Thursday, May 3, 2018

ኦዶ ሻኪሶ: ወርቅ ‘መርዝ’ የሆነባት ምድር (BBC)

ወ/ሮ ሑጤ ደንቆ የሁለት ልጆቻቸው ሞት እንዲሁም የሴት ልጃቸው አካል መጉደል ካደርሰባቸው የሐዘን ስብራት ጋር በጉጂ ዞን ኦዶ ሻኪሶ ወረዳ ዲባ በቴ ቀበሌ ውስጥ ይኖራሉ። እኚህ እናት የመጀመሪያ ልጃቸውን ሁለት እግሯን አልታዘዝ ከማለት በተጨማሪ በኋላ የወለዷቸው ወዲያውኑ እንደተወለዱ ሞተውባቸዋል።
ወ/ሮ ሑጤ ነፍሰጡር በነበሩበት ወቅት ከባድ የጤና እክል አጋጥሟቸው የነበረ ቢሆንም አሁንም የአጥንት ሕመም ህይወታቸውን አቀበት አድርጎባቸዋል። የእሳቸውን እና የልጆቻቸውን ጤንነት ይከታተሉ የነበሩ የህክምና ባለሙያዎች የእሳቸው አጥንት ህመምም ሆነ የልጃቸው እግር አጥንት መልፈስፈስ ምክንያቱ ከፋብሪካው የሚወጣው መርዛማ ኬሚካል መሆኑን እንደነገሯቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል። ወ/ሮ ሑቴ የሚኖሩበት ዲባ በቴ ቀበሌ የሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኃላ.የተ.የግ.ማኅበር ለገደንቢ ወርቅ ማምረቻ የሚገኝበት ነው። “ነፍሰጡር ሴቶች ያስወርዳቸዋል፤ ሕፃናት ሲወለዱ ያለጭንቅላት ይወለዳሉ። ጭንቅላታቸው መጠኑ በጣም ያነሰ ነው። እጅና አይናቸውም ተጎድቶ ይወለዳሉ። ሰው ታሞ ወደ ሐኪም ቤት ሲሄድ ከ ‘ነርቭ’ ጋር የተያያዘ ችግር ነው ይባላል።” በማለት የቀበሌው ነዋሪ የሆኑት አቶ ዱቤ ጋሸራ ሚጁ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በዚሁ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት እኚህ አዛውንት “ድሮ ይህንን የሚመስል ችግር አልነበረም”ይላሉ።
“መንግሥት የወጣቱን ቅሬታ ከመስማት ውጭ ምንም የለወጠው ነገር የለም።”
ዓይናቸው ከማምረቻው ውስጥ በሚወጣ ኬሚካል መጎዳቱን እንዲሁም በአግባቡ ቆመው መሄድ እንደሚያቅታቸው ነግረውናል። በተጨማሪም ከዚሁ ችግር የተነሳ በከብቶች እና በዱር እንስሳት እየደረሰ ያለው እልቂት ለትልቅ ችግር አጋልጦናል ይላሉ።
‘ሳናይድ’ እና የአካል ጉዳተኝነት
የሚድሮክ ለገደንቢ የወርቅ ማምረቻ ወርቅና ነሐስ በሚያመርትበት ወቅት ወርቁን ለማፅዳት የሚጠቀምበት ኬሚካል ‘ሳናይድ’ ይባላል። ይህ ኬሚካል ራስ ምታት፣የልብ፣ የአእምሮ እና የነርቭ ህመሞች እንደሚያስከትል የኦዶ ሻኪሶ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጦና ዋሬ ነግረውናል። ከዚህም ባሻገር የሰው አጥንት ለማጠንከር የሚረዱ እንደ ብረት(አይረን) ያሉ ንጥረ ነገሮች ከሰው እና ከእንስሳት አካል ውስጥ መጠኑን ይቀንሳል።
ይህም ለአጥንት መሳሳት እና መሰባበር እንደሚያጋልጥ አቶ ጦና ዋሬ ያስረዳሉ። የወርቅ ማምረቻው የሚገኝበት ዲባ በቴ ቀበሌ ውስጥም የአካል ጉዳተኝነት ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ነው።

