Wednesday, December 30, 2015

ወያኔ ሀገራችንን ቆርሶ ለሱዳን ሊሰጥ ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተነሥ!!!

የወያኔ ባለሥልጣናት በሰነድ ደረጃ ከዓመታት በፊት ለሱዳን ስለሰጡት በተግባር መሬት ላይ ደግሞ ሰሞኑን ሊያስረክቡት ሽር ጉድ እያሉበት ስላለው ጉዳይ በተለያዩ የብዙኃን መገናኛዎች ሲጠየቁ “ይሄንን ፈጥረው የሚያወሩት ግርግር ፈጥረው የራሳቸውን ጥቅም ማስጠበቅ የፈለጉ ቡድኖች ናቸው፤ ከእኛ ጋ ጭራሽም በአጀንዳ ደረጃም እንኳን የለም!” ሲሉ መሰንበታቸው ይታወቃል፡፡

እንዲህ ብለው እየተናገሩ ግን የሱዳን መንግሥትና የወያኔ ባለሥልጣናት ይሄንን ሰሞን ርክክቡን መሬት ላይ ተፈጻሚ ለማድረግ ሽርጉዱን አጧጡፈውታል፡፡ ለሱዳን ሊሰጡት ባሰቡት መሬት ላይ ያለውን አርሶአደርም እያፈናቀሉና እየጠረጉ መሬቱን ነጻ ሲያደርጉ ከራርመዋል፡፡ የተፈናቀሉ ገበሬዎች በጎንደር ከተማና በሌሎችን ስፍራዎች ሜዳላይ ፈሰው ይሄንን ሰሞን ጨምሮ በተለያየ ጊዜ ተመልክተናል፡፡ ለምን? ተብሎ ሲጠየቅ የወያኔ ባለሥልጣናት ከሰባት ዓመታት በፊት ይሰጡት የነበረው መልስ በሬቱን የሱዳን ባለሀብቶች እንዲያለሙት በሊዝ ተሰጥቷቸዋል” የሚል ነበር፡፡

በአሁኑ ሰዓት የወያኔ ሠራዊት ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት ርክክብ ኮሽታ በማይሰማበት ሁኔታ ለማስፈጸም በቦታው ሰፍሮ እየተጠባበቀና እንቅፋት ይፈጥራሉ ተብለው የተጠረጠሩትን ያካባቢውን አርሶ አደሮች ለመፍጀት በተጠንቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ይንን የመሬት ርክክብ በመቃወም ሊነሣ የሚችለውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ለመቀነስ ከተቻለም ለማስቀረት ሲባልም ቅማንትንና አማራን የማተላለቅ የማባላት ሴራ ተጠንስሶ ተፈጻሚ በማድረግ የሕዝቡን ትኩረት ከድንበር መሬቱ ላይ አስነሥተው የእርስ በእርስ ፍጅት ላይ እንዲጠመድ በማድረግ መሬቱን ለማስረከብ የተመቻቸ ሁኔታ መፍጠር ቻልን ብለው አስበዋል፡፡

ከአቶ መለስ በኋላ ሁለተኛው የሱዳን ጠ/ሚ በኢትዮጵያ አቶ ኃይለማርያም ለወያኔ “የሕዝብ” ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር “ለሱዳን ተቆርሶ የተሰጠና የሚሰጥም መሬት የለም! በመሬት ጉዳይ ላይም ከሱዳን መንግሥት ጋር ተደራድረን አናውቅም!” በማለት ወያኔ እንዲናገሩ የሰጣቸውን መልእክት ተላላኪው ሰውየ አድርሰውናል፡፡ አቶ ኃይለማርያም ለሱዳን ተቆርሶ ስለሚሰጠው መሬት የተናገሩት ንግግር ስለዚህ ጉዳይ አቶ መለስ አንድ ወቅት ላይ ከተናገሩት ንግግር ምንም የጨመሩት የቀነሱትም አንዲት ነገር ሳይኖር ነበር ያችኑ ሸምድደው መጥተው የተፉት፡፡

“በደናቁርት ቤት ሀን ማወቅ ሊቅነት ነው” እንዲሉ ወያኔም ብልጥ ሆነና ሊያቄለን በማሰብ ይሄንን ቃል ተናገረ፡፡ “ታዲያ እየተፈናቀለ ያለው ገበሬስ በምን ሒሳብና ለምንስ ነው ከቀየው እየተፈናቀለ እንዲለቅ እየተደረገ ያለው?” ተብለው ሲጠየቁ ደናቁርቱ፣ አሕዮቹ፣ የእንግዴ ልጆቹ፣ ጉግማንጉጎቹ፣ በክህደት ተፀንሰው በክህደት የተወለዱቱ፣ ክህደት አሳድጎ ክህደት ያስረጃቸው ጭንጋፎቹ ወያኔዎች ቅንጣት ታክል እንኳን ሐፍረት ሳይሰማቸው በዚያ እርጉም አንደበታቸው “የሱዳን ባለሀብቶች እንዲያለሙት በሊዝ ተሰጥቷቸዋል” ሲሉ የነበረውን የበፊት ሐሰተኛ ምክንያት ትተው ምን ብለው ይመልሳሉ “አይ እሱማ መሬቱ የሱዳን ነው! ሱዳኖቹ መሬታቸውን ለአማራ ገበሬዎች እያረሱ እንዲጠቀሙበት ለረጅም ዓመታት ፈቅደውላቸው ስለነበረ ነው የአማራ ገበሬዎች እዚያ መሬት ላይ ሊገኙ የቻሉት እንጅ መሬቱ የሱዳን ነው!” ብለው በአደባባይ በብዙኃን መገናኛ እንቅጩን ነግረውን አረፉት፡፡

ይንን የሚሉበት ምክንያት እንግዲህ ብልጥ ተሁኖ ተሙቶ “እነዚህ እርጉሞች መሬት እኮ ቆርሰው ሰጡ! ኧረ! እነዚህ ምን ጉዶች ናቸው! እንዴት ዓይነት ከሀዲዎች ቢሆኑ ነው? እንዴት ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ እሠራለሁ እታገላለሁ የኢትዮጵያ መንግሥት ነኝ ከሚል አካል በገዛ ሀገሩና ሕዝቡ ላይ በየትኛውም የዓለማችን መንግሥታት ታሪክ ታይቶ ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ በገዛ ሀገሩና ሕዝቡ ዘንድ ክህደት ፈጽሞ ለባዕድ ሀገር መሬትን ያህል ያውም 1600 ኪሎ ሜትር (ግዝፈ ጉዝ) እርዝመት በ20 እና 40 አንዳንድ ቦታ ላይም በ60 ኪ.ሜ. (ግ.ጉ.) ስፋት የሚያህል አገር የሚያክል መሬትን ይሰጣል? የፈለገውን ያህል ከሀዲና እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ባይ እራስ ወዳድ ቢሆኑ እንዴት በዚህን ያህል የክህደት አረንቋ ውስጥ እራሳቸውን ያሰጥማሉ?” ተብሎ ጉድ እንዳይባልና ሕዝቡም መሬቱን ላለማስነጠቅ እንዳይቆም፣ አይሆንም! አይደረግም! ብሎ እንዳይቆጣ በለመዱት ክህደት እብለት በተሞላ ሐሰተኛ ነውረኛ ስድ አንደበታቸው “ተቆርሶ ለሱዳን የሰጠነውም የምንሰጠውም መሬት የለም! መሬትን በተመለከተ ከሱዳን ጋር ያደረግነው ምንም ዓይነት ድርድር የለም!፣ አይ እሱማ መሬቱ የሱዳን ነው! ሱዳኖቹ መሬታቸውን ለአማራ ገበሬዎች እያረሱ እንዲጠቀሙበት ለረጅም ዓመታት ፈቅደውላቸው ስለነበረ ነው የአማራ ገበሬዎች እዚያ መሬት ላይ ሊገኙ የቻሉት እንጅ መሬቱ የሱዳን ነው!” ብለው ካዱ፡፡

እንዲህ ብለው ክደው ሲያበቁ ግን ከላይ በገለጽኩላቹህ መልኩ አርሶ አደሩን እያፈናቀሉም እየገደሉም ነጻ ሲያደርጉ ቆይተው መሬታችንን ለሱዳን ለማስረከብ ተጠናቀው ተቀምጠዋል፡፡ መቸ ያፍሩና! ሰው ቢሆኑም አልነበር ሊያፍሩ ሊሸማቀቁ ስቅጥጥ ሊላቸው ይችል የነበረው? መቸ ሰዎች ናቸውና? ሕዝቡ እንደራሱ ዓይን አፍንጫ እጅ እግር ይዘው ሲያያቸው ሰው እየመሰላቸው በሚያደርጉት ዕብለት ክህደት ጥፋት “እንዴት! ግን?” እያለ በመደነቅ እጅግ ይገረማል ግራ ይጋባል፡፡ እነሱ የሰው አካል ይዘው ይታዩ እንጅ እንደ ሰው ይናገሩ እንጅ አሁን የወያኔ ግሪሳ ምናቸው ነው ሰው የሚያሰኛቸው በሞቴ?

