Sunday, July 31, 2016

በጎንደር፣ በማክሰኝት፣ በምዕራብ በለሳና በበምዕራብ እስቴ ታላላቅ ሰልፎች ተደርገዋል | 4 አጫጭር መረጃዎች

ከሙሉቀን ተስፋው

1. በጎንደር ከተማ ከአምስት መቶ እስከ ስምንት መቶ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ ሰልፉን ማድመቁ የታወቀ ሲሆን ታሪካዊው ባህታዊ አባ አምሃ ኢየሱስ ሰላማዊ ሰልፉን በሚገባ መርተውታል፡፡ አባ አምሃ ኢየሱስ ለሃይማኖታቸውና ለአገራቸው ሟች እና ዓለምን በቃኝ ያሉ ባሕታዊ ናቸው፡፡ በርካታ ዓመታትን ሕወሓት አስሮ አሰቃይቷቸው ከእስር የተፈቱት በቅርብ ጊዜ ነው፡፡ አዘዞ ላይ ፖሊስ የተወሰኑ ወጣቶችን አስሮ ከሕዝቡ ጋር ግጭት ለመፍጠር ሞክሮ ነበር፡፡ ሆኖም ጀግናው የዐማራ ሕዝብ በአንድነት የታሰሩትን ወጣቶች አስፈትቶ በሰላም ወደ ቤቱ ገብቷል፡፡
አቶ ዘመነ ምሕረት በአቶ ማሙሸት አማረ የሚመራው መኢአድ ምክትል ፕሬዝዳንት ከማክሰኝት እስከ ጎንደር በእግራቸው 40 ኪሎ ሜትር ያክል ከተጓዙ በኋላ ጎንደር እንዳይገቡ ተከልክለዋል፡፡
ከደብረ ታቦር ከዐሥር በላይ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ለሰልፉ የሚሔዱ ሰዎችን አገልግሎት ሰጥቷል፡፡

2. ምዕራብ በለሳ አርባያ፡- ትናንት ምሽት በግጥም የወልቃይት ጠገዴን ዐማራነት እንዲሁም የወያኔ መንግሥት በዐማራ ሕዝብ ላይ የሚያደርሰውን በደል በተመለከተ ሲዘፍን ያመሸን ጎልማሳ ፖሊስ አስሮት አደረ፡፡ ዛሬ ከአርባያ፣ ደንቀዝ፣ ጎሃላና አካባቢው የተሰባሰበው የበለሳ ዐማራ የታሠረውን ጎልማሳ አስፈትቶ በሰላማዊ ሰለፍ ወያኔንና የትግራይን ተስፋፊነት ሲያወግዝ ውሏል፡፡ ከእኩለ ቀን በኋላ ሰልፉ ተበትኗል፡፡ ከአምሳ ሺህ በላይ ሰው ተሳትፎበታል፡፡

3. ጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት፣ ከጎንደር 40 ኪሎ ሜትር በምትገኘው የማክሰኝት ከተማ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ወጣቶች ለሰልፍ ወጥተው ነበር፡፡ ወያኔ ሌባ ነው፤ ዐማራ አሸባሪ አይደለም የሚሉ መፈክሮች አሰምተዋል፡፡ የፖሊስ አባላት ሰልፉን ለመበተን ጥረት አድርገው ነበር፤ ሆኖም ወጣቶች የሚፈለገውን መልእክተ አሰምተው መርሀ ግብራቸውን በሚገባ መልኩ አጠናቀዋል፡፡


4. ምዕራብ እስቴ፣ መካነየሱስ፡ ከጉና ተራራ ሥር የደንሳ አምባን ተንተርሳ የከተመችው የመካነ ኢየሱስ ከተማ ዛሬ ከእኩለ ቀን ጀምሮ በሰላማዊ ሰልፍ እየተናጠች ትገኛለች፡፡ እንደ መረጃ አቀባዮቻችን ሰልፉ ከሰዓት በኋላ በአካባቢው ያለው ገበሬ ሁሉ እንደተቀላቀለው ለማወቅ ተችሏል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/63629

Sunday, July 17, 2016

እናት ኢትዮጵያ በአንድነት በሚያምኑ በልጆቿ ነፃ ትወጣለች!!