የቢቢሲ ሪፖርተር በአካል በቀበሌው ተገኝቶ አንድ ኪሎ ሜትር ባልሞላ መንደር ውስጥ ሶስት የአካል ጉዳት ያለባቸው ህፃናትን አይቷል። በህፃናት ላይ የሚደርሰው የአካል ጉዳት በቀበሌው ውስጥ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ ነዋሪዎች ወልደው ለመሳም እየተሳቀቁ እንደሆነ ይናገራሉ። ወ/ሮ ደምበሊ ሔጦ የአካል ጉዳት ያለባት ህፃን አላቸው፤ “ልጆቼ በታመሙ ቁጥር ስጋት ያድርብኛል። ሌላ ተጨማሪ ልጅ ለመውለድ እንደዚሁ ልጅ ይሆንብኝ ይሆን ስል እሰጋለሁ” ይላሉ። በተጨማሪም ነፍሰጡር ሴቶች ልጃቸውን ወልደው ከአካል ጉዳት ነፃ መሆኑን እስኪያረጋግጡ ድረስ ማርገዛቸውን እንደሚደብቁ፣ የአካል ጉዳት ያለበትን ህፃን የወለዱ እናቶችም ከሰው አይን ከልለው በቤት ውስጥ ደብቀው እንደሚያሳድጓቸውም የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
በተጨማሪም የሳይናይድ ኬሚካል የተቀላቀለበት ወራጅ ውሃ የሚጠጡ እንስሳት ወዲያውኑ እንደሚሞቱ፣ የተበከለ አየር ውስጥ የሚቆዩት ደግሞ ከወደቁ በኋላ መነሳት እንደማይችሉ፣ አጥንታቸውም በቀላሉ እንደሚሰበር የአካባቢው ነዋሪዎች ያስረዳሉ።
“ድጋሚ ተመሳሳይ ችግር ይደርስብኝ ይሆን ብዬ እሰጋለሁ።”
የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች
የፋብሪካው የጥበቃ ሰራተኞች በህብረተሰቡ ላይ ልዩ ልዩ ችግሮችን እንደሚያደርሱ ቅሬታዎች ይሰማሉ። ይህንን ቅሬታ ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆኑ የወረዳው አስተዳደር ሰራተኞችም ይጋሩታል። ለፋብሪካው ከሚደረገው ከፍተኛ ጥበቃ የተነሳ መንግስት በሰጣቸው ኃላፊነት ተጠቅመው በፋብሪካው ውስጥ ገብተው የቁጥጥር እና ክትትል ስራ ማድረግ እንዳልቻሉ የኦዶ ሻኪሶ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ቦሬ ጦና ይናገራሉ። ሰራተኞችንም በሚቀጥሩበት ወቅት ህጉ በሚያዘው መሰረት እንደማያሳትፏቸወው ከድርጅቱ የሚያገኙት ምላሽም “እኛ በእናንተ ሳእሆን በፌደራል መንግስት ነው የምንመራው” የሚል እንደሆነም ይናገራሉ። የስራ እድል ማግኘትን ጨምሮ በወረዳው ውስጥ ከሚገኙ የማእድን አምራች ድርጅቶች ጥቅም እያገኘን አይደለም፤ ከዚህም አልፎ ችግር እየደረሰብን ነው በማለት የወረዳው ነዋሪዎች በተለያየ ጊዜ ሰልፍ ወጥተዋል። ምላሽ የአካባቢውን ነዋሪዎች እና ባለስልጣናት ቅሬታ መልስ ለማግኘት ወደ ማእድን ማምረቻው በሄድንበት ወቅት የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት መልስ የሚሰጡን የስራ ኃላፊዎች እንደሌሉ ነግረውናል። ነገር ግን ይህ ፅሁፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ከወጣ በኋላ ሚድሮክ ለቢቢሲ በፃፈው ደብዳቤ ጉዳቱን አላደረስኩም ብሏል።
የሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኃላ.የተ.የግ.ማኅበር የለገደንቢ ወርቅ ማምረቻ ሳናይድ የተባለው ኬሚካል በሕዝብና በአካባቢ ላይ ጉዳት አለማድረሱን በደብዳቤው ገልጿል። በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን አዶ ሻኪሶ ወርቅ በማምረት የተሰማራው ይህ ኩባንያ አካባቢውን በጠበቀና ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ እየሰሩ መሆኑንም ጭምር ገልፀዋል።
“በአካባቢ ላይም ሆነ በሰዎች ላይ ከኬሚካል ጋር ተያይዞ የተፈጠረ ችግር የለም” ብሏል።
ሚድሮክ በአካባቢው የተባሉት ችግሮች ተከስተው ቢሆን ኖሮ የሚያውቅበትም ዕድል እንደነበር ገልፆ የአካባቢን ጉዳዮች ለመከታተል ራሱን የቻለ ክፍል እንዳቋቋሙ ጠቁሟል። ከዚህም በተጨማሪ በአዶ ሻኪሶ አካባቢ በማዕድን ማውጣት ስራ ላይ የተሰማራው ሚድሮክ ወርቅ ኩባንያ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ኩባንያዎች በአካባቢው በመኖራቸው ከኬሚካል ጋር ተያይዞ ደረሰ የተባለው ጉዳት በእርግጥ ከሚድሮክ ጋር ብቻ የተያያዘ ስለመሆኑ ማረጋጋጫ የለም ብለዋል። ሚድሮክ በአካባቢው ልማት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን ገልጾ፤ ትምህርትቤቶች፣የጤና ኬላዎች፣ የመንገድ ግንባታ ላይ በመሳተፍ ለብዙ ሰዎችም የስራ ዕድል እንደፈጠሩ አስታውቋል። በማእድን ነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር የአካባቢ እና የማህበረሰብ ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሆኑት ወ/ሮ እናት ፋንታ ግን “እስከ መጋቢት 2009 ዓ.ም ባደረግነው ክትትልና ቁጥጥር መሰረት በኬሚካል የደረሰ ጉዳት አላየንም፤ ከማህበረሰቡም ሆነ ከመንግስት አካል የደረሰንም ቅሬታ የለም” በማለት ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የሻኪሶ ከተማ የማዕድን፣ነዳጅ እና ተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትሩ አቶ ሞቱማ መቃሳ ግን በሚድሮክ ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችችን ለመፍታት ድርጅቱ ከመንግሥት ጋር መስራት አለበት። ኬሚካል እና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ እየደረሰ ያለው ጉዳትም በ አስቸኳይ በገለልተኛ አካል መጣራት አለበት እንዳሉ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል። ይሁን እንጂ ጥያቄው የወርቅ ምርቱ ተጠቃሚነት ሳይሆን በህይወት የመቆየት ስጋት የሆነባቸው የዲባ ባቴ ነዋሪዎች “ከመንግስት በኩል መፍትሄ እንፈልጋለን” እያሉ ነው።
የሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኃላ.የተ.የግ.ማኅበር በ1989 ዓ.ም የለገደንቢን የወርቅ ማእድን ከመንግስት እጅ በ172 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለ20 ዓመታት በሊዝ ነበር የተረከበው። ድርጅቱ በ2014 እኤአ በአለም ባንክ በተዘጋጀው ፎረም ላይ ባቀረበው ሪፖርት መሰረት የሚድሮክ ለገደንቢ የወርቅ ማምረቻ እኤአ ከ 1997-2014 ድረስ ባሉት 16 አመታት 52 0444.71 ኪሎ ግራም ወርቅ እንዲሁም 14 670.6 የብር ማእድን አምርቶ 17.24 ቢሊዮን ብር እንደሸጠ ያሳያል።
ድርጅቱ ለ20 ዓመታት የተፈራረመው ውል አሁን በያዝነው የፈረንጆቹ አመት መጨረሻ የሚጠናቀቅ ሲሆን ስምምነቱ እንዲታደስለት አመልክቷል።
****
ምንጭ፦ 


