Saturday, July 1, 2017

አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የኢትዮጵያ ምድር የሁሉም ኢትዮጵያዉያን እኩል ሀገር መሆን የሚችለዉ ወያኔ ሲነቀል ብቻ ነዉ !!

ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያዉያን እኩል ሀገር መሆን እንዲችል:- አዲስ አበባን እንደ ማሳያ -
አዲስ አበባም ላይ ሆነ እሌሎች ጉዳዮች ላይ ወያኔ እየወሰነ ያለዉ ሆን ብሎ ህዝብን በሚያፋጅ እና ጸረ ኢትዮጵያዊነት በሆነ መልኩ ነዉ::ኢትዮጵያን ወያኔ በቅኝ ግዛት ስለያዛት ቅኝ ገዥነቱን በሚያጠናክር መልክ: ህዝቡን በሚለያይ መልክ እና በመጨረሻም ኢትዮጵያዉያንን እርስ በርሳቸዉ በሚያፋጅ መልክ ነገሮች እንዲሄዱ ይፈልጋል::
ምናልባት ኢትዮጵያ ከእጁ የምትወጣ ከሆነም በሚነሳዉ የርስ በርስ ጦርነት ድምጥማጧ እንዲጠፋ ወያኔ በደንብ አስልቶ የተነሳዉ ዛሬ አይደለም:: በተንኮል አማካሪዎቹ በኩል ወያኔ ህገ መንግስት ሲያረቅ ዛሬ የሚያናፍሰዉን ሁሉ አስልቶ እና አንሰላስሎ አስቀምጦታል::አሁን እያደረገ ያለዉ ነገሮችን ከተንኮል ጎተራዉ እየጎተተ ኢትዮጵያዉያን እርስ በርሳቸዉ እንዲጨራረሱ እና እንዲበጣጠሱ የጥላቻ ሊጡን ማጎብጎብ ነዉ::
ወያኔ ሌላዉ የመዘዘዉ ካርታ ኦህዴድ (ኦሮሞን ወክሎ) እና ብአዴን (አማራን ወክሎ) የአዲስ አበባን ጉዳይ በመወሰን ሂደት ዉስጥ እንዳሉበት ማስመሰል ነዉ:: እናም የወያኔ ካድሬዎች በደንብ አድርገዉ ይሄን ፕሮፖጋንዳ እያናፈሱት ሲሆን አንዳንድ የዋህ ሰዎች ደግሞ እዉነትም ኦህዴድ እና ብአዴን እዚህ ዉሳኔ ዉስጥ ያሉበት እየመሰላቸዉ የነዚህን ድርጅቶች ስም ሲያነሱ እና ሲጥሉ ይስተዋላል:: ሆኖም ኦህዴድ እና ብአዴን የሚባሉ የፈረስ እና የአጋሰስ ስብስቦች አዲስ አበባ እንዲህ ትሁን ወይም እንዲያ ትሁን እሚለዉ ዉሳኔዉ ዉስጥ እንዳሉ የሚመስላችሁ የዋህ ሰዎች እንዳትሸወዱ ማስገንዘብ እወዳለሁ:: ገና ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረበት: ህገመንግስት እስከጻፈበት እንዲሁም እስካሁን ድረስ ሁሉንም ዉሳኔዉን እየሰጠ ያለዉ ብቸኛዉ ሀይል ወያኔ/ህዉሃት ብቻ ነዉ::
እናም ሁሉም ወገን ለዉጥ ከፈለገ እንዲሁም እዉነተኛ የህዝቦች ዘላቂ ሰላም ከፈለገ አንድ ነገር ላይ ብቻ ያተኩር::ወያኔን በማባረር እና ስሩን በመንቀል ላይ::ኢትዮጵያን ከወያኔ ቅኝ ተገዥነት ነጻ እማዉጣት ላይ::አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የኢትዮጵያ ምድር የሁሉም ኢትዮጵያዉያን እኩል ሀገር መሆን የሚችለዉ ወያኔ ሲነቀል ብቻ ነዉ:: ወያኔ በኢትዮጵያ ፍጅት እና የጎሳዎች እልቂት እንዲመጣ አንዱን አካባቢ የአንዱ ብቻ: አንዱን ቀብሌ የዚያ ንብረት ብቻ እያለ ተንኮል እየጎነጎነ የሚፈጥረዉን ተረት ተረት ተቀብለህ ማንኛህም ወገን አብረህ አትሩጥ:: የቱም አካባቢ የማንም ብቻ አይደለም::ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያዉያን እኩል ሀብት እና እኩል ሀገር ነች::
