ ፍተሻ፣ የተቃዋሚ መሪ ፎቶዎችን፣ አገራዊ ሙዚቃዎችንና ማንኛውም ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ጽሁፎች ከኢንተርኔት አውርደው በስልካቸው ላይ ያስቀመጡ ፖሊሶች ተይዘው የተወሰኑት ማእከላዊ ሲገቡ፣ የተወሰኑት ደግሞ ጃንሜዳ አካባቢ በሚገኝ እስር ቤት መታሰራቸውን የፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል።

በድንገት የተደረገውን ፍተሻ ተከትሎ በአጠቃላይ ከ120 ያላነሱ ፌደራል ፖሊስ አባላት ሲታሰሩ፣ በፍተሻው በቀጥታ የተቃዋሚ መሪዎች ፎቶዎች ወይም ፖለቲካ ነክ የያዙ ጽሁፎች የተገኙባቸው 37 የሚሆኑ ፖሊሶች ማእከላዊ ተወስደው ታስረዋል።

ከ80 በላይ የሚሆኑት ደግሞ አጠራጣሪ የሆኑ ጉዳዮች አሉ በሚል ለተጨማሪ ምርመራ ጃን ሜዳ አካባቢ በሚገኝ ማቆያ እንዲታሰሩ ተደርጓል።

የፌደራል ፖሊስ አዛዦች የሚሰጡትን ትእዛዝ ላለመቀበል ያንገራግራሉ ተብለው አስቀድመው በተለዩ ፖሊሶች ላይ ደግሞ ክትትሉ መጨመሩን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በዚህም መሰረት በአርማጭሆና ሰሜን ጎንደር የጸረ ሽብር ግብረሃይል ሃላፊዎች የሆኑት ኢንስፔክተር ስንታየሁ፣ ሳጅን አበበ እና ም/ል ሳጅን ብርሃኑ ተይዘው ወደ ማእከላዊ ተወስደዋል።

በእስር ላይ የሚገኙት የግንቦት7 ዋና ጻሃፊ የአቶ አንዳርጋቸውን ፎቶ ግራፍ በብዙ ወታደሮች ሞባይል ስልኮች ላይ መገኘቱን ምንጮች አክለው ገልጸዋል።

ከድምጻውያን ደግሞ የቴዲ አፍሮ፣ የብርሃኑ ተዘራና የፋሲል ደሞዝ ሙዚቃዎችን ከኢንተርኔት አውርዶ ማዳመጥ ኢህአዴግን እንደመክዳት እያስቆጠረ ነው ተብሏል።

በተመሳሳይ ዜና  ድሬዳዋ ውስጥ በበረራ አስተማሪነት ይሰሩ የነበሩ ሁለት መኮንኖች ሰሞኑን ተይዘው ማእከላዊ መታሰራቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ስማቸውን እስካሁን ለማወቅ ባይቻልም፣ አብራሪዎቹ ቀድም ብሎ ከታሰሩት 4 አብራሪዎች ጋር ግንኙነት ነበራችሁ ተብለው መታሰራቸው ታውቋል።

የኤም 35 ተዋጊ ሄሊኮፕተር የበረራ አስተማሪ የነበረው የሻለቃ አክሊሉ መዘነ ወንድም ሰይፉ መዘነም ማእከላዊ ታስሮ በመሰቃየት ላይ ነው። የቀድሞው አንድነት ፓርቲ የአመራር አባል የነበረው መሳይ ትኩም ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰበት ነው።

ገዢው ፓርቲ በደህንት ተቋማት ላይ ያለው ጥርጣሬ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍ እያለ መምጣቱን የሚናገሩት ምንጮች፣ ተጨማሪ ፍተሻዎች፣ ድንገተኛ ግምገማዎችና እስሮች ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገልጻሉ።

የጥርጣሬው መነሻ ምን እንደሆነ በውል ለማወቅ አልተቻለም። ይሁን እንጅ ስራቸውን እየለቀቁ የሚጠፉ የፌደራል ፖሊሶች ቁጥር መጨመር ስርአቱን ስጋት ላይ ሳይጥለው እንደማይቀር ምንጮች  ይገልጻሉ።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40538

Tuesday, April 14, 2015

8 የፖለቲካ ፓርቲዎች ራሳቸውን ከምርጫው ሊያገሉ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ (መግለጫውን ይዘናል)

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በወላይታ ዞን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎችን ያቀረቡ 8 የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዞኑ እየደረሰባቸው የሚገኘው አፈና እና በደል መፍትሄ ካልተሰጠው ራሳቸውን ከመጭው ግንቦት 2007 ዓ.ም ምርጫ ራሳቸውን ሊያገሉ እንደሚችሉ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለዞኑ ምርጫ ማስተባበሪያ፣ ለምርጫ ቦርድና ሌሎች የመንግስት ተቋማት ባስገቡት ደብዳቤ አስጠንቅቀዋል፡፡

ከመጭው ምርጫ ራሳቸውን ሊያገልሉ እንደሚችሉ ያስጠነቀቁት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰማያዊ፣ የኢትዮጵያ ፍትሕና ዴሞክራሲ ሃይሎች ግንባር (ኢፍዴሃግ)፣ የወላይታ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ወሕዴግ)፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ (አትፓ)፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ናቸው፡፡


ማስጠንቀቂያውን ያቀረቡት ፓርቲዎች ለምርጫ ምቹ የሆነ አጋጣሚ እንዳለ በሚዲያ የሚገለፀው ትክክል እንዳልሆነ፣ ያለ ገደብ መብት የሰጠው ገዥው ፓርቲ ሰሆን በእነሱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ጫና እና በደል እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል፡፡ ፓርቲዎቹ አክለውም ምህዳሩ እጅግ የጠበበ መሆኑን በየጊዜው አቤቱታቸውን ለምርጫ ክልሎችና ለጋራ ምክርቤት ቢያቀርቡም ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኙና በአባላቶቻቸው ላይ የሚፈፀመው በደል ከአቅማቸው በላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