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/90416

Monday, April 2, 2018

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ፣ የጀግኖች አርበኞች ገድልና የሃገራችን ታሪክ ሲነሳ ለምን ወያኔን ያመዋል

ታላቋ ብሪታኒያ በድንበር የሚዋሰኑትን ሱዳንን እና ግብፅን በቅኝ ግዛት እና በበላይ ጠባቂነት (Colony and de facto protectorate 1882 _ 1956) ታስተዳድር ነበር። በወቅቱ እንግሊዝ ትከተለው የነበረው የአገዛዝ ስልት ግብፅን በቀጥታ እራሷ እያስተዳደረች ነገር ግን በሱዳን ውስጥ ለእሷ ታማኝ የሆኑ ግብፃውያንን በመሾም ሃገራቱን ትገዛ ነበር። ጣሊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በቆየበት በ5ቱ ዓመት የአርበኞች ትግል ወቅት በየወረዳውና አውራጃው ለእሱ ታማኝ የሆኑ ባንዳዎችን ይሾም ነበር። በጣም የሚገርመው ቀኝ አዝማች፣ ግራ አዝማች ወዘተ እያለ ባንዳዎቹን እንደ ኢትዮጵያ ባህል ግራዚያኒ ሹመት መስጠቱ ነበር። በመሆኑም እውነተኛዎቹን ከሃሰተኞቹ ለመለየት ለጊዜውም ቢሆን አደናጋሪ ሁኔታ ፈጥሯል። የመለስ ዜናዊ፣ የስዩም መስፍን፣ የአርከበ እቁባይ እና የስብሃት አባቶችና አያቶች የጣሊያን ባንዳ ሹመኞች እንጂ በኢትዮጵያ መንግስት የተሾሙ አለመሆናቸው ይነገራል። በመሆኑም በወቅቱ በርካታ ለጣሊያን ያደሩ ባንዳዎች ከፋሽስት ጣሊያን ጎን በመቆም በሰላይነት፣ በቅጥረኛ ወታደርነት፣ በዳኛነት፣ በቢሮ የጽህፈት ስራና በመሳሰሉት ይሰማሩ ነበር። በወቅቱ በጠላት የተሾሙ ባንዳዎች በኢትዮጵያውያን ላይ ለፋሽስት አለቆቻቸው ከሚያቀርቧቸው ክሶች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፦
  • ቀን ቀን ገበሬ፣ ሌሊት ደግሞ አርበኛ ነህ፣
  • አርበኛ ቤትህ ታሳድራለህ፣ ስንቅና መረጃም ታቀብላለህ፣
  • ከአርበኞች ጋር ግንኙነት አለህ፣ ጥይትና መሳሪያ ገዝተህ ልከህላቸዋል፣
  • የኢትዮጵያን ባንዲራ በሰርግ ወይም በሃዘን ጊዜ ተጠቅመሃል (ሰቅለሃል)፣
  • ኢትዮጵያን ለማሰልጠን ለመጣው ለታላቁና ለገናናውን የጣሊያን መንግስት አልገዛም ብለሃል ተቃውመሃል፣ ሌሎችንም ቀስቅሰሃል ወዘተ የሚሉ ነበሩ።

ለሃገራቸው ሰምአት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ እና አቡነ ሚካኤል ህዝቡን ለጣሊያን አትገዙ ብለው አውግዘዋል በማለት መረጃውን ለጣሊያን ሹማምንት ያቀበሉት ጣሊያን በህዝቡ ውስጥ ለስለላ የሰገሰጋቸው ባንዳዎች ነበሩ። የፍርድ ሂደቱንና ቅጣቱን ብንመለከት አቡነ ጴጥሮስ ላይ ለፍርድ ከተቀመጡት ከሶስቱ በጣሊያን ከተሾሙ ዳኞች ውስጥ አንዱ ትግሬ ባንዳ ሲሆን በመጨረሻም  ጥፋተኛ ናቸው በማለት በሞት እንዲቀጡ ብይን ከሰጡ በኋላ አቡነ ጴጥሮስን ህዝብ በተሰበሰበት ዓደባባይ ላይ ግምባና ደረታቸውን በጥይት ተኩሰው ከገደሏቸው የጣሊያን ወታደሮች ውስጥ አንዱ ለፋሺስት ያደረ የትግሬ ባንዳ ወታደር ነበር። ህዝቡንም ቢሆን የኢትዮጵያን ባንዲራ በመኖሪያ ቤታችሁ አጥር (ምሰሶ) ላይ አውለብልባችኋል በማለት የእስርና የግድያ እርምጃ ይወስድባቸው ነበር። በመሆኑም ወያኔ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ያውለበለቡ ጀግኖችን ማንገላታት ከጌቶቹ ከፋሽስት ጣሊያኖች  የወረሰው ነው። እንደሚታወሰው በትግሉ ወቅት በየገባበት ከተማ የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ እያወረደ የህወሃትን አርማ በመስቀል የኢትዮጵያን ባንዲራ ግን ከክብሯ አውርደው እህልና ቅራቅምቧቸውን መቋጠሪያ ከረጢት ያደርጉት ነበር። በአንድ ወቅት ሟቹ መለስ ዜናዊ ሰራዊትህ ለምን እንደዚህ ያደርጋሉ ተብሎ ሲጠየቅ፣ ባንዲራ ጨርቅ ነው በማለት እንደተሳለቀ ይታወሳል። ነገር ግን ወያኔ ሲያጣጥለው የነበረውን ባንዲራ እነ እስክንድር እና ተመስገን በክብር ሲያውለበልቡ በመታየታቸው እንደ ወንጀል ተቆጥሮ በእስር እየተሰቃዩ ይገኛሉ። ዛሬ በወያኔ አገዛዝ ዘመን ትናንትና በአድዋ፣ በማይጨውና በ5ቱ ዓመታት የኢትዮጵያ አርበኞች ትግል ወቅት ጀግኖች አባቶቻችን ደማቸውን ያፈሰሰሱለትን የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ መውለብለቡ ወንጀል ነው መባሉ በህወሃትና በወራሪው በፋሽስት ጣሊያን መሃል ከቆዳ ቀለም ውጪ ሌላ ልዩነት ያለ አይመስልም። ለህሊናህ ፍረድ ብባል እንደኔ በህግ መጠየቅ አለበት ብዬ የማምነው “ባንዲራ ጨርቅ ነው” ብሎ የተሳለቀ እንጂ የአባቶቹን ሰንደቅ አላማን በክብር ያውለበለበ አይደለም።