ወያኔ ሆን ብሎ ኢትዮጵያን በሰባት ክልል ከልሎ ሰባቱን ክልሎች ለሰባት ብሄረሰቦች አድሎ ሲያበቃ ሰማኒያ የሀገሪቱ ብሄረሰቦችን/ጎሳዎችን/ማህበረሰቦችን ሀገር አልባ አድርጓቸዋል::በወያኔ የሀገር ሽንሸና መሰረት አንድ ክልል ሲከለል ያክልል የአንድ ብሄረሰብ ሀብት እና ንብረት ይሆንን እና በዚያ ክልል የሚኖረዉ ሌላዉ ኢትዮጵያዊ ግን መጤ ወይም ሀገር አልባ ተደርጎ እንዲቆጠር ይደረጋል::በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ከሚገኙት ሰማኒያ ሰባት ብሄረሰቦች ዉስጥ ክልል ያላቸዉ ሰባት ብቻ ሲሆኑ ሰማኒያ የሚሆኑት የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች/ማህበረሰቦች/ጎሳዎች ክልል የላቸዉም::
ይሄም ማለት በወያኔ የደንቆሮ ፍች መሰረት እነዚህ ክልል የሌላቸዉ ሰማኒያ ብሄረሰቦች አገር የላቸዉም::ምክንያቱም በየትኛዉም ክልል ቢሄዱ የሚቆጠሩት መጤ ወይም ሀገር አልባ ተደርገዉ ነዉ::የወያኔ አስተሳሰብ በመሰረታዊነት ታላቅ የተስቦ በሽታ የተጠናወተዉ አስተሳሰብ ነዉ::በርካታ ኢትዮጵያዉያንን እየገደለ ያለ እና በመጨረሻም ኢትዮጵያዊነትን ስሩ እንዲነቀል ተግቶ የተቀመረ አስተሳሰብ ነዉ::
በመሆኑም የመጀመሪያ ተቃዉሞ የሚጀምረዉ የወያኔን ህገመንግስት ብሎም ህግጋት: የወያኔን ክልል: የወያኔን ዉሳኔ እና የወያኔን አስተሳሰብ በሙሉ ዉድቅ ማድረግ ነዉ::ወያኔ የሰራዉን እና የወሰነዉን ሁሉ በልብህ አፍርሰህ መነሳት አለብህ:: ተወደደም ተጠላም ወያኔ የሰራዉ እና የዘራዉ ሁሉ ይፈርሳልም: ይደመሰሳልም::የወያኔ መርዝ እና ካንሰራዊ አስተሳሰብ በሙሉ ይነቀላል::
ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያዉያን እኩል ሀገር መሆን የሚችለዉ መቼ ነዉ ብለህ መጠዬቅ ከቻልክ ብቻ ይሄን እዉነት ትደርስበታለህ:: ኢትዮጵያ የኢትዮጵያዉያን ሁሉ ሀገር እንድትሆን ወያኔን ንቀል::ከዚያም ሁሉም በጋራ አንዲት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመስራት ወገብህን ጠበቅ አድርገህ ተነስ::ምርጫ የለም::ያለዉ ምርጫ አንድ ነዉ::ሁሉም እኩል አሸናፊ የሚሆንበትን ስልት እና ስትራቴጅ መንደፍ ነዉ::ይሄም ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያዉያን እኩል ሀገር መሆን እንዲችል ማድረግ::ለዚህም አንዲት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመስራት በጋራ መነሳት::
ኢትዮጵያን እግዚአብሄር ይባርካት !
http://www.zehabesha.com/amharic/?p=77858