‹‹የወረዳና የዞን የምርጫ አስተባባሪዎች የገዥውን ፓርቲ ድምጽ ከመስማት በስተቀር ምንም አይነት ውሳኔ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡›› ያሉት ፓርቲዎች በዚህም ምክንያት ምህዳሩ እጅግ መጥበቡንና ከችግር ላይ ችግር እየተደራረበ በመምጣቱ ከፍተኛ አደጋ ላይ መሆናቸውን በደብዳቤው ገልጸዋል፡፡

ፓርቲዎቹ ለጠቅላይ ሚኒስትር፣ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለደቡብ ክልል ምርጫ ቦርድና ሌሎችም አገራቀፍና የክልሉ ተቋማት በላኩት ደብዳቤ:-

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40524

Saturday, April 11, 2015

በሰሜን ጎንደር የጦር መሳሪያ ሽያጭ መጧጧፉ ተሰማ


በሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኙ ወረዳዎች የጦር መሳሪያ ሽያጭ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጧጡፎ በመሸጥ ላይ መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል።

በአለፋ ፣ ጣቁሳ፣ መተማ፣ አርማጭሆ፣ ቋራና በሌሎችም በርካታ ወረዳዎች አንድ ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከ45 ሺ እስከ 60 ሺ ብር በመሸጥ ላይ ነው። የጦር መሳሪያዎችን በብዛት የሚገዙት አርሶ አደሮች ናቸው።

በርካታ ቁጥር ያለው የኢህአዴግ ወታደር በጠረፍ ከተሞች ውስጥ ከሰፈረ በሁዋላ የጦር መሳሪያ ሽያጩ መድራቱን ነዋሪዎች ይናገራሉ። በቅርቡ በአርማጭሆ የታየው አለመረጋጋት ነዋሪዎች የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን እንዲገዙ ሳያስገድዳቸው እንደማይቀር አስተያየት ሰጪዎች ይገልጻሉ።

የኢህአዴግ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተከታታይ የጦርነት ልምምድ በማድረግ ላይ መሆናቸውን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

መንግስት ሰሞኑን የክልሉ ነዋሪዎች የጦር መሳሪያዎቻቸውን አስመዝገበው ህጋዊ ፈቃድ እንዲይዙ መመሪያ አውጥቶ አንዳንድ ነዋሪዎች መሳሪያዎቻቸውን ሲያስመዘግቡ ታይቷል።

በሻውራ ከተማ ከሰፈሩት የፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል አንድ ጌጡ የተባለ ፖሊስ የኦነግ አባል ነህ ተብሎ በመጠርጠሩ ታስሮ ወደ አዲስ አበባ ተወስዷል።

ምንጭ  – ኢሳት ዜና

http://satenaw.com/amharic/archives/6168

Friday, April 10, 2015

በወልቃይት ወረዳ የፌደራል ፖሊሶች ባደረሱት ድብደባ የአንድ ሰው ሕይወት ጠፋ ከሁመራ እስከ ትክል ድንጋይ ወታደሮች ሴት እህቶቻችን ላይ ወሲባዊ ጥቃት ይፈጽማሉ

በትግራይ ምእራባዊ ዞን ወልቃይት ወረዳ ማይ ገባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ በአካባቢው የሚገኙትን እለታዊ ስራቸውን በሚያከናውኑ ንፁኃን ሰዎች ላይ የተቃዋሚ ድርጅት ተላላኪዎች ናችሁ በማለት በደል እያደርሱባቸው እንደሚገኙ ተገለፀ ሲል ደህሚት አስታወቀ::

በምንጮቹን ጠቅሶ ደህሚት እንደዘገበው በወልቃይት ወረዳ ማይ ገባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የስርአቱ ፌደራል ፖሊስ አባላት ሰርተው ኑሮአቸውን የሚመሩ ዜጎቻችንን የትጥቅ ትግል ለሚያካሂዱ ድርጅቶች የተላካችሁ ናችሁ፤ በረሃ ላይ የደበቃችሁትን መሳሪያም አስረክቡን በማለት መጋቢት 1/2007 ዓ/ም በርካታ ንፁሃን ወገኖች በገመድ አስረው እየደበደቧቸው መዋላቸውን ለማወቅ ተችሏል::

መረጃው ጨምሮ እንዳስረዳው ምንም አይነት ወንጀል ሳይኖራቸው ባስከፊ ሁኔታ እየተደበደቡ የዋሉት በርካታ ወገኖች ቢሆኑም በተለይ ወርቅ ለቀማ ላይ የነበሩትን 6 ሰዎች በአስከፊ ሁኔታ ተደብድበው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ከተደበደቡት ውስጥም የአስገደ ፅንብላ ተወላጅ የሆነው ሓዱሽ ታፈር የተባለ ንፁህ ወገን ወድያውኑ መሞቱን መረጃው አክሎ አስረድቷል::

በሌላ ዜና ከሁመራ እስከ ትክል ድንጋይ ድረስ ያሉት የስርዓቱ ወታደሮች ህዝቡን እያንገላቱት መሆናቸውን ምንጮች አስታወቁ ሲል ደህሚት ዘግቧል::


በመረጃው መሰረት ከተለያዩ ክፍሎች የተውጣጡ አዲስ ወታደሮች ከሁመራ ጀምረው እስከ ትክል ድንጋይና ሌሎች አካባቢዎች ሰፍረው እንደሚገኙና በተለይ በትግራይ ምእራባዊ ዞን ህዝቡ ከቦታ ወደ ቦታ ተንቀሳቅሶ እለታዊ ኑሮውን እንዳይመራ እንቅፋት ሁኖው እንደሚገኙ ተገለፀ::

መረጃው በማስከተል እነዚህ ከስነ ምግባር ውጭ የሆኑ ወታደሮች በሴት እህቶቻችን ላይ ወሲባዊ አመፅ እየፈፀሙ ስለሚገኙ። በኤች አይ ቪ ኤዲስና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች እየተጠቁ በመሆናቸው ምክንያት ወላጅ የሌላቸውን ልጆች ለማሳደግም በመገደዳቸው ምክኒያት ነዋሪው ህዝብም ድርግቱ መፍትሄ እንዲደረግለት በማለት ወደ ሚመለከታቸው አካላት ያቀረበውን ጥያቄ እስካሁን መፍትሄ እንዳላገኘበት ለማወቅ ተችሏል::