ጥሩ እንግዲያውስ ያገሬ ገበሬ ቀየ ሱዳኖች እያረሰ እንዲጠቀምበት ለረጅም ዓመታት ፈቅደውለት ሲያርሰው የኖረ መሬት ከሆነ ሕዝቡ “የለም! አይደለም ደማችንን ስናፈስለት አጥንታችን ስንከሰክስለት የኖርነው የኢትዮጵያ መሬት ነው! እንኳንና ይሄንን ያህል መሬት አንዲት ሳንቲ ሜትር (ቅንጠ ጉዝ) እንኳን አንሠጥም!” እያለ ነውና እየቀጠቀጣቹህ እየጨፈጨፋቹህ ከገዛ መሬቱ አጽድታቹህ አፈናቀላቹህ ለሱዳን ከማስረከባቹህ በፊት የምትሉት መሬት የሱዳን ለመሆኑ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በብዙኃን መገናኛ ማስረጃ አቅርቡልና!!!

እውነቱ ግን አይደለምና ይሄ የአሀሬ ገበሬ ከአያት ቅድመ አያት ቅምቅማቱ እየወረሰው እየተረከበው የመጣው፣ እየተጨፈጨፈ እንዲነሣ እንዲለቀው እየተደረገበት ያለው መሬት ይቅርና ስናር ድረስ ያለው መሬት የኢትዮጵያ ለመሆኑ ከበቂ በላይ ማስረጃዎች ሞልተዋል፡፡ ቱርኮች በበርካታ መድፎች ታግዘው ድንበር አልፈው ስናርን በያዙ ጊዜ ዐፄ ቴዎድሮስ ለንግሥት ቪክቶሪያ በጻፏቸው ደብዳቤዎች ልቀቁ ቢሉ እምቢ በማለታቸው ሊገጥሙ እንደሆነ በጻፏቸው ደብዳቤዎች በተደጋጋሚ መግለጻቸውን ማንም የሚያውቀው ታሪክ ዘግቦ የያዘው ሀቅ ነው፡፡ ዐፄ ቴዎድሮስ ገና በሽፍትነታቸው እያሉ ጀምረው ወራሪዎቹ ድንበር እየተሸገሩ ስናር በገቡ ቁጥር ሔደው በመውጋት ድል እያደረጉ እያባረሩ ጠብቀው ያቆዩት መሬት ነበር፡፡

እነሱ ግን ሳይታክቱ ሳይሰለቹ በየጊዜው ድንበር እየዘለሉ እየመጡ ዛሬ ሊወስዱት አቆብቁበው ካሉበት ድረስ ደረሱ፡፡ እጅግ የሚገርመኝ ነገር የሱዳን መሬት ከኛን ሀገር ከእጥፍ በላይ 2,505,813 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (አራት ማዕዘናዊ ግዝፈ ጉዝ) ሆኖ እያለ የሕዝባቸው ቁጥር ደግሞ ከእኛ ሕዝብ ከግማሽ በታች አርባ ሚሊዮን (አእላፋት) ሆነው እያለ የዚህን ያህል መስበድበዳቸው ነው፡፡ “ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል” ነው የሚባለው?

ወያኔዎች እውነት በሀገርና በሕዝብ ላይ ጸያፍና አስነዋሪ ክህደት የፈጸማቹህ ካሆናቹህና በድርጊታቹህ የማታፍሩ ከሆነ መሬቱ የኢትዮጵያ ለመሆኑ ጠንቅቀው የሚያውቁ ማስረጃና መረጃ የያዙ ተቆርቋሪ ወገኖች አሉና ከእነሱ ጋፍ ፊት ለፊት በመገናኘት የያዙት ማስረጃና መረጃ የተሳሳተ የውሸት መሆኑን እንድንረዳ እንድናውቅ አድርጋቹህ አሳፍራቹህ ስትሰዷቸው እንያቹሃ? እስኪ ወንድ ከሆናቹህ ከሀዲ፣ ነውረኛ፣ ወራዳ ወንበዴ ካልሆናቹህ ይሄንን አድርጉና በሉ እንያቹሃ?

መንጋ ጭንጋፍ የእንግዴ ልጅ ሁላ!!! እኔ አይደለም እናንተን ሆኘ መኖርን ላስብ ልመኝ ይቅርና እናንተን በማየቴ በእናንተ ዘመን በመኖሬ ራሱ እንዴት ዓይነት ልገልጸው ከባድ ሐፍረት መሸማቀቅ ውርደት እንደሚሰማኝ እንዴት አድርጌ በነገርኳቹህ!!! እንዴትስ አድርጌ ብነግራቹህ እናንተን ይገባቹሀል እንዴ?

የነውረኛነታቹህ ነውረኛነት ጭራሽ “ሀገሬ ተቆርሳ ባዕድ አይወስዳትም ይሄንን በዓይኔ ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ!” እያለ ከሱዳን ወታደር ጋር ጉርቦ ለጉርቦ የሚተናነቀውን ጀግና ቆፍጣና ያገሬን ገበሬ “እንደ አማራ ክልል ሽፍቶች ጠብ ጫሪነት ቢሆን ኖሮ የሱዳንና የኢትዮጵያ ግንኙነት ይሻክር ነበር። ሱዳኖች ታግሰውናል!” ብላቹህ ጀግኖቹን ቆራጦችን የቁርጥ ቀን ብርቅና ድንቅ ዕንቁ ወገኖቻችንን “ሽፍታ” ብላቹህ አዋርዳቹህ ስትጠሩ እንዲያው ጥቂት እንኳን አታፍሩም? ለነገሩ ሀገር ማለት ድንበር ማለት ምን ማለት እንደሆነ የት ታውቁትና ምድረ ምናምንቴ የእርግማን ልጅ ቆሻሻ ሁላ!

እንግዲህ ልዩነታችን ይሄንን ያህል ነው፡፡ ምንም እንኳን እናንተ ያልተማራቹህ የደናቁርት ጥርቅም ብትሆኑም ቅሉ “ያልተማረ” እያላቹህ የምትገልጹት ያገሬ ገበሬ ለአንድያ ለፍሱ ሳይሳሳ ለውድ ሀገሩ ለክቡር ድንበሩ መሥዋዕትነትን ሲከፍል “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል!” የሚለውን የአሕያ አስተሳሰብ የሁለንተናቹህ መርሕ ያደረጋቹህት እናንተ የጉግ ማንጉግ ጥርቅሞች ግን “የእኛ (ወያኔ) ህልውና አደጋ ላይ ከሚወድቅ የምናባቱ ሀገር፣ የምናባቱ ሉዓላዊነት፣ የምናባቱ ብሔራዊ ጥቅም” እያላቹህ ከሀገር መሬት እስከ ሕፃናት ሴቶች ልጆቻችን ድረስ ለባዕዳንና ለጠላት አሳልፋቹህ በመስጠጥ የጠላት መጫዎቻ መቀለጃ በማድረግ ይህች ሀገርና ይሄ ሕዝብ አይቶት ሰምቶት ለማያውቀው ውርደት ዳረጋቹህት፡፡ የኢትዮጵያዊነት የሰውነት ልዩነታችንን ርቀት ልብ አላቹህት? ይሄንን ያህል ናቹህ ምድረ ወራዳ! እንዴት ብላቹህ ልብ ትሉታላቹህ? መቸ የሰውነት መገለጫ አላቹህና!
እንዲያው በሞቴ አንድ ጥያቄ ልጠይቃቹህ፡- ስንት ዓመት ለመኖር ነው በዚህ ደረጃ ዘቅጣቹህ አድፋቹህ ጎድፋቹህ እረክሳቹህ የገዛ ሀገራቹህን የገዛ ሕዝባቹህን ጥቅም አሳልፋቹህ በመስጠት እራሳቹህን ለማኖር የምትጥሩት? ሰው እንዴት በዛ ቢባል ከ80 ዓመት በላይ ለማይኖረው ዕድሜ የዚህን ያህል እራሱን ያዋርዳል? ሽህ ዓመት ትኖራላቹህ እንዴ? እንዲህ እያደረጋቹህ “ኢትዮጵያዊያን ነን” ስትሉ እንዲያው ትንሽም አታፍሩም? ሰው ብትሆኑ ነበራ! በነውረኛ ድርጊታቹህ በክህደታቹህ ልታፍሩ ልትሸማቀቁ ትችሉ የነበረው፤ እናንተ ምናቹህ ሰው ነው?