የወያኔ ዘረኛ ቡድን ከጅማሮው ይዞ የተነሳውን አማራን የማጥፋት ኢትዮጵያንም የማፈራረስ ሴራ በተግባር ለመፈጸም ደፋ ቀና እያለ ሲገኝ በግልጽም ይሁን በድብቅ በተለያየ መንገድ ስልጣንን እና ጠብመንጃን መከታ በማድረግ በብአዴን ካድሬዎች እየታገዘ ከባድ ወንጀሎችን በአማራው ሕዝብ ላይ ፈጽሟል:: እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ሕዝብን የአማራ ማንነት በመደለዝ የትግራይ ክልል አካል እንዲሆኑ በማድረግ የሚፈጽመውን ደባ የተቃወሙ የወልቃይት ሕዝቦችን በማሰቃየት፣ በመግደልና በማሰር ላይ ይገኛል:: ይህንን የሕወሓት በሕዝብ ላይ የሚፈጽመውን ሽብር በመቃወም እንዲሁም የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ክልል አካልና ማንነቱ አማራ ነው ያሉ ሕጋዊና ሰላማዊ የወልቃይት የማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴ አባላትን ለማፈን ሰሞኑን የተንቀሳቀሰው የሕወሓት ዘረኛ ቡድን በጎንደር ሕዝብ እፍረትን ተከናንቧል:: ይህን ተከትሎ የወልቃት ሕዝብ የወከላቸውን ኮሚቴ አባላትን በመያዝና በማንገላታት በቀጣይነት ለሕዝብ ያለውን ንቀት በማሳየት ተደጋጋሚ ወንጀሎች እየፈጸመ ይገኛል:: በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በሕወሓት መሪነት የሚደረገውን ማንኛውም ግድያ እስር አፈና ማሳደድ እና ተመሳሳይ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች እንደ ኢትዮጵያዊነቴ አጥብቄ እቃወማለሁ/አወግዛለሁ:: በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚደረግ የዘረኝነት ዘመቻ ይቁም!!!
እናት ኢትዮጵያ በልጆቿ ነፃ ትወጣለች!!

ዳዊት ደምመላሽ

Monday, July 11, 2016

ዜጎችን የመኖር ሕልውና እያሳጡ ልማት የለም። የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን መበቀል ይቁም

ከዘጠና ሰባት ምርጫ በኋላ በኣዲስ ኣበባ ሕዝብ ላይ የበቀል ጎራዴውን የመዘዘው የሕወሓት ኣገዛዝ በኦሮሚያ ክልል የተነሳበት ተቃውሞ ለበለጠ በቀል ኣነሳስቶታል። ዜጎችን ሲፈናቀሉ ተለዋጭ ቤት ከመስጠት ይልቅ ከትግራይ ክልል ለሚመጡ የሕወሓት ኣባላት ኮንዶሚኒየም ቤት ከጦር መሳሪያ ምርቃት ጋር ይሰጣቸውል።የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በማለት የገበሬዎችን መሬት በመንጠቅ በኢኮኖሚ የበለጸጉ ጥቂት የሕወሓት ዘረኛ ጎጠኛ ቡድኖችን በኢንቨስትመት ስም ለማስፈር ያሰበው ኣላማ በኦሮሞ ሕዝብ ተቃውሞ ከሽፎ የተበተነበት ጎጠኛው ስርዓት አዲስ አበባን አለማለሁ በሚል ሰበብ የከተማውን ነዋሪ በማንገላታት በመግደል እና ሜዳ ላይ በማፍሰስ እያፈናቀለ መሆኑ በነዋሪው ዘንድ ከፍተና ቅሬታ ከመፍጠሩም ኣልፎ ስልታን ጠባቂ የሆኑ የኣገዛዙ ኣገልጋዮች በተፈጠሩ ግርግሮች መሃል መሞታቸው ይታወቃል። ይህ ለሕዝብ ያልቆመ ፖሊሲ ኣጽድቆ ለማስፈጸም መስራት ያመጣው ኣደገኛ ውጤት ነው።

የወያኔው ኣገዛዝ የኣዲስ ኣበባን ከተማ ሙሉ በሙሉ በሕወሓት ኣባላት እና ዘመዶቻቸው ቁጥጥር ስር በማዋል የኢኮኖሚ የበላይነት ለማግኘት እና ስልጣን ላይ ለመቆየት በሚያደርገው እያንዳንዱ እኩይ ተግባር ዜጎች የመኖር ሕልውና እንዲያጡ ከማድረጉም በላይ ለሕዝብ ያለን ንቀት በተደጋጋሚ እያሳየ ነው። ሰብዓዊነት በጎደለው እና በሕገወጥ መንገድ የኣገዛዙ ኣካላት ነዋሪዎች ከ30 እና 40 ኣመታት በላይ ከኖሩበት መኖሪያቸው ካለምንም ምትክ መኖሪያ ቤት በማፈናቀል የጎዳና ሕይወት እንዲኖሩ በማድረግ ላይ ይገኛል። ተቆጣጣሪ ባሌላቸው የኣገዛዙ መስተዳደር ኣባላት እና ኣመራሮቻቸው ደካማ እና ያልበሰለ ኣመራር ችግር ፈጣሪነት በሕዝብ ላይ ከባድ ችግሮች መፈጠር ቀጥሏል።ለረዥም ኣመታቶች ከኖሩበት ቦታ ሕጋዊ ማስረጃ እና ሰነዶች እንዳላቸው ተረጋግጦ እያለ ተለዋጭ ቤት ለመስጠት ዛሬ ነገ እየተባለ ዜጎች እየተጉላሉ ሲሆን ከትግራይ ክልል ለሚመጡ የሕወሓት ኣባላት ግን የኮንዶምኒየም ቤቶች ከጦር መሳሪያ ምርቃት ጋር እየተከፋፈሉ እንደሚገኙ በየክፍለከተማው የሚገኙ ምንጮች ይገልጻሉ።