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40419

Thursday, April 9, 2015

ኢትዮጵያዊቷ አይሁድ በእስራኤል የሰፈነውን ዘረኝነት እዋጋለሁ አሉ

በእስራኤል ፓርላማ ሲገቡ የመጀመሪዋ ሴት ትውልደ ኢትዮጵዊት አይሁድ የሆኑት የሽአዲስ ታመኑ ሽታ ዘረኝነትን እንደሚዋጉ ተናገሩ፡፡
ሴትየዋ ባገባደድነው ወር በእስራኤል ተካሂዶ በነበረው የፓርላማ ምርጫ በጥቂት ድምጾች ተሸንፈው ከፓርላማ እንደራሴነት ውጪ ቢሆኑም እንኳን ዘረኝነትን በየትም ቦታ ሆነው ለመዋጋት ነው ቃል የገቡት፡፡

የምሰራው ብዙ ስራ አለኝ ያሉት ወይዘሮዋ “የኔና የወገኖቼ የፊት ገጽ በዘረኝነት ወላፈን በሚገረፍበት ሀገር ውስጥ መኖር አልችልም” በማለት ነበር በፓርላማም ሆነ ከፓርላማ ውጪ ይህን አስከፊ ችግር ለመዋጋት እንደቆረጡ የተናገሩት፡፡

በእስራኤል ያሉ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አይሁዶች ከሀገሪቱ ህዝብ 1.5 በመቶ ብቻ የሚሸፍኑ ቢሆኑም በወታደራዊ አገልግሎትም ሆነ በበርካታ መንገዶች የዘር መድሎና መገለል እንደሚደርስባቸው ይነገራል፡፡ የሀገሪቱ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለኤችአይቪ ተጋላጭ ከሆኑ ማህበረሰቦች የደም ልገሳ አልቀበልም በሚል ትውልደ ኢትዮጵያውኑን አይሁዶች የደም ልገሳ ከልክሏል፡፡

ራሳቸው ወ/ሮ የሽአዲስ ታመኑ ሽታንም በቅርብ ጊዜያት የፓርላማ አባላት ደም ሲለግሱ እሳቸው እንዳይለግሱ ተከልክለው የነበረበት ሁኔታ ትልቅ ውዝግብ አስነስቶም ነበር፡፡

በሌላም በኩል በቅርብ ጊዜ የወጡ ዜናዎች የእስራኤል መንግስት ለትውልደ ኢትዮጵያዊያኑ ቁጥራቸውን ለመቀነስ በሚል የወሊድ መከላከያ ያለፈቃዳቸው ሲያስውጣቸው እንደከረመ ይፋ አድርገዋል፡፡


ይህንና ሌሎች አይን ያወጡ የዘር መድሎና ጥላቻ የመዋጋጥ ጥረቱ ታዲያ ለሴትየዋ ይሳካ ይሆንን? ጊዜ የሚመልሰው ነው የሚሆነው፡፡
http://satenaw.com/amharic/archives/6134

Ethiopia Bloggers Evidence Doesn’t Back Charges, Lawyer Says

April 9, 2015
by William Davison
Ethiopian prosecutors have failed to present evidence relating to charges that a group of bloggers and journalists support terrorism, a defense lawyer at the latest court hearing said.
Six members of the Zone 9 blogging group and three freelance journalists were charged in July at the Federal High Court in Ethiopia’s capital, Addis Ababa, for working with banned organizations such as the U.S.-based Ginbot 7, which the Horn of Africa nation categorizes as a terrorist group. A witness on Wednesday testified that police last year collected a political manifesto from a Health Ministry office, where one of the defendants worked, lawyer Ameha Mekonnen said.
“No witness is brought who has either direct or indirect knowledge of the material element of the charge,” Ameha said in an interview. “The witnesses are here to prove that there was no maltreatment or pressure when the search was conducted.”
The defendants are the latest government critics to be tried under Ethiopia’s 2009 anti-terrorism law, which the U.S.
has said is being used to criminalize legitimate dissent. Ethiopian officials reject the accusation.
The manifesto collected was for a “peaceful” political party led by the author Lencho Lata, a former head of the rebel Oromo Liberation Front, Ameha said. All of the other evidence filed to the court by prosecutors is of a similar public nature, he said.
Prosecutors will get a final chance to present witnesses when the trial resumes on May 26, Ameha said.
Source: Bloomberg
http://ecadforum.com/2015/04/09/ethiopia-bloggers-evidence-doesnt-back-charges-lawyer-says/

Wednesday, April 8, 2015

በ24ኛው ክፍለጦር ውስጥ የሚገኙ ወታደሮች ትጥቃቸውን እየሸጡ በመጥፋት ላይ ናቸው ተባለ •

ትህዲኤን እንደዘገበው በምዕራብ እዝ በ24ኛ ክ/ጦር ውስጥ የሚገኙ የገዢው ኢህአዴግ ጉጅሌ ወታደሮች በየወቅቱ መሳሪያቸውንና ትጥቃቸውን እየሸጡ በመጥፋት ላይ እንዳሉ ተገለፀ::
(ፎቶ ከፋይል)


ትህዴን ከክፍለጦሩ ውስጥ ባገኘነው መረጃ መሰረት ሲል በዘገበው ዘገባው በምዕራብ እዝ 24ኛ ክ/ጦር የገዢው ኢህአደግ ጉጅሌ የሰራዊት አባላት በሚቀጠሩበት ወቅት በስርአቱ የሚገባላቸው ቃል ሰለማይተገበር ካላቸው የማህበራዊ ችግር የተነሳ መሳሪያዎቻቸውንና ትጥቃቸውን እየሸጡ በመጥፋት ላይ እንደሚገኙ ከገለፀ በኋላ። በተለይ ደግሞ የክፍለ ጦሩ አባላት 2ኛ ረጅመንት የሆኑት ሁለት ወታደሮች መጋቢት 20/ 2007 ዓ/ም ክፍላቸውን ትተው ዳንሻ አልፈው በጎንደር መንገድ በመሄድ ላይ እያሉ ለሲቪሉ ማህበረሰብ መሳሪያቸውንና ትጥቃቸውን ግዙን መሳፈሪያ አጥተናል እንዳሏቸው ሊታወቅ ተችሏል::