ወገናዊ ጥሪ ሀገሩን እያገለገለ ለሚመስለው የወያኔ ሠራዊት፡-

በገዛ ሀገራቹህና ሕዝባቹህ ላይ ታሪካዊ ክህደት በመፈጸም ወደ ሱዳን ተቆርሶ የሚሰጠውንና ተቆርሶ የሚከለለውን መሬት ለማስረከብ የሀገራቸውን መሬት አሳልፈው ላለማሰጠት ሲዋደቁ ለቆዩትና ለመዋደቅ የተዘጋጁትን ያገሬን ገበሬዎች “በአፈጻጸሙ ላይ ችግር የሚፈጥሩ ችግር ፈጣሪዎች!” ብሎ በመፈረጅ በእነሱ ላይ እርምጃ ለመውሰድ አቆብቁበህ ያለህ የወያኔ ሠራዊት ሆይ! እባካቹህ የዚህ ምስኪን ሕስብና ምስኪን ሀገር አካ መሆናቹህን አስቡ! መገመት እንደሚቻለው ማሰብ ማሰላሰል የምትችሉ ይመስለኛል፡፡ የኢትዮጵያ ሠራዊት ነን ብላቹህ እንደምታስቡም ያታወቃል፡፡ እንዲህ ከሆነ ዘንዳ እንደወታደርነታቹህ የሀገርን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ከባዱ ግዴታና ኃላፊነት ያለው በእናንተ ላይ ሆኖ ሳለ ወያኔ እናንተን በመጠቀም የሀገርን ሰፊ መሬት አሳልፎ ለባዕድ ለመስጠት የሚያደርገውን ጥረት እንደምን በጸጋ ተቀብላቹህ አስፈጻሚዎች ትሆናላቹህን???
እስኪ ልብ ብላቹህ አጢኑት? እውን ሀገር ለማስገኝጠል ሉዓላዊነቷን ለማስደፈር ነው ወይ ወደ ውትድርናው የተቀላቀላቹህ? “የገዛ ሀገሩን ያፈራረሰው ብቸኛውና የመጀመሪያው ከሀዲ ሠራዊት” ሠራዊት ተብለህ በታሪክ ተወቃሽ ተከሳሽ መሆን ትፈልጋለህ ወይ? ካልሆነ በወገንህ ላይ ልታርከፈክፈው ያዘጋጀኸውን አረር ከውስጥህ ለሀገር ሳይሆን የሀገርን ጥቅም አሳልፎ በመስጠት ለወያኔ ህልውና ታማኝ ሆነው ታጥቀው እየሠሩ ባሉት ከሀዲዎችና በሱዳን ወራሪ ወታደሮች ላይ አርከፍክፈውና ታሪክ ሠርተህ የዜግነት ግዴታህን ተወጣ! ስምህን ከባንዶች ሳይሆን ከጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ተርታ አሰልፍ! አስቀምጥ! ይሄንን ቆራጥ እርምጃ በመውሰድ የተጣለብህን ታሪካዊ አደራ ተወጣ! አደራ በሀገሩ ፍቅር ተለክፎ ሰክሮ ነሁልሎ የሀገሩ መሬት በከሀዲያን በባንዶች ለባዕድ መሰጠቱ ኅሊናውን ባሳተው ባንገበገበው ባሳበደው ወገንህ ላይ እንዳታዘንበው በሰማይና በምድር ንጉሥ በመድኃኔዓለም ክርስቶስ፣ በአጋእዝተ ሥላሴ ስም የተገዘትክ የታሠርክ ያድርግህ!

ወገናዊ ጥሪ የወያኔን የውንብድናና የጠላትነት ተግባር እንዲህ እየተመለከትክ ለወያኔ በመሥራት ወያኔን እያገለገልክ ሀገርን የምታገለግል ለሚመስልህ የመንግሥት ሠራተኛ የወያኔ ደጋፊ ሁሉ፡-

እንደምታዩት ወያኔ ከራሱ በላይ ቅንጣትም እንኳን ብትሆን ለሀገርና ለሕዝብ የማያስብ የነውረኞች የጉዶች ቡድን ነው፡፡ ይሄ የጉዶች ቡድን ከራሱ በላይ ለማንም እንደማያስብ ለራሱ ጥቅም ከሆነ ግን አላደርገውም የሚለው ምንም ነገር የሌለው ከሀዲ እርጉም የባንዳ ጥርቅም መሆኑን እያያቹህ “እኛን እስከጠቀመ ድረስ፣ በልተን እስካደርን ድረስ” በሚል ይሄንን ግዙፍ ጸያፍ የክህደት ተግባሩን በቸልታ ብትመለከቱ አስተሳሰቡ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” እንደመሆኑ ይሄ በሀገር ላይ የጨከተ የአውሬና የደናቁርት መንጋ ነገ ለእያንዳንዳቹህም የማይመለስ መሆኑን ጠንቅቃቹህ በመረዳት “በቃኝ! ከዚህ በኋላ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የወያኔ የጥፋትና የክህደት ሥራ ተባባሪ አልሆንም!” ብላቹህ በአንድነት በመነሣት ከራሱ በስተቀር “ኧረ እንዲያው ድንቁርናቸው ነው እንጅ ለራሳቸውም እኮ አይጠቅምም ነበር!” ለማንኛውም ከራሱ በስተቀር ለማንም በማያስበው ከሀዲ መንጋ ላይ በመነሣት እራስህን ሀገርህን እንድታድን በልዑል እግዚአብሔር ስም ትጠየቃለህ፡፡ ይሄንን ባታደርግ ግን ብዙ ሳትቆይ የሚቆጭህ መሆኑን አበክሬ ላስገነዝብህ እወዳለሁ “ወይኔ! ምነው ያኔ ተነሥቸ በነበርኩ!” የምትልበት መራራ ጊዜ ከፊትህ መጥቶ አፈር ድሜህን ያስግጥሀል፡፡ ልብ አድርግ፡፡

ወገናዊ ጥሪ ለትግሬ ሕዝብ፡-

የትግሬ ሕዝብ ሆይ! ወያኔ የህልውናው መሠረቱና አለኝታው የባዕዳን ሀገራት መንግሥታና ሆዳም አሕያ የየብሔረሰቡ አድር ባይ ሹማምንት አገልጋዮቹ መሆናቸው ቢታወቅም የአንተ አቅም ለእሱ ህልውና የሚያበረክተው ኢምንት እንደሆነ ቢታወቅም አንተን መሠረቴ አለኝታየ እያለ ህልውናው መሆንህን እየተናገረ በስምህ በመነገድ እንደኖረና እንዳለ አሳምረህ ታውቀዋለህ፡፡ 

እስከአሁንም ወያኔ በዚህች ነገርና ሕዝብ ላይ በተደጋጋሚ ክህደት ሲፈጽም “በስማችን እየገዛህማ እንዲህ ልታደርግ አትችልም!” ስትል ታይተህ ተሰምተህ አታውቅም፡፡ ይልቁንም የሚመካበትን ሙሉ ድጋፍ ስትሰጥ ነው የኖርከው፡፡ እንኳንና እዚህ ሀገር ውስጥ ያለኸው ይቅርና በውጪ ሀገራት በነጻነት መቃወም በሚያስችላቸው ሀገራት ያሉ ልጆችህ እንኳን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገን ጋር ሆነው የወያኔን የክህደት ተግባር ሲያወግዙ ሲቃወሙ ታይተው ተሰምተው አይታወቁም፡፡

ወያኔ የህልውናው መሠረትና አለኝታው አንተ እንደሆንክ እንድትታሰብ ማድረጉና ያደረገውን ቢያደርግ ዝም ማለትህ ወያኔ በፈጸመው ክህደትና ወንጀሎች ነገ ተጠያቂው አንተ መሆንህን ልብ ብለኸዋል ወይ? ከዚህ በላይ መቸና ምንስ ቢያደርግ ነው “አይ! በስማችን እየተጠቀምክማ እንዲህ ልታደርግ አትችልም! አንተ ነገ አላፊ ነህ እኔ ግን እንደ ሕዝብ ኗሪ ነኝ ነገ አንተ በፈጸምከው ግፍ ወንጀልና ክህደት ሁሉ እኔ ተጠያቂ ዕዳ ከፋይ መሆኔ ስለማይቀር እንዲህ እንኳን ልታደርግ አትችልም!” የምትለው መቸና ምንስ ቢያደርግ ነው? የወያኔ ነውረኛ ቆሻሻ ወራዳ ማንነት እንደ ሕዝብ አያሸማቅቅህም ወይ? አያሳፍርህም ወይ? እባክህ ይሄ የወያኔ አሳፋሪና አዋራጅ ክህደት መንቂያህ ይሁንና “ዞር በል ወራዳ አዋራጅ አላውቅህም! አልይህ!” በማለት ከሌሎቹ ወገኖችህ ጋር ቁም ተሰለፍ! “አንተን የሚበላ ጅብ እኔንም ይብላኝ” ከሚለው አስተሳሰብህ ተላቀቅ!!!

ወገናዊ ጥሪ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፡-

የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ዝምታህ እስከመቸ ነው? ከቶ ምን ቀረህ? ይሄ የወያኔ ክህደት ምንም ቢሆን ልትታገሳቸው ከማትችላቸው ጉዳዮች እንዳልሆነ እያወክ የዝምታህ ምሥጢር ምንድን ነው? ምን ዓይነት አዚም ነው አፍዝዞ አደንዝዞ እያስበላህ ያለው? ኧረ እባክህ ንቃ! ኧረ እባክህ ጨርሰህ ሳትጠፋ በቃ! በል?