ታሪክን ወደ ኋላ ሄደን ለማየት ብንሞክር የጣሊያን ጦር በ1988ዓ.ም አድዋ ላይ በአፄ ምኒልክ ብልህ አመራርና በጀግኖች አባቶቻችን ድል ተመቶና ተዋርዶ ከሃገራችን ከተባረረ በኋላ ቂም ቋጥሮ አርባ አመት ኢትዮጵያን ለመበቀል ተዘጋጅቶ በታንክ በአውሮፕላንና በዘመናዊ መሳሪያ በመታገዝ በ1928 ዓ.ም ኢትዮጵያን ቀኝ ግዛት ለማድረግ በሃገራችን ላይ መጠነ ሰፊ ጦርነት ከፈተ። የኢትዮጵያ አርበኞች ከመሃል ሃገር ተነስተው ወደ ማይጨው በእግር በፈረስ በመጓዝ ጦርነቱ ወደሚደረግበት ትግራይ ተመሙ። ይሁንና ጣሊያኖች የራሳቸውን መደበኛ ወታደር ብቻ ሳይሆን ባንዳዎችን መሳሪያ አስታጥቀው ጠበቋቸው። በመሆኑም ባንዳ ሽፍቶች ወገናቸው የሆኑት ኢትዮጵያውያኖችን መንገድ እየጠበቁ የደፈጣ ጥቃት በመፈፀም እየገደሉ መሳሪያቸውን ይነጥቁ፣ በአጋሰስ ተጭኖ ይላክ የነበረ ስንቅና ትጥቅ ይዘርፉ ነበር። በተለይ ከዋናው ሰራዊት መንገድ በመሳት ተነጥለው በምግብና በውሃ ጥም እጦት የሚንከራተቱትን አርበኞች መሳሪያቸውንና ንብረታቸውን ለመዝረፍ አድፍጠው ያጠቋቸው ነበር። በመሆኑም አርበኞቻችን ያደርጉት የነበረው ትግል ከወራሪው የጣሊያን ወታደር ጋር ብቻ ሳይሆን ከትግሬ ባንዳ ሽፍቶችም ጭምር ነበር። ጊዜው ስለራቀ አሁን ሲያስቡት ቀላል ሊመስል ይችል ይሆናል እንጂ አባቶቻችን ስንት ውጣ ውረድ አሳልፈውና ተንከራተው፣ ከውጭ ወራሪ ጠላት እና ከውስጥ ባንዳ ጋር ታግለው ነው ሃገራችንን በነፃነቷና በአንድነቷ ጠብቀው ያቆዩዋት። (የሃበሻ ጀብዱ የተባለውን በአዶልፍ ፓርለሳክ የተጻፈውንና በተጫነ ጆብሬ የተተረጎመውን የ1989 ዓ/ም እትም መጽሐፍ የባንዳን ክህደትና ሸፍጥ በተመለከተ ብዙ መረጃ ይሰጣል)።
ፋሺስት ጣሊያን ሰዎችን በባንዳነት ሲመለምል ከሚከተለው መስፈርት ውስጥ ዋናው ግለሰቦቹ ከሌላ ሰውም ሆነ ከሃገራቸው በፊት እራሳቸውን የሚያስቀድሙ፣ ለጥቅም ያደሩ እራስ ወዳድ መሆናቸው ነው። በመሆኑም ንግስና ይገባናለ የሚሉ ያኮረፉ የትግሬ ባላባቶች የነበራቸው የስልጣን ጥማትና ራስ ወዳድነት በቀላሉ ለጣሊያን ፕሮፓጋንዳ ሰለባነት አጋልጧቸዋል። ይህ ለጥቅም ሲባል ሌላውን ሰው ለጠላት አሳልፎ የመስጠት ባህሪ በቆይታ ከግለሰብ ወደ ማህበረሰብ እያደገ (እየተዛመተ) በመሄድ ትግራይ ብቻ ትጠቀም ወይም (Tigray First) ወደሚል የቡድን ዝርፊያና ወደ ዘረኝነት አደገ። በዚህ የስግብግብነት ባህሪያቸው ላይ የፋሺስት ያልተቋረጠ የጸረ አማራና የጸረ ኢትዮጵያ ፕሮፓጋንዳ፣ ከደርግ ጋር ሲዋጉ ይከተሉት የነበረው ማህበረሰብን ሁሌም በጨቋኝና በተጨቋኝ መደቦች የሚከፍለው የኮሚኒስት ፍልስፍና፣ የአረብ ሃገራት በእርዳታ ስም ያደርጉት የነበረው የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት፣ የወያኔ አመራሮች ከላይ እስከታች የነበራቸው የትምህርት እጦት፣ የግንዛቤና የባህሪ ችግሮች ሲጨማመሩበት ምን ያህል ሰዎቹን፣ ስግብግብ፣ እራስ ወዳድና ደም የጠማው ክፉ አውሬ (Beast) ሊያደርጋቸው እንደሚችል መገመት ይቻላል።
ወራሪው ፋሽስት ጣሊያን በአምስቱ ዓመታት ቆይታው የገነባውን መንገድና ሕንፃ በመመልከት የኢትዮጵያ አርበኞች ጣሊያንን ተዋግተው ማባረራቸውን ለጣሊያን ያደሩ ባንዶች ሲኮንኑና ሲቃወሙ መስማት የተለመደ ነበር፡፡ ይህ አባባላቸው መነሻው ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ላሰለጥን ነው የመጣሁት የሚለው ፕሮፓጋንዳ ነው። እነዚህ በቀኝ መገዛትን ይደግፉ የነበሩ ባንዶች ፋሽስት ጣሊያን በኢትዮጵያ በመቆየቱ ለሚያገኙት ጥቅም እንጂ የህዝቡ ሞትና ስቃይ፣ የሃገር ክብርና ነጻነት መጓደል አይቆረቁራቸውም ነበር። ፋሽስት ጣሊያን ቢቆይ(በቀኝ ቢገዛን)መንገድና ሕንፃ ይገነባልን ነበር የሚለው ደካማ አስተሳሰብ እኛ ኢትዮጵያኖች እራሳችን ሠርተን ሀገራችንን መለወጥ፣ መገንባት፣ ማሳደግ እንችላለን የሚል በራስ የመተማመን ስሜት የሌለው የአባቶቹን ታሪክ ወደኋላ ሄዶ መመልከት ያልቻለ ነው። የአክሱም፣ የላሊበላና የጎንደር ስልጣኔን ማየት የተሳናቸው፣ አፄ ምኒሊክ መንገዱን፣ ስልኩን፣ ባቡሩን፣ መኪናውን፣ ዘመናዊ የመንግስት መዋቅርና ስልጣኔና የመሳሰለውን እንዳልጀመሩ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የመርዝ ቦንብ እያዘነበ የገባውንና 30ሺህ የአዲስ አበባን ህዝብ የጨፈጨፈውን ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ለማሳደግ (ለማሰልጠን) ነው የመጣው በማለት ባንዶች ማናፈሳቸው፣  የፋሽስት አስተሳሰብ እራስን ዝቅ የማድረግን፣ እኛ ብንማር፣ ብንሰራ በራሳችን እውቀትና ልፋት ብንጥር ሃገራችንን እናሳድጋለን የሚልን አስተሳሰብ የሚፃረርና የሚያቀጭጭ፣ የበታችነትን ስሜት ውጤት ነው። ባንዳ ክብርም ሆነ ፍቅርና ወንድማማችነት አያቅም። የባንዳ አልፋና ኦሜጋ ጥቅም እንጂ የሃገር ነጻነት፣ የወገን ፍቅር፣ ያባቶች ታሪክና ተጋድሎ አይደለም። ለእነሱ ሴረኛነት እንጂ እውነተኛነት ቦታ የለውም። ሉዓላዊነት፣ ነጻነት፣ ኩራት የሚባሉ የመንፈስ ልእልና የላቸውም። ብርሃንና ጨለማ ህብረት እንደሌላቸው ሁሉ አርበኝነትና ባንዳነት ፈጽሞ አንድነት የላቸውም። እኛና እነሱ የተለያየ ፍላጎትና ማንነት ያሉን የሁለት ዓለም ሰዎች ነን። ምናልባት በቆዳችን (በመልክ) ልንመሳሰል እንችል ይሆናል እንጂ ሊታረቁ የማይችሉ የተለያዩ ስነልቦና ያለን ሰዎች ነን።
ጣሊያን ሃገር ውስጥ እያለ በሹመኝነት ቢሮክራሲው ውስጥ ተሰግስገው የነበሩት ሹምባሽ ባንዶች ልክ ጣሊያን በአርበኞች ትግል ከሃገር እንደተባረረ ሁኔታዎች አስገድዶን እንጂ ንጉሳችንንና ሃገራቸንን ጠልተን አይደለም በማለት በተገለባባጭ የእባብ ፀበያቸው ንጉሱን ተማፀኑ። ቀ/ኃ/ስላሴ የፈራረሰችና በፋሽስት ዝብርቅርቋ የወጣን ሃገርን ለማስተካከል ብዙ ስራ እንደሚጠብቃቸው ግምት ውስጥ በማስገባት ሃገሪቷን ለማረጋጋት ሲሉ ለባንዳዎቹ ይቅርታ በማድረግ ቀጥታ ሃገርን በማደራጀትና በማቅናት ስራ ተጠመዱ። ይሁን እንጂ ሹምባሽ ባንዶች በጣልያን ጉያ ስር ሆነው አርበኛውንና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊውን እየሰለሉ እንዳላስፈጁ፣ ከድል በኋላም ሴረኛነታቸውን ባለመተው ከንጉሱ ስር እየተልከሰከሱ በአርበኛው ላይ የእባብ መርዛቸውን ይረጩ ነበር። ሃገርን ሲያደሙ የነበሩ ባንዶች በቢሮክራሲው (በመንግስትን ስልጣን) ውስጥ ተሰገሰጉ። በወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ያየውንና የታዘበውን በስነ ቃል እንዲህ ብሎ ገለፀ።
“እምዬ ኢትዮጵያ ሞኝነሽ ተላላ፣
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ፣”