መረጃው በማከል እንዳስረዳው የክፍለ ጦሩ አዛዦች ለሰራዊቱ የማህበራዊ አገልግሎት ተብሎ የመጣውን ገንዘብ። ከታች እስከ ላይ ተሳስረው ለግል ጥቅማቸው እያዋሉት መሆናቸውን በሰራዊቱ ተገምግሞ ሲያበቃ። እስከ አሁን ድረስ ግን የተተገበረ ለውጥ እንደሌለ መረጃው ጨምሮ አስረድቷል ሲል ትህዴን ዘግቧል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40389

የአንዳርጋቸውን የትግል መንገድ ሚሊዮኖች ይከተላሉ። – ሳሙኤል አሊ (ከኖርዌይ)

ወደ በረሃ ወርዶ የሰራውን ስራ በፎቶዎቹ  እያየው ነው እነዚህን ፎቶዎችን ሳይ አይኔ በእንባ ይሞላሉ ልቤ በእልህ ይቀጣጠላል የተዘበራረቀ ስሜት ወደ ውስጤ ሲገባ ይታወቀኛል የደስታ ስሜት፣ የእልህ ስሜት፣ የቆራጥነት ስሜት፣ የጽናት ስሜት፣ የእውነተኝነት ስሜት ብቻ ምን ልበላቹህ ተደበላልቀው ውስጤን ይወጥሩታል እናም ፎቶዎቹን ሳያቸው የሚያወሩኝ ያህል ደስታን ይሰጡኛል 

አንድ ቀን ታድያ አንድ የጎረቤት አገር ሰው ሁል ጌዜ በተደጋጋሚ ጌዜ  የዚህን ሰውዬ ፎቶዎች  ተመስጠህ ታየዋለህ ለምንድነው አለኝ 

የኔም መልስ አይ ደስ ስለሚለኝ ነው አልኩት። እርሱም መልሶ ጥያቄወችን ይጠይቀኝ ጀመር አባትህ ነው? ዘመድህ ነው? ገበሬ ነው? ወዛደር ነው? ወታደር ነው? ምንድ ነው? ንገረኝ ደጋግመህ  ስታየው አባትህ ከሆነ  ብዬ ነው አልያም ዘመድህ  ደግሞ ይሄኘው   ፎቶ ገበሬ ደግሜ  ያኛው  ወዛደር ይሄኛው ደግሞ ወታደር ይመስላል ማን ነው ንገረኝ አለኝ እኔም ስመልስለት ልክ ብለሃል  እንደአባቴ የማየው አባት ያውም የኔ ብቻ ሳይሆን ነጻነት ለተጠሙ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አባት ነው።  ከገበሬም ገበሬ ነው ስለገበሬው ነጻነት የሚታገል የገበሬው ወዳጅ ነው። ከወዛደርም ወዛደር ነው ድንጋይ እየተሸከመ እንጨት እየፈለጠ ወዛደሩን ለማሳደግ የሚተጋ የፍቅር አባት ነው። ከወታደርም ወታደር ነው ወዳጅን ሳይሆን ጠላትን በህዝብ አናት ላይ ቁጭ ብሎ በብረት ረግጦ የነገሰና የሚገዛን አገር አፍራሽ ለመገርሰስ ወታደር ሆኖ ለአገሩ ነጻነት ዘብ የቆመ  ብርቅዬና ውድ የኢትዮጵያ ወታደር ነው  ብዬ ገለጽኩለት። ስሙም አንዳርጋቸው ጽጌ  ይባላል  ስምን መለአክ ያወጣዋል ይባላል እውነት ነው ስምና ተግባርን አዋህዶ  የያዘ  የዘመኑ የኢትዮጵያ ብርቅዬ ልጅ ነው።

አንድ አርጋቸው ማለት የተራራቀን ማቀራረብ፣ የተለያየን ማገናኘት፣ ያልጸናን ማጽናት፣ የሚለውን ትርጉም ሲሰጠን። ጽጌ ማለት ደግሞ አበባ ማለት ነው። ሲተረጉም  የአንድነት አበባ እንደውም  የትም የማይበቅለው ኢትዮ ጵያዊ አበባ የእግዛአብሔር ጸጋ የሚያበቅለው አደይ አበባችን ነው።

ታድያ ይህንን የኢትዮጵያ የሰላም ባንዲራ፣ የነጻነት መዝሙር፣ የፍቅር ቅኔ፣ የእውነት ታጋይ፣ የሆነውን ድንቅዬ መከታችንን  ከአመት በፊት የመኖች ሚልዮን ዶላሮችን ተቀብለው ለአገር አጥፊው እና ለአረመኔው ወያኔ አሳልፋ የሰጠችው አንዳርጋቸው ሰለ ኢትዮጵያ ነጻነት የታገለ  ታጋያችንን የመን አሳጣችን። በአሁኑ ሰዓት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያን የድረሱልኝ ጥሪ እያሰሙ ይገኛሉ። ወያኔ ግን ይሄን የወገን  ጥሪ የሚሰማበት ጆሮ አልፈጠረበትም። የዜጋቸው ደህንነት ያሳሰባቸውና ያስጨነቃቸው አገሮች ነገሩ ሳይብስ በጊዜው ዜጎቻቸውን አስወጥተዋል። ከ45 በላይ ኢትዮጵያን ግን የሚደርስላቸው አጥተው በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ አርበኛውን አንዳርጋቸው አፍኖ ለማምጣት የመን ድረስ አምርቶ  የነበረው ቦይንግ ዛሬ የጥይት ናዳ እየወረደባቸው ላለው ዜጎቻችን መድረስ አልቻለም።  አንዳርጋቸውን ለማሳፈኛ ለየመን ያወጡት በሚልዮን የሚቆጠር  ዶላር የዜጎቻችንን ነፍስ ለማዳን ሳይችሉ ቀርተዋል።  ይልቅ ለነሱ የወገን ድረሱልኝ ጥሪ ከወደ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር በፌስ ቡክ መስኮት የተናገሩት ቢኖር ስልክ ቁጥር ነው። እንዴት አሳፋሪ ነገር እየሰሩ እናዳለ የሁል ግዜ ተግባራቸውን በድጋሚ አሳይተውናል።  እኔን ያሳዘነኝ ነገር የራሷን የቤት ስራ ሳትሰራ፣ የራሷን የውስጥ መረጋጋት ሳታመጣ፣ ሰለራሳ ሕዝብ ሳትጨነቅ፣ የኢትዮጵያን እውነተኛ ታጋይ አሳልፋ  መስጠትዋ <<የራስዋ አሮባት የሰው ታማስላለች>>  የሚለውን አባባል ያስታውሰኛል ቢሆንም ግን  የመን ለሰራችው ስራ ልትጠየቅ ይገባል።