አንድ ላይ ሆ! ብለህ ይሄንን ግፈኛ ነውረኛ ወራዳ አገዛዝ እንዳትገላገል ያደረጉህን እንደወትሮህ ሀገር ስትነካ ቀፎው እንደተነካበት ንብ አንድ ላይ ሆ! ብለህ በመነሣት የሀገርህን ድንበር ብሔራዊ ጥቅምህን እንዳታስጠብቅና እንዳታስከብር ወያኔ ኦነግና ሌሎቹ የጥፋት ኃይሎች በዘር በሃይማኖት ከፋፍለው የጥንካሬህን ምንጭ አንድነትህን አፈራረሱት የአንደኛህ ሕመም ለሌላኛህ የማይሰማህ የጎጥህ እንጅ የሀገርህ ጥፋትና ጉዳት የማይገድህ የማትተባበር አድርገው የግፍ አገዛዙ በአፍ ጢምህ እስኪደፋህ በሰብእናህ እስኪጫወትብህ ሀገር አልባ አድርጎ እንደባሪያ እንደመጻተኛ በሀገርህ ጉዳይ የማያገባህ ባዕድ እስኪያደርግህ አገርህን ሲያፈራርሳት ድረስ ተሸክመኸዋል፡፡

በፊት ከነበረህ የላቀና የሠለጠነ አስተሳሰብህ ማለትም ጠባብ ጎጠኝነት ጠባብ ብሔርተኝነት ጎጅ እንጅ ጠቃሚ አለመሆኑን፣ ጠባብ ብሔርተኞች ሥልጣን ይዘው ሆነው እንደምናያቸው ፀረ ዲሞክራሲያዊና (መስፍነ ሕዝባዊና) ፀረ ሰብአዊ አስተሳሰብ መሆኑን፣ የሰው ልጆችን ዕኩል ያለማየት ለማየትም ያለመፈለግ አድልኦ የሞላበት ኢፍትሐዊ አስተሳሰብ የተጣባው የተቆራኘው መሆኑን፣ ሀገር የሚያፈርስ ነቀርሳ አስተሳሰብ መሆኑን ጠንቅቀህ ተረድተህ አንድነትን የነገሮችህ ሁሉ መሠረት በማድረግ በምንም ነገር ብትፈተን ምንም ዓይነት ችግር ቢደርስብህ ጨቋኞችና ሀገር የተለያዩ ነገሮች መሆናቸውን በመገንዘብ አንድነትህን ለድርድር ሳታቀርብ በሀገርህና በህልውናህ ላይ የሚመጣብህን ፈተና ስትመክት፣ ስታከሽፍ፣ ስታሸንፍ ከኖርክበት የሐሳብ ልቀትህና የሠለጠነ ሥነልቡናዊ ልዕልናህ ከፍታህ አውርደው የድንቁርና አስተሳሰብ በሆነው፣ ጠንቅ፣ ችግር፣ ሞት በሞላበት ጠባብ የጎጠኝነት ነቀርሳ የመረዙህንና በጠንቅ በምስቅልቅል ማጥ ውስጥ ላትወጣ እያሰመጡህ ያሉትን ወያኔን ኦነግንና ሌሎች የጥፋት ኃይሎችን ከነደንቆሮ አስተሳሰባቸው ከጫንቃህ ላይ አሽቀንጥረህ ወርውረህ በአንድነት መድኃኒትህ እራስህንና ሀገርህን ከሞት ከጥፋት ከመፈራረስ ታድን ትታደግ ዘንድ የእነ አርበኛው አቡነ ጴጥሮስን ግዝት የሰማችው ምድር ለአንተ ደግሞ አፍ አውጥታ “የኔ ሞት ያንተ ሞት ነው! የኔ መፈራረስ ያንተ መፈራረስ ነው! የኔ መጥፋት ያንተ መጥፋት ነው! ልብ አድርግ ስማ! ስማ! ስማ!” እያለች ትማጸናለች ለራስህ ብትል ስማ!!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!


ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49582

Sunday, December 27, 2015

እነ ሀብታሙ አያሌው በጠቅላይ ፍ/ቤት የቃል ክርክር አደረጉ | አብርሃ ደስታ “ጭቆናን ካላጋለጥኩ ምኑን ተቃዋሚ ሆንኩት?” አብርሃ ደስታ

‹‹እኔ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል እንደመሆኔ መጠን የኢህአዴግን ጭቆና ማጋለጥ ግዴታዬም መብቴም ጭምር ነው! ይህን ካላደረጉ ምኑን ተቃዋሚ ሆንኩ?›› አብርሃ ደስታ ‹‹እኔ አሸባሪ አይደለሁም! የታሰርኩት በኢህአዴግ የፖለቲካ ሴራ ነው! እኔ የፖለቲካ እስረኛ ነኝ!›› ዳንኤል ሺበሺ


በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በሥር ፍ/ቤት ውሳኔ በነፃ የተሰናበቱት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ አቶ የሺዋስ አሰፋና በተመሳሳይ የክስ መዝገብ ውስጥ ከአመራሮቹ ጋር የተከሰሰው አቶ አብርሃም ሰለሞን በፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2008 ዓ.ም በመቅረብ የቃል ክርክር አድርገዋል፡፡

በችሎቱ የተሰየሙት ግራ ዳኛ መዝገቡ ለዛሬ የተቀጠረው ታህሳስ 8 ቀን 2008 ዓ.ም ተከሳሾቹ የፍ/ቤቱ ሰብሳቢ ዳኛ የሆኑት አቶ ዳኜ መላኩ ከሰብሳቢነታቸው እንዲነሱ ባቀረቡት የፅሁፍ አቤቱታ ላይ መልስ ለመስጠት፤ የተከሳሾቹንና የአቃቤ ሕግን የቃል ክርክር ለማድመጥ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ተከሳሾቹ ‹‹ሰብሳቢው ዳኛ ይነሱልን!›› ብለው ያቀረቡት ጥያቄ ፍ/ቤቱ ስላላመነበት ውድቅ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

አቃቤ ሕግ በችሎቱ ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታው ተከሳሾቹ ከግንቦት ሰባት አመራር አባላት ጋር በተለያየ ጊዜ መገናኘታቸውን፤ ይህንንም የሚያስረዳ ማስረጃ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ማቅረባቸውን ነገር ግን የስር ፍ/ቤቱ እነዚህን ማስረጃዎች ሳይመዝን ‹‹በደፈናው ውሳኔ ስለሰጠ›› ይግባኝ መጠየቃቸውንና የስር ፍ/ቤቱ ውሳኔ ሲሰጥ ከጭብጥ መውጣቱን ገልጿል፡፡ ‹‹ፍ/ቤቱ ከፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ አንቀፅ 23 መሰረት የቀረበውን የሰነድ ማስረጃዎች በመመልከት የስር ፍ/ቤት ውሳኔን በመሻር ተከሳሾቹ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ ፍ/ቤቱ ይወስንልን ዘንድ እንጠይቃለን›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

1ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌውና 5ኛ ተከሳሽ አቶ አብርሃም ሰለሞን በጠበቃቸው አምሃ መኮንን በኩል የመከራከሪያ ሃሳባቸውን አቅርበዋል፡፡ አቶ አምሃ መኮንን የስር ፍ/ቤቱ ደምበኞቻቸውን በነፃ ሲያሰናብታቸው የቀረቡትን ማስረጃዎች መዝኖ መሆኑን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡ አቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ያቀረባቸው ነገሮች እንደመረጃ እንጂ እንደማስረጃ ሊያዙ እንደማይገባ የተከሳሾቹ የቀድሞ ጠበቃ በስር ፍ/ቤት ክርክር አድርገው የስር ፍ/ቤቱ ሐምሌ 2 ቀን 2007 ዓ.ም ‹‹በማስረጃ ሊያዙ ይገባል!›› ብሎ ብይን ማስተላለፉን አቶ አምሃ አውስተዋል፡፡ ጠበቃው ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ በኩል የሚቀርቡ ማስረጃዎችም ፍ/ቤት ሊመረምራቸው እንደሚገባ ሲያስረዱ፡- ‹‹የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ በኩል የሚቀርቡ መረጃዎችን ፍ/ቤቱ ሙሉ ለሙሉ የሚቀበል ከሆነ የፍ/ቤቱ ሚና ምን ሊሆን ነው? ፍ/ቤቱ ከተቋሙ በኩል የሚቀርቡለትን መረጃዎች ሙሉ ለሙሉ የሚቀበል ከሆነም ፈራጁ ፍ/ቤት ሳይሆን ብሔራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ነው›› በማለት አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡

ደምበኛቸው አቶ ሀብታሙ አያሌውም በክሱ ላይ ‹‹ዘመነ ካሴ›› ከተባለው የግንቦት ሰባት አባል ጋር በመነጋገር አብረው ለመስራት ተስማሙ ተብሎ ቢገለፅም ይህን የሚያስረዳ ማስረጃ አለመቅረቡን ገልፀዋል፡፡ ደምበኛቸው ከግለሰቡ ጋር ባደረጉት የስልክ ልውውጥ አንድም ቦታ ላይ አብረው ለመስራት መስማማታቸውን እንዳልገለፁ ጠበቃው ጠቁመዋል፡፡ በክሱ ላይ የአንድነት ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ የሆነው አቶ ሀብታሙ አያሌው ከዘመነ ካሴ ጋር ግንኙነት አደረጉ ተብሎ የተገለፀው ከእውነታ የራቀ መሆኑን ጠበቃው ገልፀዋል፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ አቶ ሀብታሙ አይደለም የአንድነት ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሊሆኑ ቀርተው፤ የፓርቲው አባል እንዳልነበሩም አቶ አምሃ አስረድተዋል፡፡ አቶ ሀብታሙ በበኩላቸው በክሱ ላይ ተከሳሽ በዚህ የሞባይል ቁጥር ግንኙነት አድርጓል ተብሎ አለመገለፁን የስልክ ልውውጡም ምን እንደሆነ የሚያስረዳ አንዳች ነገር አለመቅረቡን ለፍ/ቤቱ አስረድተዋል፡፡

አቶ አምሃ ደምበኛቸው በሆነው 5ኛ ተከሳሽ አቶ አብርሃም ሰለሞን ላይ ምንም አይነት የሰነድ ማስረጃ አለመቅረቡን የግንቦት ሰባት አባል ነው ሲባልም፤ በግንቦት ሰባት መዋቅር ውስጥ እንዳለ የሚያሳይ ማስረጃ አለመቅረቡን ደምበኛው በምንም አይነት የሽብርተኝነት ተግባር ላይ እንደተሰማራ የሚገልፅ ምንም አይነት ማስረጃ አለመቅረቡን ገልፀዋል፡፡ አቶ አብርሃም ሰለሞን በበኩሉ ያለአንዳች ማስረጃ መታሰሩን ሲያስረዳ፡- ‹‹ከታሰርኩ በኋላ ነው ማስረጃ ሲፈለገብኝ የነበረው፤ ከታሰርኩ በኋላም ቤቴ እንኳ አልተፈተሸም፡፡ መንግስት አሰረኝ ብዬ አላምንም ያሰረኝ አንድ ግለሰብ ነው›› ሲል ተደምጧል፡፡

2ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ 3ኛ ተከሳሽ አቶ አብርሃ ደስታና 4ኛ ተከሳሽ የሺዋስ አሰፋ ያለጠበቃ በመቆም በግል ክርክራቸውን ያካሄዱ ሲሆን፤ ሶስቱም ተከሳሾች የአቃቤ ሕግ የይግባኝ ማመልከቻ ላይ እነሱን የሚመለከት ቅሬታ አለመቅረቡን ለፍ/ቤቱ ገልፀዋል፡፡ አቶ ዳንኤል ሺበሺ ‹‹እኔ አሸባሪ አይደለሁም! የታሰርኩት በኢህአዴግ የፖለቲካ ሴራ ነው! እኔ የፖለቲካ እስረኛ ነኝ!›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ የቃል ክርክር ለማድረግ ያዘጋጁት ወረቀትም በማረሚያ ቤቱ እንደተቀደደባቸው ለፍ/ቤቱ አሳይተዋል፡፡ ወረቀቱ ማህተም የተደረገበት ቦታ ተቀዶ መውጣቱን በችሎቱ ለነበሩ ታዳሚያን በግልፅ ታይቷል፡፡

3ኛ ተከሳሽ አቶ አብርሃ ደስታም ከታሰሩ በኋላ ማስረጃ ሲፈልግባቸው እንደነበርና በብሔራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ የሚቀርብ መረጃ በፍ/ቤት ሳይመዘን ሙሉ ለመሉ ተቀባይነት የሚያገኝ ከሆነ ተቋሙ ከሳሽም፣ መስካሪም፣ ዳኛም ሆነ ማለት ነው፡፡ ይህ ከሆነ ዘንድ ደግሞ ፍ/ቤት መምጣትም አያስፈልግም ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ በክሱ ላይ ለኢሳት ቴሌቪዥን ቃለምልልሰ ሰጠ ተብሎ የቀረበው ክስ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ሲያስረዱ፡- ‹‹እኔ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል እንደመሆኔ መጠን የኢህአዴግን ጭቆና ማጋለጥ ግዴታዬም መብቴም ጭምር ነው! ይህን ካላደረጉ ምኑን ተቃዋሚ ሆንኩ?›› በማለት ለፍ/ቤቱ የገለፁ ሲሆን፤ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በመቅረብ ሃሳባቸውን ሲገልፁ የነበሩትም የኢህአዴግን ጭቆናን ማጋለጥ መብታቸው በመሆኑ እንደሆነ ለፍ/ቤቱ አስረድተዋል፡፡

4ኛ ተከሳሽ አቶ የሺዋስ አሰፋ በእሳቸው ላይ የቀረበ አንድም የሰው ምስክር እንደሌለ ገልፀው፤ ማዕከላዊ በነበሩበት ወቅትም በምርመራ ላይ አንድም ቀን ስለግንቦት ሰባት ተጠይቀው እንደማያውቁ ምርመራ ላይ ሲጠየቁ የነበሩትም ስለ ሰማያዊ ፓርቲ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አቶ የሺዋስ የሰማያዊ ፓርቲ አባል በመሆናቸው ብቻ አያሌ መከራዎችን እየተጋፈጡ እንደሚገኙ ለፍ/ቤቱ አስረድተዋል፡፡ ያለፉትን 6 ወራት በማንም አለመጎብኘታቸውን ለፍ/ቤቱ ገልፀዋል፡፡

ፍ/ቤቱ የቃል ክርክሩ በፅሁፍ ተገልብጦ ከቀጣይ ቀጠሮ በፊት ከመዝገቡ ጋር ተያይዞ እንዲቀርብ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ 1ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌው የሚገኙበት የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተከሳሹ ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ታህሳስ 19 ቀን 2008 ዓ.ም መልስ እንዲሰጥ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ የማረሚያ ቤት ተወካዩ በተጠቀሰው ቀን አቶ ሀብታሙን ይዞ እንዲቀርብ ፍ/ቤቱ አዟል፡፡
የፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የግራ ቀኙን ክርክር መዝኖ ውሳኔ ለመስጠት ለታህሳስ 29 ቀን 2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ እነ ሀብታሙ አያሌው ነሐሴ 14 ቀን 2008 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ከተመሰረተባቸው የሽብርተኝነት ክስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ውሳኔ ማስተላለፉ አይዘነጋም፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49442




Thursday, December 24, 2015

ግፍ ሲፈጸም ዝምታን ከመረጥን እንደ አገር እንጠፋለን -ሃብታሙ አያሌው | ከቂሊንጦ እሥር ቤት

ለነጻነታቸው በሚያደርጉት ትግል፣ ኢትዮጵያ እንደ እናት ሆና የረዳቻቸዉ ፣ እንደ ጋና፣ ታንዛኒያና ሴኔጋል ያሉ የአፍሪካ አገሮች እንኩዋን ሳይቀሩ የትናየት በደረሱበት ዘመን፣ እንደ ደርግ ዘመን አሁንም በኢትዮጵያ፣ ረሃብና ችጋር የሚገድለን አልበቃ ብሎ፣ ኢትዮጵያዉያን በኢትዮጵያዉያን እጅ እየተገደሉ ነው። 

በቅርቡ በጎንደር እና በኦሮሚያ የተለያዩ ቦታዎቸ እንዳየነው፣ በዜጎች ላይ የደረሰው ግድያ፣ ድብደባና ግፍ እጅግ በጣም ልቤን እንዳደማው መግለጽ እወዳለሁ። ለሞቶት ነፍስ ይማር፣ ለቤተሰቦቻቸዉም መጽናናቱን ያብዛላቸው እላለሁ።

በወገኖቻችን ላይ የደረሰን ጭካኔ አጥብቄ እያወገዝኩ ፣ የአገዛዙ ታጣቂዎች ተቃዉሞ ከሚሰማባቸው ቦታዎች በአስቸኩዋይ እንዲወጡ እጠይቃለህ። መንግስት ገዳዮችን፣ ትእዛዝ የሰጡትን ለፍርድ እንዲያቀርብና ጉዳት ለደረሰባቸው አስፈላጊውን ካሳ እንዲሰጥ እጠይቃለሁ። ገዢዎች የሕዝብን መሰረታዊ ጥያቄ በማናናቅ፣ በሚቆጣጠሩት ሜዲያ በሕዝብ ላይ የሚያሰሙት ዛቻ፣ ማስፈራራት ፣ ስድብ አቁመው፣ ለሕዝብ መሰረታዊ የመብት፣ የነጻነት የፍትህና የመሬት ባለቤትነት ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡ እጠይቃለሁ።

እኔን ጨመሮ በርካታ ዜጎች በሰላም ሐሳባችንን በመግለጻችን ሽብርተኞች ተብለን፣ ፍትህ ተነፍገን በግፍ ታስረናል። ነጻ ጋዜጦች ተዘግተዋል። በሌሎች አገሮች የእንስሳት መብቶች ሲከበሩ፣ በኛ አገር ግን ለሰብእና ክብር አይሰጥም። ዜጎች በአገራቸው ፈርተዉና ተሸማቀው ነው የሚኖሩት። ብዙዎች ተስፋ ቆርጠው ስደትን መርጠዋል። በልማት ስም ጥቂቶችን ለመጥቀም፣ ገበሬዎች ከእርሻቸው ይፈናቀላሉ። “ከዚህ ብሄረሰብ ናችሁ፣ የናንተ መሬት አይደለም” ተብለው ብዙዎች የዘር ማጽዳት ወንጀል ይፈጸምባቸዋል። በጎንደር ለምለም የአገራችን መሬት፣ ሕዝብ ፓርላማው ሳያውቀው ሊሰጥ እንደሆነ እየሰማን ነው። አገር በ 11% አድጋለች እየተባለ፣ አሥር ሚሊዮኖች ለረሃብ ተጋልጠዋል። ይሄ ሁሉ መቆምና መስተካከል አለበት። “ኢሕአዴግ ልብ ይበል ፤ 
የጥፋት እጆቹን ይሰብሰብ ፣ ሕዝብን ያክብር፣መሰረታዊ የፖለቲካ ሪፎርም ያድርግ፣ ለብሄራዊ መግባባት ራሱን ያዘጋጅ” እላለሁ።


ነጻነትን ለተጠሙ፣ ፍትህን ለተራቡ ኢትዮጵያዊያን መልእክት አለኝ። ነጻነት፣ ፍትህ ከሌሎች በስጦታ የሚሰጠን አይደለም። ነጻነትና ፍትህ እኛው ራሳችን ታግለን የምናገኘው ነው። በመሆኑም የአገሪቱዋ ሕገ መንግስት እና አለም አቀፍ ሕጎች በሚፈቅዱት መሰረት፣ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጻችንን እንድናሰማና ትግሉን እንድንቀላቀል ጥሪ አቀርባለሁ። ግፍ ሲፈጸም ዝምታን ከመረጥን እንደ አገር እንጠፋለን። የአንዱ ሕመም እኛንም ሊያመን ይገባል። እንተባበር፣ እንደራጅ፣ በጋራ፣ በማያዳግም ሁኔታ፣ “በኢትዮጵያችን ከዚህ በሁዋላ በግፍ ደም መፈሰስ የለበትም” እንበል። አሁንስ በቃን !!!!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49378