ተምረናል የሚሉ የዘመናችን የባንዳ ልጆች ይህ እንደ ጥላ ሁሌም የሚከተላቸው አሳፋሪ የክህደት ታሪካቸውን ለመሸሽ እንደ መጀመሪያ አማራጭ ያስቀመጡት ከእውነት የራቀ ለእነሱ የሚያመቻቸውን የሃሰት ትርክት በመፃፍ ያችኑ ተረት ተረታቸውን እንደ ዳዊት እያነበነቡ እራሳቸውን ማጽናናት ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ገድልና ታሪካቸው፣ የጦርነት ውሏቸው በተነሳ ቁጥር ቁስላቸውን እየነካካ ስለሚያሰቃያቸው ኢትዮጵያን ከነታሪኳ አንድ ላይ ለማጥፋት ይከጅላቸዋል። የአክሱም ስልጣኔ ለትግሬው ምኑ እንደሆነ ቢጠየቁ ታሪክ አጣቅሰው በመረጃ መናገር የማይችሉ ደናቁርት በባዶ እብሪት ተወጥረው አክሱም ለወላይታው ምኑ ነው እያሉ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያላቸውን ንቀት በአደባባይ ይገልጻሉ። እንደ እብደትም ሲያደርጋቸው ኢትዮጵያ የመቶ አመት ታሪክ ነው ያላት፣ አርበኞች የተዋደቁለትን ሰንደቅ አላማ ጨርቅ ነው እያሉ ይሳደባሉ። የባንዳ ክህደት በባንዲራ ብቻ የሚገለጽ ሳይሆን ጀግኖቿንም በማዋረድና የሰሩትን አኩሪ ገድል ጥላሸት በመቀባትም ነው። ለምሳሌ በአድዋ ጦርነት የኢትዮጵያን ህዝብ አስተባብረውና ጦሩን መርተው ለድል ያበቁትን የጦሩን መሃንዲስ የዳግማዊ አፄ ምኒሊክንና የእቴጌ ጣይቱ ሃውልት በአድዋ እንዳይቆም በወያኔ መከልከሉና በተቃራኒው ደግሞ የብዙ ኢትዮጵያውያንን ደም ላፈሰሰው ለጣሊያን የጦር አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዳቦርሚዳ ሃውልት እንዲቆምለት መፍቀዳቸው ህወሃቶች ለአማራ ያላቸውን ስር የሰደደ ጥላቻ ብቻ የሚያሳይ ሳይሆን ከፋሺስት ጋር ያላቸውን ታሪካዊ ዝምድና ይመሰክርባቸዋል።