አንዳርጋቸው በኢትዮጵያን ልቦና ውስጥ የፈጠረው የአንድነት መንፈስ ወያኔን የማስወገድ  ሃላፊነትን ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን መንገድ ያሳየ  በመሆኑ  እኛ ልጆችህ ያሰብከውን ዲሞክራስያዊት አገር የማየት ህልምህን እውን ለማድረግ በአንድ አንዳርጋቸው ምትክ ሚልዮኖች ተተክተው ወደትግሉ ጎራ ገብተናል። ገዳያችንን ልናጠፋ፣  አንባገነኖችን ልንገረስስ፣ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ  ቆርጠን ተነስተናል። እናም የተደወለው ደውል  የክተት ነውና  ሁሉም በያለበት  ወያኔ የተባለውን ሰው በላ አውሬ  ከኢትዮጵያ  ምድር እስከ መጨረሻው ለመደምሰስ እና ጨርሶ እንዳያንሰራራ አድርጎ የማስወገድ ደውል ነውና  ሁላችንም ለዚህ ክተት ጥሪ ተሳታፊ ሆነን ትግሉን እንቀላቀል።  የነጻነት ታጋይ የአንዳርጋቸው ጽጌ ልጆች እንዳለን ዛሬ የምናሳይበት ጊዜ  ነውና ገዳያችንን ገለን፣ አሳዳጃችንን አሳደን፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በስደት ከተበታተንበት ተሰባስበን በደስታና በሰላም የምንኖርባት  ዲሞክራሳዊት አገር እንዲኖረን ክተቱን ተቀብለን ነጻነታችንን እናመጣለን።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40372

Tuesday, April 7, 2015

በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን የማውጣት እንቅስቃሴ አልተጀመረም

በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በየመን የሚካሄደውን የእርስ በርስ ጦርነት ተጋፍጠው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ቢሆንም፣ ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉትን ከ2 ሺ ያላነሱ ፈቃደኛ ኢትዮጵያውያንንን ለመመለስ እንቅስቃሴ እየታየ አይደለም ሲሉ የመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያውያኑ ኢምባሲው ባቀረበው ጥሪ መሰረት ምዝገባ አካሄዱ ቢሆንም ፣ መቼና እንዴት እንደሚሄዱ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።


አንዳንድ አገራት የባህር እና የአየር ሃይላቸውን በመላክ ዜጎቻቸውን ቢያወጡም ፣ በኢትዮጵያ በኩል ስለሚደረገው እንቅስቃሴ መንግስት አስቸጋሪ ነው ከማለት በስተቀር መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።

ሱዳን ዜጎቿን በአየር ለማውጣት ያደረገችው ሙከራ ከሰአነ መሪዎች የማረፍ ፈቃድ በመከልከሉዋ ሳይሳካላት ቀርቷል ሱዳን ከሳውድ አረቢያ ጎን በመቆም በሃውዚ አማጽያን ላይ የሚደረገውን የአየር ድብደባ ከሚደግፉት አገራት መካከል ናት ፓኪስታን ዜጎቿን በአየር 
ማስወጣት የቻለች ሲሆን፣ ግብጽ፣ ቻይና፣ ሩሲያና በርካታ አገራት ዜጎቻቸውን በተሳካ ሁኔታ እያወጡ ነው። አልጀሪያና ህንድ ደግሞ ዜጎቻቸውን በሙሉ ማውጣታቸው ታውቋል 

የኢህአዴግ መንግስት በሳውድ አረብያ የሚመራውን የአየር ድብደባ ደግፎ መግለጫ መስጠቱ ይታወቃል ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ ከስልጣን የተባረሩት ፕ/ት ሃዲ ተመልሰው ወደ ስልጣን እንዲመጡ እንደምትፈልግና ከሱዳንና ጁቡቲ ጋር 
በመሆን ስለምትወስደው ቀጣይ እርምጃ እንደምትመክር ተናግረዋል የአቶ ሃይለማርያም መግለጫ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ በየመን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላል በሚል ተተችቶአል።

ጦራቸውን ከአማጽያን ጎን ያሰለፉት እና የሃውዚ ሚሊሺያዎችን የሚደግፉት የቀድሞው ፕሬዚዳንት አሊ አብዱላ ሳላህ ኢትዮጵያ ውስጥ በጥገኝነት ይኖራሉ። ሳላህ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ በሳውዲ የሚመራው የአየር ድብደባ ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል።
ኢህአዴግ በሳላህ ላይ ያለው አቋም ግልጽ አይደለም 
በሌላ በኩል ደግሞ የኢህአዴግ ደጋፊ የሆነቸው ቻይና በሳውዲ መሪነት የሚወሰደውን እርምጃ እየተቃወመች ነው።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40348

Monday, April 6, 2015

የገዢው መንግስት በባህር ዳር ከተማ ያደረጋቸው የምረጡኝ ስብሰባዎች ውጤት አልባ መሆናቸው ተነገረ

 በባህር ዳር ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተማዎችና ሙሉዓለም አዳራሽ የተደረገው ስብሰባ የተፈለገውን ግብ ሳይመታ መጠናቀቁን የስብሰባው ተሳታፊዎች ተናገሩ፡፡