Saturday, December 19, 2015

‹‹ኃብታሙ አያሌው ላይ በጤንነቱ የተነሳ ለሚደርስ ችግር›› ሐኪሞቹ ‹‹ኃላፊነት አንወስድም›› አሉ

                        ኃብታሙ አያሌው


የቀድሞው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግኑኝነት ሐብታሙ አያሌው ከማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ቆይታ አንስቶ እያሰቃየው የሚገኘውን የኩላሊት ህመሙን ከብዙ ንትርክ በኋላ በዘውዲቱ ሆስፒታል እንዲታከም የተደረገ ቢሆንም የሐብታሙን ህክምና በመከታተል ላይ የሚገኙ ሐኪሞች ኩላሊቶቹ ከፍተኛ ክትትል የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ሐብታሙ በሆስፒታሉ አልጋ በመያዝ አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ እንደሚገባው ያዛሉ፡፡

እንደ ሆስፒታሉ የመረጃ ምንጮች ከሆነም ሐብታሙን ታህሳስ 5 ቀን 2008 በዘውዲቱ ሆስፒታል የመረመሩት ዶክተሮች የምርመራቸውን ውጤት ከተመለከቱ በኋላ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት ከሌሎች ሶስት የኩላሊት ህክምና ስፔሻሊስቶች ጋር በመመካከር ቢሆንም የህሊና እስረኛውን ለህክምና ምርመራ ያመጡት የወህኒ ቤቱ ፖሊሶች ሐብታሙን ‹‹አሳይታችሁ አምጡት››ተብለናል በማለት መልሰው ወስደውታል፡፡


በሆስፒታሎች አልጋ ይዘው እንዲታከሙ በዶክተሮች የሚታዘዙ እስረኞች በፖሊስ እንዲጠበቁ ተደርገው አልጋ የሚይዙ ቢሆንም ሐብታሙ ጤንነቱ አሳሳቢ መሆኑ እየተነገራቸው ህክምናውን አቋርጦ እንዲሄድ አድርገውታል፡፡


በዚህ ወቅት በፖሊሶቹ ውሳኔ የተበሳጩ ዶክተሮች ‹‹በጤንነቱ የተነሳ አንዳች ችግር ቢፈጠርበት እኛ ኃላፊነት አንወስድም፡፡እናንተም የባለሞያ ምክራችንን ትታችሁ ህመምተኛውን መውሰዳችሁን ፈርሙልን››በማለት ጥያቄ ቢያቀርቡላቸው ለመፈረም ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በመግለጽ ወስደውታል፡፡


ሐብታሙ፣አብርሃ፣የሺዋስና ዳንኤል ዛሬ በቀረቡበት ፍርድ ቤት የተሰየሙት የመሐል ዳኛ ጉዳያቸውን የመመልከት ሞያዊም ሆነ ስነ ምግባራዊ ብቃት እንደሌላቸው በመጥቀስ እንዲነሱላቸው መጠየቃቸው ተነግሯል፡፡


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49259

Tuesday, December 15, 2015

የህወሓቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በጎንደር ከፍተኛ ተቃውሞ ደረሰባቸው


ከአዲስ አበባ ጎንደር የገቡት የአገዛዙ ባለስልጣናት የህወሓቱ አባይ ፀሀዬ፣ የህወሓት ተላላኪ የሆነው ብአዴን ቁንጮዎች በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ ናቸው፡፡ የክልሉ ሹም ገዱ አንዳርጋቸውም በአጃቢነት ተገኝቷል፡፡

አባይ፣ በረከትና አዲሱ በትናንትናው ዕለት የዞኑን ካቢኔ አባላትና ጥቂት የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ የከተማው ነዋሪዎችን በጎሃ ሆቴል ሰብስበው በጎንደር ስለሰፈነው አለመረጋጋት፣ አመፅና ጦርነት ለማነጋገር ሞክረው “ይህ ሁሉ ችግር ከደረሰና ሁኔታው ከቁጥጥር ውጭ ከሆነ በኋላ ምትመጡ እስከ ዛሬ የት ነበራችሁ? የህዝብ ቁጣ ጫፍ ደርሷል አሁን እናንተ መጣችሁ አልመጣችሁ የምትፈይዱት ቅንጣት ታክል ነገር የለም…” የሚል ምላሽ ያለበት ከወትሮው ለየት ያለና ጠንካራ ተቃውሞ ከተሰብሳቢው ተሰንዝሮባቸዋል፡፡ በተለይም በባለስልጣናቱና በካቢኔው መካከል የተፈጠረው እሰጣገባና ንትርክ ወደ ከረረ ያለመግባባት ውስጥ እንደከተታቸው ታውቋል፡፡


እነበረከትና አባይ የጎንደርን ነዋሪዎች በየክፍለ ከተማው ሰብስበው ለማነጋገር መድረክ እንዲያመቻቹላቸው የዞኑን ካቢኔ አባላት ጠይቀው የካቢኔ አባላቱ በአሁኑ የትኩሳት ወቅት ህዝብ መሰብሰብ ከአቅማቸው በላይ እንደሆነ እና ባለስልጣናቱ ራሳቸው ወርደው ያሻቸውን ማድረግ እንደሚችሉ ቁርጥ ያለ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡


በመሆኑም እነ በረከትና አባይ ፀሀዬ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ ወድቀው የሚያደርጉት ጭንቅ ጥብብ ብሏቸው አሁንም በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ይገኛሉ፡፡


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49153

መድረክ ባለ 6 ነጥብ መግለጫ አወጣ | “ሕዝቡ በጉልበትና በማጭበርበር የተቀማውን መብት ለማስመለስ በሰላማዊ መንገድ ይታገል”

የሕዝቦችን ሕገመንግሥታዊ መብቶች በመጣስ የሚከናወኑ የኢህአዴግ ሕገወጥ እርምጃዎች ሕዝባችንን ለከፍተኛ ችግር፣ ሀገራችንንም ለአሳሳቢ ሁኔታ እየዳረጉ ስለሆነ በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል!!
(ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ የተሰጠ መግለጫ)
የኢህአዴግ አገዛዝ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ በተግባር ሊያውላቸው ያልተዘጋጀባቸውን ድንጋጌዎች ከሀገሪቱ ሕገመንግሥት ጀምሮ ሲያውጅ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ያወጃቸውን ድንጋጌዎች በማፍረስና በተግባር እንዳይውሉ በማድረግ የዜጎችንና የሕዝቡን መብቶች የሚጥሱ ተግባራትን እየፈጸመ ይገኛል፡፡ ይህ ሁኔታ ከአንድ የሕዝብን የሥልጣን ባለቤትነት በጉልበትና በማጭበርበር ቀምቶ መንግሥት ነኝ ከሚል አምባገነን ቡድን የሚጠበቅ ቢሆንም፣ መዘዙ የሀገራችንን ደህንነትና የሕዝቦቻችንን እኩልነትና አንድነት ለማይሹ ኃይሎች አፍራሽ እንቅስቃሴ ቀዳዳ እየሰጣቸው መሆኑ መድረክን በእጅጉ ያሳስበዋል፡፡
ከእነዚህ ሕገመንገሥታዊ ድንጋጌዎች ጥሰት መነሻነት ከተፈጠሩት ውስብስብ ችግሮች ውስጥ አንዱ የአዲስ አበባ ከተማንና የኦሮሚያን ክልላዊ መንግሥት ግንኙነት በሚመለከት፣ በሕገመንግሥቱ አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 5 “የኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አቅርቦት ወይም የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምንና የመሳሰሉትን ጉዳዮች በተመለከተ እንዲሁም አዲስ አበባ በኦሮሚያ ክልል መሐል የሚገኝ በመሆኑ የሚነሱ ሁለቱን የሚያስተሳስሩ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ያለው ልዩ ጥቅም ይጠበቅለታል” የሚለውን በማንአለብኝነት ከመጣስ የመነጨ ችግር ነው፡፡ በዚህ ረገድ የኢህአዴግ ሥርዓተ-አልበኝነት መገለጫ ሆኖ የቆየው በሕገመንግሥቱ የሰፈረው ዝርዝር የአፈጻጸም ሕግ ሳይወጣ ከ21 ዓመታት በላይ መቆየቱ ተጠቃሽ ነው፡፡ እንዲሁም በአዲስ አበባ አከበቢ የሚሠሩ የልማት ሥራዎችንም በሚመለከት ሕዝቡን በአግባቡ ሳያወያዩ ጥቂት እበላ ባይ ካድሬዎችን በአስፈጻሚነት በማሰማራት የእርሻ መሬታቸውን እየነጠቁ ወደ አዲስ አበባ ከተማ የማካለል እንቅስቃሴ ላይ መሠማራቱ በተከታታይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችንና ውዝግቦችን ከማስነሳቱም በላይ ለብዙ ዜጎች ሕይወት በኢህአዴግ መንግሥት አርመኔአዊ እርምጃ መቀጠፍ ምክንያት ሆኖአል፡፡
ባለፉት ሁለት ሳምንታት የአዲስ አበባ ከተማን ከሕግ አግባብ ውጪ ማማስፋት ጋር በተያያዘ በሕዝቡ ዘንድ ካደረው ስጋት በመነሳት የተቀሰቀሰውን ሰላማዊ ሕዝባዊ ተቃውሞን በኃይል ለማስቆም የኢህአዴግ መንግሥት በወሰደው እርምጃም በርካታ ተማሪዎችና ሌሎች ዜጎች መገደላቸውን መድረክ በእጀጉ ይኮንነዋል፡፡