ወያኔ  ከደርግ ጋር ስዋጋ ወደ 50 ሺህ ሰው አልቆብኛል ይላል። ነገር ግን ወያኔ የመንግስት ስልጣን ከያዘበት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በየማጎሪያው የሰራቸውን ለጊዜው ትተን በአጋዚ ጦሩና በፌዴራል ፓሊስ የተጨፈጨፈው የሰላማዊው ህዝብ ብዛት ወያኔ  ከደርግ ጋር ስዋጋ ሞተብኝ ከሚለው በብዙ ጊዜ እጥፍ የሚበልጥ ነው። ለምሳሌ ለህዝቡ ሃላፊነት የማይሰማው የወያኔ አገዛዝ ትርጉም በሌለው በባድሜ ጦርነት ወደ 75 ሺህ ህዝብ በላይ ማግዷል፣ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠር የወልቃይት አማራ ህዝብን ህወሃት ገድሏል፣ በጎንደር፣ በደብረ ታቦር፣ በባህር ዳር፣ በደብረ ማርቆስ፣ በወልዲያ፣ በሸዋ፣ በአዲስ አበባ (በረራ)፣ በቢሾፍቱ ደብረዘይት፣ በአንቦ፣ በጨለንቆ፣ በጋምቤላ፣ በኮንሶና በመሳሰሉት ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች የጨፈጨፋቸው ዜጎች በብዙ መቶ ሺህዎች ወይም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ናቸው። እዚህ ላይ መገንዘብ የሚያስፈልገው ህወሃት ሞቱብኝ የሚላቸው ታጋዮቹ ጦር ሜዳ ላይ ነው፣ ነገር ግን እነሱ እየገደሉት ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን በጦር ሜዳ ላይ ሳይሆን ሰላማዊ ህይወቱን በሚመራበት በመሃል ሃገር ላይ ነው።
ያን ሁሉ ብልግናቸውንና የፈጸሙትን ወንጀል ከኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወረ ይመስል “ለማያቅሽ ታጠኚ” እንደሚባለው ዓይነት ዛሬ ደግሞ ለኢትዮጵያ ባንዲራ ተቆርቋሪ መስለው ህዝብ ያተራምሳሉ። በሽታቸው የሚድነው ጥፋታቸውን አምነው የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ በመጠየቅ ብሔራዊ እርቅ ማውረድ እንጂ ህዝብን በማተራመስ ወይም ታሪክ በመደለዝ አይደለም። መቼስ ባለጌ ሁሌም ባለጌ በመሆኑ ውለታም ሆነ ይሉኝታ አያቅምና ይህንን ሁሉ አንገት የሚያስደፋ አሳፋሪ ታሪክ ና በደም የተጨማለቀ እጅ ይዘው ደጉ የኢትዮጵያ ህዝብ ሳይጸየፋቸው ገበናቸውን ሸፍኖና ይቅር ብሎ እንደ ባዳ ሳይሆን እንደ ወንድም ባኖራቸው በእነሱም ብሶ የኢትዮጵያን ህዝብ ምክንያት እየፈለጉ ጭንቅ ጭንቅላቱን ይቀጠቅጡታል። —//—

ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች አባቶቻችን
ደረጀ ተፈራ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/89509

Tuesday, March 27, 2018

“ባህር ዳር ላይ በግፍ የታሰሩ የአማራ ልጆች በአስቸኳይ ይፈቱ!”

ከመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት የተሰጠ መግለጫ
አማራን ማህበራዊ ደስታ እና ሰላም እንዳይኖረው አደርጋለሁ በማለት ምሎ ተገዝቶ የመጣው እብሪተኛው የወያኔ ትግሬ ፋሽሰት መንግስት በዘወትር አሽከሩ ብዓዴን አማካኝነት በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ከተማ ሰላማዊ ወጣት የአማራ ምሁራንን ወደ ማጎሪያ ስፍራ ወስዶ በማሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡ እነዚህ ምሁራን የታፈሱት በሰላማዊ መንገድ ተንቀሳቅሰው ለአማራ ህዝብ ነጻነት የሚታገል የፖለቲካ ድርጅት ለመመስረት ህጉ የሚጠይቀውን ሁሉ ሲያሟሉ ቆይተው፤ የቅድመ ምስረታ ጉባዔ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ዕቅድ ለመንደፍ ለእራት በተሰባሰቡበት ሰዓት ነው፡፡ በእንዲህ ያለ ሁኔታ የሚንቀሳቀሱ ዜጎች እንክብካቤ እንጅ እስራት እና እንግልት አይገባቸውም ነበር፡፡ ይሁን እንጅ ማንኛውንም ዓይነት የአማራን ህዝብ እንቅሰቃሴ በተመለከቱ ቁጥር አይናቸው ደም የሚለብሰው የስርዓቱ ቁንጮወች ይህ እንዲሆን ፈፅሞ አይፈልጉም፡፡ የአማራ ህዝብ ያለበት ነገር ሁሉ ያንገበግባቸዋል፡፡ ቅናት እና ፍርሃት በእጅጉ ያውኳቸዋል፡፡ ሞት ሞት ይሸታቸዋል፡፡
በተመሳሳይም ከወያኔው ማሰቃያ እስር ቤት በህይወት ተርፈው ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸውን አስመልክቶ የደስታ ጊዜ ለማሳለፍ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በእንድ ጓደኛቸው ቤት የተሰባሰቡ የነጻነት ታጋዮች በግፈኛው ስርዓት ማናለብኝነት እንደገና ለእስራት ተዳርገዋል፡፡ እነዚህም ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ የአማራ ልጆች ናቸው፡፡
አማራ ከሌሎች ጋር ተባብሮ ለመታገል ሲንቀሳቀስም ሆነ ለብቻው በአማራነቱ ለመደራጀት ሲፈልግ ዘረኛው ስርዓት ያለ የሌለ የአፈና ጉልበቱን በመጠቀም ዕንቁ የአማራ ልጆችን ሲገድል እና ሲያስር ብሎም በህጋዊ መንገድ የመሰረቱትን የፖለቲካ ድርጅት ሲነጥቅ እና ሲያፈርስ 27 ዓመት ሆኖታል፡፡ ይህ አይነት አካሄድ ከአሁን በኋላ በአማራ ላይ እንደማይሰራ ሊረዳ ያልቻለው ወያኔ መግቢያ ጉድጓዱን አርቆ በመቆፈር ላይ ይገኛል፡፡
ከላይ በተጠቀሰው ሁኔታ ባህር ዳር እና አዲስ አበባ ላይ የታሰሩ ሁሉም እስረኞች ያለምንም ቅደመ ሁኔታ በአስቸኳይ ይፈቱ፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን አድማ መምታትን ጨምሮ መጠነ ሰፊ እርምጃ እንዲወስድ መዐሕድ ለመላው የአማራ ህዝብ ጥሪ የሚያስተላልፍ መሆኑን አበክሮ ያስጠነቅቃል፡፡
ድል ለአማራ ህዝብ!
የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት (መዐሕድ)
http://www.satenaw.com/amharic/archives/53584

Wednesday, March 21, 2018

የኦሮሚያ ፍትህ ቢሮ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ “ሕዝብን የገደሉ ይጠየቁ” በማለታቸው ታሰሩ



ልበ ሙሉ፡ ደፋር፡ ጀግና፡ አንደበተ ርትዑ፡ የወገን ጥቃት የሚያመው፡ ትንታግ፡ ልበ ደንዳና ኦቦ ታዬ ደንደአ። የኦሮሚያ ክልል ፍትህ ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ሃላፊ ናቸው። በዚህ የጭንቅና የምጥ ወቅት የተገኙ ኮከብ በመሆናቸው ልናመሰግናቸው፡ ከጎናቸውም ልንቆም የሚገባን እንደሆነ ይሰማኛል። አቶ ታዬ በሁለት ቃለመጠይቆች ላይ ባሳዩት ፍጹም ድፍረትና የወገን ተቆርቋሪነት ነጥረው የወጡ የኢትዮጵያ ልጅ ናቸው። ዛሬ ጭራቆቹ እጅ ላይ ወድቀዋል።
የትግራዩ ገዢ ቡድን የለማን ኦህዴድ ለማዳከምና ለመሰባበር እንቅልፍ አጥቶ እያደረ ነው። የኦሮሚያን የወረዳ፡ የከተማና የዞን ባለስልጣናትን በማሰር የጀመረው እንቅስቃሴ ወደላይ ከፍ ብሎ የካቢኒ አባላት ጋ ደርሷል። አቶ ታዬ የትግራዩን ገዢ ቡድን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ለህዝባቸው ያላቸውን ፍጹም ተቆርቋሪነት በማሳየታቸው በኮማንድ ፖስቱ መታሰራቸው ታውቋል። በተለይ ሰሞኑን በሞያሌ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ ”በስህተት” በሚል መገለጹን ተከትሎ አደባባይ በመውጣት ”ስህተት አይደለም፡ ግልጽ የጦር ወንጀል ነው። የመከላከያም ሆነ የኮማንድ ፖስቱ አዛዦች በህግ ሊጠየቁ ይገባል” ማለታቸው በትግራዩ ገዢ ቡድን ሰፈር ጸጉር እስኪነቀል ያበሳጨ መሆኑ ተሰምቷል።
ከዚህ ቀደምም የትግራዩ ገዢ ቡድን ቄሮዎች ላይ ምርመራ ጀምሬአለሁ ያለ ሰሞን ሚዲያ ላይ ወጥተው ”ምን አገባህ” በማለት ምላሽ መስጠታቸው ከህዝብ ከፍተኛ ከበሬታን እንዲያገኙ አድርጓቸዋል። ከትግራዩ ገዢ ቡድን ደግሞ ጥርስ አስነክሶባቸዋል። እሳቸው ብቻ አይደሉም። የአምቦ ከተማ ፖሊስ አዛዥ፡ የሞያሌ ከተማ ከንቲባ፡ ሌሎችም የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት እያሳዩ ያሉት የህዝብ ወገንተኝነት በደማቁ የሚነሳ ነው። ከትግራዩ ገዢ ቡድን ዱላ ይልቅ የህዝባቸው ቁጣ የሚያስፈራቸው ናቸው። መንገዳቸውን መርጠዋል። ዘላቂ ጉዞ ከህዝብ ጋር እንጂ ከሚያልፍ ስርዓት ጋር እንዳልሆነ አውቀውታል። ካወቁ አይፈረድባቸውም። ለምንስ ይቀጣሉ? እየሰጠመ ካለ መርከብ ዘንድ ምን አላቸው? ቄሮን የመስለ መከታና ጋሻ እያላቸው ? ?
የትግራዩ ገዢ ቡድን ዙሩን ማክረር ፈልጓል። ለህዝብ የሚበጀው፡ ለሀገር የሚጠቅመው እንዲህ ዓይነቱ በትዕቢትና ድንቁርና የሚነዳ አመራር አልነበረም። ድምሩ ዜሮ የሆነ፡ አጥፍቶ መጥፋት መስመር ላይ የቆመ አካሄድ አወዳድቅን አጉልና ዘግናኝ ከማድረግ ውጪ የህዝብን የነጻነት ተጋድሎ አይቀለብሰውም። የአቶ ታዬ ደንደአ እስር ህዝብን ለቁጣ የሚፈነቅል ተጨማሪ ምክንያት እንጂ ወደ ቤቱ የሚያስገባ፡ በፍርሃት ተሸብቦ አንገቱን ደፍቶ እጅ የሚያሰጠው አይሆንም።
ሺ ታዬዎች ተፈጥረዋል። ሚሊየን ለማዎች በቅለዋል። ለትግራዩ ገዢ ቡድን የደንቆሮ ለቅሶ መልሶ መላልሶ ሆኖበት እንጂ ለነጻነት የቆመን የህዝብ ልብ ወደ ኋላ የሚመልሰው ምንም ዓይነት ምድራዊ ሃይል የለም። ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ ይባላል። የትግራዩ ገዢ ቡድን ከዚህ በኋላ የራሱን መጨረሻ የማሳመር ሃላፊነቱ የራሱ ብቻ ነው። አወዳደቁ አጉል እንዳይሆን ነገሮችን የማለስለስ ስራ እንጂ እንዲህ ማጦዝ ከማንም በላይ የሚጎዳው ራሱኑ ነው።
ትላንት ዛሬ አይደለም!!!!
https://ecadforum.com/Amharic/archives/18716/