ከዘጠና ሰባት ምርጫ በኋላ በኣዲስ ኣበባ ሕዝብ ላይ የበቀል ጎራዴውን የመዘዘው የሕወሓት ኣገዛዝ በኦሮሚያ ክልል የተነሳበት ተቃውሞ የበለጠ በቀሉን እንዳጋለበት በተግባር የሚሰራው ክፋት ይመሰክራል።ዜጎችን የመኖር ሕልውና ኣሳጥቶ በላስኪት ቤት ያውም በክረምት ለበሽታና ሞት መዳረግ ልማት ኣይደለም፤የዜጎችን ሕልውና ያለገናዘበ ያልመዘነ ልማት በቀል እና ዘረፋ ነው።ይህ ሕዝብን የማያከብር ኣገዛዝ በተደጋጋሚ ያስመሰከረው ነገር ቢኖር የግፍ ብትሩን በዜጎች ላይ ማሳረፉን ማሳየቱ ብቻ ነው።የዜጎች ብሶት ኣሁንም እንደቀጠለ ሲሆን የሕወሓት ኣገዛዝ እስካልተወገደ ድረስ ዜጎች የመኖር ሕልውና ስለማያገኙ ሕዝብን በማደራጀት እና በማስተባበር ኣገዛዙን ማስወገድ ቀዳሚ ስራችን ሊሆን ይገባል።

http://www.satenaw.com/amharic/archives/17612

Wednesday, July 6, 2016

ታዛዥና እስረኞችን የሚያጉላላ ዳኛ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ሆኖ ተሾሟል

የምታዩት ግለሰብ ዳኛ ዳኜ መላኩ ይባላል። ሃብታሙ እንዳይታከም እገዳ ያደረገ፣ በቀጠሮ ላይ ቀጠሮ እየሰጠ በ እስረኞች ላይ ትልቅ መጉላላትን የፈጠረ፣ ቀጠሮ ሰጥቶ ብዙ ጊዜ የሚቀር ዳኛ ነው።

“ከሰብዓዊነት በታች ወድቃችሁ ሁላችንንም ክፉኛ አሳዘናችሁን!አምናለሁ፣ ሀብትሽ ላይ የተቃጣውን የክፋት መንፈስ የፍቅር አምላክ ይመክተዋል!” ይላል ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ የዛሬውን አሳዛኝ የፍርድ ቤት ድራማ ተመልክቶ።

ዳኛው ዳኜ መላኩ ይባላል። ላለፉር አንድ አመት በቆጠሮ ላይ ቆጠሮ እየሰጠ እነ ሃብታሙን ሲያከራትትና ሲያጉላላ የነበረ ዳኛ ነው። ይህ ዳኛ የሕወሃትን መመሪያ እየተቀበለ የሚሰራ ዳኛ ተብዬ ካድሬ በመሆኑ በቅርቡ እንደውም ትልቅ ሹመት አግኝቷል። ዳዊት ሰለሞን በዚህ ዳኛ ዙሪያ የሚከተለውን ጽፏል፡


“የሐብታሙ አያሌው የጤንነት ጉዳይ አሳሳቢ በመሆኑና ከአገር ውጪ የተሻለ ህክምና እንዲያገኝ የጉዞ እግዱ እንዲነሳለት ለቀረበ አቤታቱ ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም የመሐል ዳኛው ዳኜ መላኩ ባለመምጣታቸው የሐብታሙ፡ጉዳይ ለሐሙስ ተቀጥሯል ። በችሎት ያልተገኙት ዳኛ ዳኜ መላኩ በቅርቡ በኢህአዴግ ፓርላማ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት በመሆን መሾማቸው አይዘነጋም ።ዳኜ ለረዥም አመታት በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በዳኝነት ከመስራታቸው በላይ የህሊና እስረኞችን ጉዳይ በመከታተል የስርዓቱን ውሳኔ በፍርድ ቤት ስም ሲያስተላልፉ መቆየታቸው ለፕሬዘዳንትነት አብቅቷቸዋል ። ሰውዬው ልጆች ፣ሚስት ፣ቤተሰብና ህሊና ካለውም በስቃይ ውስጥ የሚገኘውን የህፃን አባትና ፍትህ ፍለጋ ችሎት ውስጥ ራሷን ስታ፡በወደቀችው ባለቤቱ ስም እንጠይቃለን ።”

http://www.satenaw.com/amharic/archives/17517