የተገደሉት ዜጎችም

1ኛ፡- ተማሪ ካረሳ ጫላ ምዕራብ ወለጋ ጉልሶ ወረዳ፣
2ኛ፡- ተማሪ ጉቱ አበራ ምዕራብ ወለጋ ጉልሶ ወረዳ፣ 3ኛ፡- ተማሪ ሚፍታህ ጁንዲ በምዕራብ ሐረርጌ በደኖ ወረዳ፣
4ኛ፡- ተማሪ ገዘሃኝ ኦልሂቃ የሀራማያ ዩንቨርሲቲ ተማሪ፣
5ኛ፡- ተማሪ ደጀኔ ሰርቤሳ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ቶሌ ወረዳ፣
6ኛ፡- ተማሪ በቀለ ሰቦቃ አዳበርጋ ወረዳ ሙገር፣
7ኛ፡- ተማሪ በቀለ ሰይፉ አዳበርጋ ወረዳ ሙገር፣
8ኛ፡- ተማሪ ሙራዲ አብዱ የሀራማያ 2ኛ ደረጃ ተማሪ፣
9ኛ፡- አቶ ጫላ ተሾሜ ምዕራብ ሸዋ ጨለያ ወረዳ ባቢቻ ከተማ፣
10ኛ፡- ተማሪ አብደታ ባይሳ ምዕራብ ሸዋ ጫለያ ወረዳ ባብቻ ከተማ፣
11ኛ፡- ተማሪ ዱሌ ምዕራብ ሸዋ ጨለያ ወረዳ ጌዶ ከተማ፣
12ኛ፡- አቶ ታመነ ጸጋዬ ምዕራብ ሸዋ ጨለያ ወረዳ ጌዶ ከተማ፣
13ኛ፡-ተማሪ ደረጀ ጋዲሰ ምዕራብ ሸዋ ጨለያ ወረዳ ጌዶ ከተማ፣
14ኛ፡- ተማሪ ፈቃዱ ግርማ ምዕራብ ሸዋ ጨለያ ወረዳ ጌዶ ከተማ፣
15ኛ፡-ተማሪ ሉጫ ገማቹ ምዕራብ ወለጋ ኢናንጎ ወረዳ፣
16ኛ ተማሪ አያና ባንቲ ምዕራብ ወለጋ ኢናንጎ ወረዳ፣
17ኛ፡- ተማሪ አላዛር ምዕራብ ወለጋ ኢናንጎ ወረዳ ነዋሪ
18ኛ አቶ ኤብሰ ቱጆ ሆሮ ጉዱሩ ፍንጫ፣
19ኛ፡- አቶ ደበላ ጣፋ ጫንጮ ላይ ተገድሎ ተጥሎ የተገኘ፣
20ኛ ወ/ሮ ዲሶ ሚሊኬሳ ሕልፈታ ወረዳ
21ኛ፡- አቶ አበበ ቡሎ ወሊሶ ከተማ፣
22ኛ፡- አቶ ታዴ ሰፈራ አመያ ከተማ፣
23ኛ፡- አቶ ሌንጮ ሁንዴራ ወሊሶ ከተማ፣
24ኛ፡- አቶ ሰለሞን ሞገስ አማያ ከተማ፣
25ኛ፡- አቶ ታዴ አንዲሳ ወንጪ ከተማ፣
26ኛ፡- አቶ እናውጋው ኃይሉ ግንደበረት ወረዳ፣
27ኛ፡- ተማሪ አብደታ ለታ ግንደበረት ወረዳ
28ኛ፡-አቶ ባይኢሳ ገደፋ አቡና ግንደበረት
ወረዳ 29ኛ፡- ተማሪ አስቻለው ወርቁ ግንጪ ወረዳ፣
30ኛ፡- ተማሪ ሰይፉ ቱራ ግንጪ ወረዳ፣
31ኛ፡- ተማሪ አሸናፊ ግንጪ ወረዳ፣
32ኛ፡- አቶ ገላና ባቃና ጪቱ ከተማ ነዋሪ የነበሩ ስለመሆናቸው የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ከዚህም ሌላ ከመቶ ባለይ ዜጎች ቆስለዋል፣ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለእስራት ተዳርገዋል፡፡ ሰላማዊና ሕጋዊ ተቃውሞን ለማፈን በመንግሥት እየተወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ እስከ አሁንም እንደቀጠለ በመሆኑ፣ በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት መድረክን በእጅጉ እያሳሰበው ይገኛል፡፡ እንደዚሁም በቅርቡ በጎንደር ከተማ በሚገኘው ወሕኒ ቤት በእስረኞች ላይ የተፈጸመው ግዲያ መድረክን አሳስቦታል፡፡
ከዚህም ሌላ በሕገመንግሥቱ አንቀጽ 40 ንዑስ አንቀጽ 4 ላይ “የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬት በነፃ የማግኘትና ከመሬታቸው ያለመነቀል መብታቸው የተከበረ ነው” የሚለውንና በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 5 የኢትዮጵያ አርብቶ አደሮች ለግጦሽም ሆነ ለእርሻ የሚጠቀሙበት መሬት በነፃ የማግኘት፣ የመጠቀምና ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብት አላቸው” ተብሎ የተደነገገውን በመተላለፍ፣ በከተሞችና በእንቨስትመንት ማስፋፋት ስም የአርሶ አደሮችንና አርብቶ አደሮችን መሬት እየቀሙ በማፈናቀል ለከፍተኛ የኑሮ ችግሮች እየዳረጉዋቸው ይገኛሉ፡፡ መድረክ ይህንን የኢህአዴግ መንግሥት የመሬት ቅሚያ እርምጃ ደጋግሞ ሲያጋልጥ የቆየ ሲሆን በእርምጃው ምክንያት በሕዝቡ ላይ እያደረሰ ያለው የጉዳት መጠን ከጊዜ ወደጊዜ በአሁኑ ወቅት እየሰፋ ስለመገኘቱ መረጃዎች ያሳያሉ፡፤
በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አገዛዙ በርካታ የሀገሪቱን ከተሞች ለማስፋፋትና መሬቱንም በፌዴራል መንግሥት ቁጥጥር ሥር በመሬት አስተዳደር ኮርፖሬሽን ለማስተዳደር፣ የማስተር ፕላንና የሪፎርም ከተሞች ብሎ በመሰየም፣ በየከተሞቹ አከባቢዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮች ይዞታዎች አርሶ አደሩን ሳያማክሩና ተገቢውን ካሳ ሳይከፍሉ ወደ ከተማ ለማካለል እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ነዋሪውን ሕዝብ ለከፍተኛ ስጋትና ጭንቀት እየዳረጋቸው ይገኛል፡፡ ስለሆነም የኢህአዴግ አገዛዝ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ አንስቶ በማንአለብኝነት አምባገነናዊ ስሜት እየተመራ ፌዴራላዊ ሥርዓቱንና የዜጎችን ሕገመንግሥታዊ መብቶች በመጣስ እየፈጸመ ከሚገኘው ሕገወጥ ተግባር እንዲቆጠብ እንጠይቃለን፡፡ በተለይም፡-


1ኛ፡- ከአዲስ አበባ ከተማና ከኦሮሚያ ክልል ግንኙነት ጋር በተያያዘ እየተከሰቱ ያሉ ችግሮች ሕገመንግሥቱን ተግባራዊ ባለማድረግ ምክንያት እየተከሰቱ ስለሆኑ የሕገመንግሥቱን አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 5 ተግባራዊ የሚያድርግ ሕግ በአስቸኳይ ወጥቶ ተግባራዊ እንዲደረግና ለችግሩ ዘላቂ እልባት እንዲሰጥ፣ ለከተማዋ ልማት የሚወጡ እቅዶችም የሕገመንገሥቱን ድንጋጌ የሚያከብሩ ሆነው የአከባቢውን አርሶ አደሮች መብትና ጥቅም በሚገባ የሚያስጠብቅ እንዲሆኑ፣


2ኛ፡- በቅርቡም መንግሥት ሕገወጥ እርምጃ ለመውሰድ በተንቀሳቀሰበት ምክንያት በኦሮሚያ ክልል ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎችን ባደረጉና በሌሎችም ሰላማዊ ዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው የኃይል እርምጃ በአስቸኳይ እንዲቆም፣


3ኛ፡- እስከአሁን የዜጎችን ሕይወት በሕገወጥነት ያጠፉና ሌሎች ጉዳቶችን ያደረሱ የመንግሥት አካላትም ለሕግ እንዲቀርቡና ለሟቾቹ ቤተሰቦችም ተገቢው ካሳ እነዲከፈላቸው እንዲደረግ፣


4ኛ፡- በመላ ሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ሕገመንግሥቱ ያረጋገጠላቸው ከመሬታቸው የያለመፈናቀል መብታቸው ተከብሮ፣ በየአከባቢያቸው በልማት ሥራዎች ሰበብ ኑሮአቸው እየተናጋ ለችግር የሚዳረጉበት ሁኔታ በአስቸኳይ ተወግዶ፣ የሚከናወኑት የልማት ሥራዎችም ቢሆኑ የአከባቢውን ሕዝብ ይሁንታ ያገኘና መብታቸውን የጠበቀ እንዲሆን እንዲደረግ፤