ቅዳሜ መጋቢት 26/2007 ዓ.ም በተደረገው ስብሰባ የብአዴን አባላትን በጥሪ ወረቀት የከተማ ነዋሪዎችን ቤት ለቤት በመዞር በስብሰባው እንዲገኙ በመመዝገብና የተለመደውን ማስፈራሪያ በመጠቀም እስከ ቀኑ 6 ሰዓት በተደረገው ስብሰባ ተሳታፊዎች የተለያዩ
ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን በመስጠት የገዢውን መንግስት ካድሬዎች ሲያሸማቅቁ መዋላቸውን ተሳታፊዎች ለዘጋቢያችን ገልጸዋል፡፡

ያለፈውን አምስት ዓመት “ የህዝቡ ችግር ምንድን ነው? ” በማለት ሰብስባችሁ ሳታነጋግሩን ዛሬ የምርጫ ወቅት ሲደርስ በመሰብሰብ መልካም ሰርተናል ለምን ትላላችሁ?

ከምርጫ ቀን በኋላ የምትገቡትን ቃል ሁሉ በመርሳት ከጥቃቅን አገልግሎቶች ጀምሮ ህዝቡን በመልካም አስተዳደር እጦት ማሰቃየት እንደ ልማድ አድርጋችሁ የምትሰሩበት አካሄድ ሆኖ እያለ፤ ዛሬ ለምርጫ ሲባል ራሳችሁን እንደ ቅዱስ አድርጋችሁ ለምን ታቀርባላችሁ?

የገዢው መንግስት ስራውን በአግባቡ አለመስራቱን በተለያየ የአፈጻጸም ስራዎች ታይቷል፡፡ ህዝቡ በኑሮ ውድነት እየተሰቃየ ባለበት ወቅት በዘይትና ስኳር ሰበብ ህዝቡን ከአንድ አመት በላይ ለሌላ ሰቆቃ ዳርጋችኋል፡፡ይህም አመራራችሁ ከዘመኑ ፍጥነት ጋር ለመጓዝ
እንዳልቻለ ያስረዳልና አመራሩን ከታች ጀምሮ በተማሩ ሰዎች እንዲያዝ ለምን አታደርጉም?

ከክፍለ ከተማው ዝቅተኛ ሰራተኛ ጀምሮ እስከ ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ባለሙያዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በሙስና እየተዘፈቁ የራሳቸውን ሃብት ሲያከማቹና በህዝቡ ላይ ልዩ ልዩ ተጽእኖ ሲያደርሱ ይህን በመከላከል ህብረተሰቡን ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኝ
ከማድረግ ይልቅ ዝምታን የመረጣችሁበት ጊዜ ነው፡፡ዛሬ ሙስና እንደ ህጋዊ አሰራር ተቆጥሮ ማንኛውም አሰራር ያለ እጅ መንሻ የማይፈጸምበት ጊዜ ላይ ቆማችሁ መልካም ሰራን ማለቱ ዋጋ ያሰጠዋል ወይ?

አገራችን አደገች ስትሉ በየጊዜው እንሰማለን፡፡የጥራታቸውን ጉዳይ ሳናነሳ በመንግስትና ህብረተሰቡ መዋጮ የተሰሩ የኮብልስቶን መንገዶች አሉ፡፡ሀገር አቋራጭ መንገዶችም ደረጃቸው አድጎ ተመልክተናል፡፡ በሌላ መልኩ ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ምንጩ
ባልታወቀ ሁኔታ ከመሬት ተነስተው ህንጻ ሲገነቡ እናያለን፡፡በእያንዳንዱ ቤተሰብ ኑሮ ላይ የሚታይ ለውጥ ሳይኖር አድገናል የሚለው መግለጫ ምን ማለት ነው?እድገት ሁሉን ያማከለ ነው ትላላችሁ ታዲያ እድገቱ የታለ? እኛ ሲያድጉ፣መኪና ሲቀያይሩ፣

ቤተሰባቸውን ሲያቀማጥሉና በየቦታው ህንጻ ሲገነቡ የምናያቸው በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦችን ብቻ ነው፡፡ሁሉን ያማከለ ዕድገት ሳይኖር አድገናል ማለቱ ህዝቡን ማታለል አይሆንባችሁም?

በከተማም ሆነ በገጠር ያለው መሬት በተወሰኑ ግለሰቦች፣ አመራሮችና ቤተሰቦቻቸው ከመያዙ ባሻገር ከዓመት ዓመት እየባሰ መሄዱ የመልካም አስተዳደርና የፍትህ እጦት ሆኗል፡፡ወጣቶች መሬት በማጣት ወደ ከተማ መፍለሳቸውና ወደ አረብ ሃገራት
መሰደዳቸው ችግር ሆኖ ቢቀጥልም የተሰጠ መፍትሄ የለም፡፡መሬት በጥቂት ሃብታሞችና ለመንግስት ታማኝ በሆኑ ግለሰቦች እጅ መሆኑ አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል በቤት ክራይ እንዲሰቃይ አድርጎት ይታያል፡፡ታዲያ ፍትሃዊነትን አስፍነናል ለማለት
የሚያስደፍር ስራ አላችሁ ወይ? የሚሉና የመሳሰሉ በገዢው መንግስት የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በድፍረት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡

የገዢው መንግሰት ካድሬዎች በቅስቀሳው መልካም ውጤት እንገኛለን በማለት ከተለያየ መስሪያ ቤቶች የሰበሰቧቸው የመንግሰት ሰራተኞችን በሙሉዓለም አዳራሽ ፤ በክፍለ ከተሞች ለተሰበሰበው ህዝብ ለስላሳ፣ቆሎ፣ውሃናዳቦ በማቅረብ ቡና በማፍላት የ24
ዓመቱን የኢህአዴግ ጉዞ ያስገኘውን ለውጥ በማጋነን ቢያወሩም በታሰበው መልኩ የህብረተሰቡን አስተሳሰብ የሚቀይር ውጤት እንዳልተገኘ በስፍራው የታደሙ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡

የዚህ ዜና ሙሉ ዘገባ በሚቀጥሉት ቀናት ይቀርባል።
http://satenaw.com/amharic/archives/6062

(መልካም ዜና) የፋሺሽቱ የግራዚያኒ ኃውልት ስያሜ እንዲወገድ ውሳኔ ተላለፈ

እንደሚታወቀው፤ “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል ለሚታወቀው ለሮዶልፎ ግራዚያኒ፤ አፊሌ በምትሰኝ የኢጣልያ ከተማ አንድ የመታሰቢያ ኃውልትና መናፈሻ ተቋቁሞለት፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ እ.አ.አ. በነሐሴ 2012 ተመርቆለት ነበር። በኢትዮጵያ ላይ እጅግ አስከፊ የጦር ወንጀል በማስፈጸም ለታወቀው ፋሺሽት ይህንን የመስለ ተግባር ተቀባይነት ስለ ሌለው ማሕበራችን፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ፤ በሚገኙ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች እንዲሁም በመንፈሳዊና በሌሎችም ድርጅቶች ድጋፍ ጭምር ተቃውሞውን በልዩ ልዩ መንገድ ሲገልጽ ከርሟል።

ጥረቱም ሁሉ፤ በቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ እርዳታ፤ መልካም ውጤት ማስገኘት ጀምሯል። ባለፈው ወር፤ እ.አ.አ. መጋቢት 13 ቀን 2015 አፊሌ ከተማ የምትገኝበት የላዚዮ አውራጃ ምክር ቤት ባሳለፈው ውሳኔ የግራዚያኒ ስያሜ በ15 ቀን ውስጥ እንዲወገድ፤ አለበለዚያ ለመታሰቢያ ኃውልቱ የወጣው ገንዘብ እንዲመለስና ተጨማሪ እርምጃም እንደሚወሰድ ገልጿል። የውሳኔውን ዋና ዋና ነጥቦች ከዚህ በታች መመልከት ይቻላል።

በዚህ አጋጣሜ፤ ስለ ኃውልቱ ለተገኘው መልካም ውጤት በድጋፋቸው ለተባበሩት ሁሉ ማሕበሩ ጥልቅ ምሥጋናውን በትሕትና ይገልጻል።

የላዚዮ አውራጃ ኦፊሴያላዊ መግለጫ፤ (ቁ. 24/1) ዋና ዋና ነጥቦች
(ዶር. ግርማ አበበ በኢጣልያንኛው ሰነድ መሠረት በእንግሊዝኛ ባቀረቡት መሠረት)
ጉዳዩ፤ የአፊሌ ከተማ ማሕበራዊ ምክር ቤት ለማርሻል ሮዶልፎ ግራዚያኒ አፌሌ
ስለ መረቀው ትንሽ የሚሊታሪ ሚዩዚየም፤ እ.አ.አ. ሐምሌ 21 ቀን 2012
ያስተላለፈውን ውሳኔ እንዲሰርዝ የቀረበ ጥሪ፤


በላዚዮ አውራጃ የተወሰደ እርምጃ
እ.አ.አ. መጋቢት 13 ቀን 2015
እ.አ.አ. ሕዳር 11 ቀን 2004 የወጣውን የላዚዮን አውራጃ ሕግና ሌሎችንም ጉዳዮች በመመልከት፤
በተጨማሪም እ.አ.አ. በየካቲት 18 ቀን 2002 የወጣውን የክልሉን ሕግ በማስታወስ፤


የአፊሌ (ከተማ) ማሕበረሰብ ምክር ቤት እ.አ.አ. በሐምሌ 21 ቀን 2012 አንድ ትንሽ የሚሊታሪ ሚዩዚየም ለማርሻል ሮዶልፎ ግራዚያኒ እንዲመረቅ የወሰነ መሆኑን በማሰብ፤ ሮዶልፎ ግራዚያኒ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የወንጀለኞች ዝርዝር የተመዘገበ፤ በሰዎች ላይ የመርዝ ጋዝ የተጠቀመና በኢትዮጵያ የቀይ መስቀል ሆስፒታል በቦምብ እንዲደበደብ ትእዛዝ ያስተላለፈ በፋሺሽት ኢጣልያ ቁልፍ መሪ የነበረ መሆኑን በማስታወስ፤

የአፊሌ ማሕበረሰብ ምክር ቤት ትንሹን የሚሊታሪ ሚዩዚየም ለማርሻል ሮዶልፎ ግራዚያኒ በመመረቅ ያስተላለፈውን ውሳኔ እንዲሰርዝ፤ ይህንንም ተግባር፤ የላዚዮ ባለሥልጣን እ.አ.አ. በመጋቢት 13 ቀን 2015 ከወሰነበት ቀን ጀምሮ በ15 ቀኖች ውስጥ እንዲፈጽም ታዟል።

የማሕበረሰቡ ምክር ቤት ውሳኔውን እንዲሰርዝ የተላለፈለትን ትእዛዝ በተፈቀደለት ጊዜ ውስጥ ካላጠናቀቀ፤ ለትንሹ የሚሊታሪ ሚዩዚየም መሥሪያ በአውራጃው ባለሥልጣን የተሰጠውን ገንዘብ እንዲመልስ ይጠይቃል።


በመጨረሻውም፤ የአፊሌ ማሕበረሰብ ምክር ቤት በአውራጃው ባለሥልጣን የተጠየቀውን ሳይፈጽም ቢቀር፤ ባለሥልጣኑ ጉዳዩን፤ የአፊሌ ከተማ ምክር ቤትን ውሳኔ፤ ወደ ፍርድ ለማቅረብ አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል።


ማሳሰቢያ፤ ፋሺሽት ኢጣልያ በውድ ሐገራችን በኢትዮጵያ ላይ በፈጸመችው የጦር ወንጀል ስለ ተጨፈጨፉት አንድ ሚሊዮን ወገኖቻችን፤ ስለ ወደመውና ስለ ተዘረፈው ንብረት ተገቢው ፍትሕ፤ ብቁ የሆነ ካሣና ይቅርታ የመጠየቅ ተግባር እንዲከሰት በመከናወን ላይ ስላለው ጥረት ዝርዝሩን በwww.globalallianceforethiopia.org መመልከት ይቻላል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/40329

Sunday, April 5, 2015

የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት ሊያደናቅፍ የሞከረው እና በዋሽንግተን ዲሲ በሰማያዊ እና የአንድነት ድጋፍ ድርጅቶች የተጠራው የሰማያዊ ፓርቲ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ!!

የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት በሰማያዊ እና አንድነት የድጋፍ ድርጅቶች አስተባባሪነት በዋሽንግትን ዲሲ ከተማ የተጠራውን የሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባ ለማደናቀፍ የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ውጭ እንዳይወጣ አገዛዙ በማን አለብኝነት ቢከለክለውም፤ በዛሬው እለት በዋሽንግተን ዲሲ በሽራተን ሆቴል የተጠራው ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጲያውያኖች በዛሬው ዕለት በቦታው በመገኘት በአገዛዙ በኩል እየተወስደ ባለው አስከፊ የውንብድና ድርጊቶች ሠላማዊ ትግላችን ለአንድም ሰኮንድ አይቋረጥም! እንደውም የበለጠ እልህ እንድንገባና ትግላችንን እና ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥል ያደርገናል ብለዋል። በዚሁ እለትም በተደረገው ስብሰባ ላይ ከፍተኛ ለሰማያዊ ፓርቲ በተደርገው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ላይ ከፍተኛ ገንዘብ የተሰበሰበ ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ ለሰላማዊ ፓርቲ እና ደጋፊዎቹ እንዲሁም ለሌሎች የሰላማዊ ትግል ታጋዮች ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት እና አጋርነት ገልጸዋል!!
በዚሁ ስብሰባ ላይ ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በስክይፕ ከአዲስ አበባ በቀጥታ ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ወቅታዊ እንቅቃሴና የምርጫ ሁኔታ ምን ላይ እንድሚገኝ በሰፊው ለተሰብሳቢው በማስረዳት እና ከተሳታፊኢዎች ለቀርበላቸው ጥይቄዎች ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በዚሁ ስብሰባ ላይ ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማሪያም በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተው ለስብሰባው ተሳታፊዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በዚሁ ስብሰባ ላይ የተለያዩ በውጭ አገር የሚገኙ ሚዲያዎች ተጋብዘው የነበረ ሲሆን ከኢትዮቲዩብ እና ከቪኦኤ በስተቀር ኢሳትን ጨምሮ ሌሎች ሚዲያዎች በቦታው አለመገኘታቸው ታውቋል።
ይህው ስብሰባ በነገው እለት በቦስተን ከተማ የሚቀጥል ሲሆን በቀጣይም በሌሎች ከተሞች ስብሰባው በታቀደው መሰረት የሚቀጥል መሆኑን የታወቀ ሲሆን፤ በተለይ የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት በህዝቡ ላይ የሚያደርሰውን ጭቆና እና ስቆቃ፤ እንዲሁም በፓርቲዎች ላይ የሚካሂደው ወከባ እና እንግልት የበለጠ እልህ እና የትግል አጋርነታቸውን አጥናክረው እንድሚቀጥሉ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየገለጹ መሆኑ ታውቋል!!
http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/17735

Friday, April 3, 2015

በጋሞ ጎፋ ፖሊስ ‹‹መሬቱ ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት ተሰጥቷል፡፡›› በሚል ህዝብ ላይ የጭካኔ እርምጃ ወሰደ


በጋሞ ጎፋ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ አልጌ ቀበሌ ፖሊስ በንፁሃን ላይ የጭካኔ እርምጃ መውሰዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በአባያ ሀይቅ ዙሪያ በእርሻ ስራ ላይ የተሰማሩት ነዋሪዎች መሬት ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት እንደተሰጠባቸው መነገሩን ተከትሎ የአካባቢው ሽማግሌዎች ከሶስት ጊዜ በላይ ለክልሉ አስተዳደር ማመልከቻ ቢያስገቡም መልስ ሊያገኙ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡ የክልሉ አስተዳደር ምንም አይነት መልስ ባይሰጥም የዞኑ አስተዳደር ‹‹መሬቱ ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት ተሰጥቷል፡፡›› የሚል ውሳኔ በማስተላለፉ ነዋሪዎቹ ይህን የዞኑን አስተዳደር ውሳኔ እየተቃወሙ ይገኛሉ፡፡ ይህን የህዝቡን ተቃውሞ ተከትሎም ፖሊስ በአባያ ነዋሪዎች ሰፈር እየመጣ እያስፈራራ እንደሚመለስ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

የካቲት 30/ 2007 እንደተለመደው ፖሊስ ነዋሪዎቹን ለማስፈራራት ወደ ሰፈር በሄደበት ወቅት ነዋሪዎቹ ፖሊሶቹን ‹‹ከሰፈራችን ውጡልን!›› እንዳሏቸው ተገልጾአል፡፡ ይሁንና ፖሊስ ከሰፈራቸው እንዲወጡለት የጠየቁትን አዛውንቶችን ጨምሮ ነዋሪዎች ላይ ድብደባ መፈጸሙ ተገልጾአል፡፡ ፖሊስ አዛውንቶቹ ላይ ድብደባ መፈጸሙን የተቃወሙ ወጣቶች ላይ ጥይት በመተኮስ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ወስዷል፡፡ በወቅቱም አንድ ሰው ሲሞት ከ8 ሰዎች በላይ ከፍተኛ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው ተገልጾአል፡፡

እስካሁን ድረስ በንጹሃኑ ላይ የጭካኔ እርምጃ የወሰዱት ፖሊሶች ምንም አይነት ህጋዊ እርምጃ እንዳልተወሰደባቸውና በስራ ገበታቸው ላይ እንደሚገኙም የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

ምንጭ፦ ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

http://satenaw.com/amharic/archives/5931