5ኛ፡- በተለይም በአሁኑ ወቅት ከተሞችን በማስፋፋት ስም የአርሶ አደሩን መሬቶች ወደ ከተማ ለማካለልና በከፍተኛ ዋጋ በሊዝ ለመሸጥ የሚደረገው እንቅስቃሴ፣ አርሶ አደሩን በስጋት ውስጥ እየከተተው ስለሚገኝ፣ ኑሮአቸውን ለማሻሻል የሚበቃ በቂ ካሳ ሳይከፈል ይዞታቸውን ለመንጠቅ የሚደረገው እንቅስቃሴ እንዲቆም እንዲደረግ፣


6ኛ፡- በቅርቡ በጎንደር ከተማ በሚገኘው ወሕኒ ቤት የተገደሉ በርካታ ዜጎች ጉዳይ በአስቸኳይ ተጣርቶ የሰላማዊ ዜጎችን ሕይወት ያጠፉና ጉዳት ያደረሱ አካላት ለፍርድ እንዲቀርቡና ለሟቾቹ ቤተሰቦችም ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው እንዲደረግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡

በመጨረሻም መድረክ በንጽሐን ዜጎቻችን ላይ በኢህአዴግ መንግሥት የተወሰደውንና እየተወሰደ ያለውን ኢሰብአዊ ግዲያ በጥበቅ እያወገዘ ለሟቾቹ ቤተሰቦች መጽናናትን ይመኛል፡፡ መላው ሕዝባችንም በኢህአዴግ በጉልበትና በማጭበርበር በተካሄዱት ምርጫዎች የተቀማውን ሕገመንግሥታዊ መብቶቹን ለማስከበር ሰላማዊ ትግሉን እንዲያጠናክር የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ጥሪ ያቀርባል፡፡


ድል ለሕዝባዊ ትግላችን !!
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ
ታህሳስ 5 ቀን 2008 ዓ ም
አዲስ አበባ


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49137

Monday, December 14, 2015

ሕዝብን ለመጨፍጨፍ እየዘመተ ያለው ጦር


በነሶሞራ የሚመራው እዝ፣ ህዝብን ለመጨረስና በሃይል አንገትን ለማስደፋት ሁለት ዲቪዝን ጦር ወደ ምራብ ሸዋና ወለጋ እየወሰደ ነው። ይህ አይነቱ እንቅስቃሴ አገዛዙ ሊወስደው የሚችለው የመጨረሻ ተግባር ነው። ጎንደር ላይ ከሰፈረው ጦር በተጨማሪ ወደ ኦሮሚያ እየተሰማራ ያለው ሲደመርበት በሌሎች ከተሞች የሚኖረው ጦር በጣም የተመናመነ ነው።

በመሆኑም በአዲስ አበባ. በጎጃም፣ በወለኦ፣ በሰሜን ሸዋ፣ እና በደቡብ ክልል ሕዝቡ ለነጻነትና ለመብት ድምጹን ማሰማት ቢጀመር ይሄ ስርዓትን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመገርሰስ አመቺ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሎ ይገመታል።
በመሆኑም ሌላው ማሀበረሰብ ድምጹን ያሰማ ዘንድና በኦሮሚያና በጎንደር ለመብታቸው ከቆሙ እየተገደሉ ካሉ ወገኖቻችን ጎን እንዲቆም ያስፈልጋል።

እስከ አሁን በጎንደር ከ150 በላይ ዜጎንች የተገደሉ ሲሆን በኦሮሚያ የዛሬን ቀን ሳይጨመር ከሰባ በላይ ሕይወታቸው አልፏል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49101

Thursday, December 10, 2015

የኖርዌይ ኢምባሲ ዜጎቹ ወደ ጎንደርና ኦሮሚያ የተጠቀሱ ከተሞች እንዳይሄዱ መከረ


(ዘ-ሐበሻ) አዲስ አበባ የሚገኘው የኖርዌይ ኢምባሲ በጎንደር እና በኦሮሚያ ባለው አለመረጋጋት የተነሳ ዜጎቹ በሁለቱ ክልሎች በተመረጡ አካባቢዎች እንዳይሄዱ አስታወቀ::

ከኖርዌይ ኢምባሲ የአዲስ አበባ ድረገጽ ዘ-ሐበሻ ያገኘችው መረጃ እንደሚጠቁመው በጎንደር ባለፈው ሳምንት በ እስር ቤት ላይ የደረሰው ቃጠሎን ጉዳይ አንስቶ በአሁኑ ወቅት በታች አርማጭሆ; በም ዕራብ አርማጮና ጭልጋ አካባቢ ጦር የታጠቁ ኃይሎች እንቅስቃሴ እያደረጉ በመሆኑ ወደዚያ አካባቢ ለመሄድ ለደህነነት አስጊ በመሆኑ ዜጎቹ እንዳይሄዱና ከነዚህ አካባቢዎች እንዲርቁ መክሯል::

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተጀመረው ተቃውሞ አደባባይ ከወጣ እና ፖሊስ እና ተማሪዎችም ከተፋጠጡ በኋላ በተለይ በአምቦ እና በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተቃውሞው እጅጉን በማየሉ የኖርዌይ ዜጎች ወደዚያ አካባቢ እንዳሄዱ አስጠንቅቋል::


በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ የተረጋጋና ያልታሰበ ነገር ሊከሰት እንደሚችል ያስታወቀው ኢምባሲው ዜጎቹ ወደዚያው እንዳይሄዱ ከሄዱና አንድ ችግር ካጋጠማቸውም ቶሎ ለኢምባሲው ሪፖርት እንዲያደርጉ አስጠንቅቋል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48924


Saturday, December 5, 2015

ትግሬው ድርጅት ብአዴን ተጨማሪ 5ሚሊዮን አማሮችን ከምድረ ገጽ የማጥፋት ዕቅዱን ይፋ አደረገ

ተጨማሪ መሬቶችንን ለትግሬና ለሱዳን መስጠትና የሚፈናቀለው ህብረተሰብ በርሀብ እንዲያልቅ ማድረግ በዕቅዱ ተካትዋል!!

በ35ኛው የሙት አመት ዝክር ላይ የተወያየው የጠላት ትግሬ ቡድን ብአዴን የእስካሁኑ የ5ሚሊዮን አማሮች ከምድረ ገጽ መጥፋት አንጸባራቂ ድል ብሎታል።የተጨማሪ የ5ሚሊዮን አማሮች እልቂት የሚፈጸምበትን የማስፈጸሚያል ስልት በዝርዝር ያስቀመጠው ጠላት ድርጅት ብአዴን ለተግባራዊነቱ እንረባረባለን ሲል መግለጫ አውጥትዋል።የዘር ማጥፋቱ የማስፈጸሚያ ስልት እንደሚከተለው ቀርብዋል።
1.የሚያመክኑ መድሀኔቶችን በወሊድ መቆጣጠርና ክትባት ሽፋን በብዛት ማሰራጨትና እንዲጠቀሙ ማድረግ።
2.ህዝቡን በመከፋፈል በሚፈጠረው ግጭት የአማሮች እልቂት እንዲከሰት ማድረግ
3.በኢንቨስትመንት ሽፋን ትግሬዎችን በማስፈር አማሮችን በማፈናቀል በርሀብ እንዲያልቁ ማድረግ።
4.የበሽታ ወረርሽኝ እንዲከሰት በማድረግ የህክምና አገልግሎት እንዲዘገይ በማድረግ እልቂት እንዲፈጸም ማስቻል።
5.የአማራ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ የግብር ጫና በመጣል ከውድድር ውጪ እንዲሆኑና ጠላት ትግሬ እንዲቄጣጠር ማድረግ ፣እንዲሁም በአብቁተ አማካኝነት አርሶ አደሩ እዳ ውስጥ እንዲዘፈቅ ማድረግ።
6.የውሸት ክሶችን በመፍጠር አማሮች እንዲታሰሩና እንዲገደሉ ማድረግ።
7.ከዚህ በፋት በማብቃትና በቢ.ፒ.አር .እንደተደረገው በአማራው መንግስት ሰራተኛ ላይ የሚያሸማቅቁና ሞራልን የሚሰብሩ አስጨንቀው ለበሽታ የሚዳርጉ ግምገማዎችንን በማካሄድ የህብረተሰቡ ሞራል እንዲላሽቅ ማድረግ ይህ በጥላቻና ሞራል በሚነኩ ዘለፋዎች የታጀበ ነው።
8.ተጨማሪ መሬቶችንን ለትግሬና ለሱዳን መስጠትና የሚፈናቀለው ህብረተሰብ በርሀብ እንዲያልቅ ማድረግ።
9.ተምሮ የሚመረቀው የአማራ ወጣት ተመሮ ስራ እንዳያገኝና በራሱ ተስፋ እንዲቆርጥ ማድረግ።
10.ተካታታ የጥላቻ ዘመቻዎችን በማድረግ ሌሎች ህብረተሰቦች እንዲያገሉት ማድረግ ።እነዚህ በዝርዝር የቀረቡት ዋና ዋና የማስፈጸሚያ ስልቶች ናቸው ተፈጻሚነታቸውም በሚስጥር እንደሚሆን ከጠላት ትግሬ ድርጅት ብአዴን ተገልጽዋል በተጨማሪም ዕቅዱ የትግሬን የበላይነት በአተማማኝ ሁኔታ ለማስቀጠል እንደሚረዳ ተገልጽዋል።

http://www.satenaw.com/amharic/archives/11021