Sunday, March 18, 2018

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሰላማዊ ዜጎችን መግደል እንዲቆም ጠየቁ

ከእስር በቅርቡ የተፈቱት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ወልዲያ ናቸው።  የጉዟቸው ምክንያት ደግሞ ልጆቻቸው በመንግሥት ታጣቂዎች የተገደሉባቸውን ቤተሰቦች ለማፅናናት እንደሆነና በዚህም “መንግሥት ሰላማዊ ዜጎችን ተኩሶ ሊገል አይገባም” የሚል መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ እንደሆነ ለባልደረባችን ለመለስካቸው አምሃ ነግረውታል።መለስካቸው ከአዲስ አበባ ደውሎ ሦስቱንም እንዲሁም አብረዋቸው ያሉትን የ13 ዓመት ዕድሜ ልጃቸው ዮሴፍ እሸቱ የተገደለባቸውን አባት አቶ እሸቱ ጀመረን አነጋግሯል።
 VOA Amharic
http://www.satenaw.com/amharic/archives/53041

Saturday, March 17, 2018

ወደ ኬንያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ሊጨምር ይችላል ተባለ

ባለፈው ሣምንት ቅዳሜ በቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ የመከላከያ ሠራዊት በነዋሪዎች ላይ የፈጸመው ግድያ በየአቅጣጫው ቁጣን ቀስቅሷል። የኮማንድ ፖስቱ ድርጊቱ በተሳሳተ መረጃ ምክንያት የተከሰተ መሆኑን ቢገልፅም የመከላከያ ኃይሉ ጥቃት ሆን ተብሎ የተፈጸመ የወንጀል ድርጊት እንደኾነ የገለጡ አሉ


ከኢትዮጵያ ተጨማሪ ዜጎች ወደ ኬንያ ሊሰደዱ እንደሚችሉ የዓለም የምግብ መርኃ-ግብር (WFP) ሥጋቱን ገለጸ። የድርጅቱ የኬንያ ጽ/ቤት ቃል አቀባይ ፒተር ስሜርዶን ተፈናቃዮችን በተመለከተ ሲናገሩ፦ «በኢትዮጵያ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት ምናልባት ቁጥራቸው ሊጨምር ይችላል ብለን እንጠብቃለን» ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። ወደ ኬንያ የተሰደዱት ኢትዮጵያውያን «አሁን ቁጥራቸው ከ9, 600 በላይ ናቸው ተብሎ ይገመታል» ያሉት ስሜርዶን አብዛኞቹ ሴቶች እና ሕፃናት መሆናቸውን ገልጸዋል። ከትናንት ጀምሮም የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት እና የዓለም የምግብ መርኃ-ግብርን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ወደ ኬንያ የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ለመርዳት ሁኔታውን እያጠኑ መሆኑን ለዶይቼ ቬለ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ የተሰደዱ ዜጎችን ለመመለስ «ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ»መሆኑን ገልጿል። የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አሰፋ አብዩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ «ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚመለከታቸው ከክልልና ከፌድራል መንግሥት ከአካባቢ አስተዳደር ቡድን ተዋቅሮ ወደ ቦታው ሔዷል። ሕብረተሰቡን የማረጋጋት ሥራ እየተሰራ ነው። የተጎዱ ቤተሰቦችን የመደገፍ ሥራ እየተሰራ ነው። የተፈናቀሉ እና ወደ ኬንያ ድንበር የሔዱ ዜጎቻችንን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው» ሲሉ ተናግረዋል።
http://www.dw.com/am/%E1%8B%88%E1%8B%B0-%E1%8A%AC%E1%8A%95%E1%8B%AB-%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%88%B0%E1%8B%B0%E1%8B%B1-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%E1%8B%8D%E1%8B%AB%E1%8A%95-%E1%89%81%E1%8C%A5%E1%88%AD-%E1%88%8A%E1%8C%A8%E1%88%9D%E1%88%AD-%E1%8B%AD%E1%89%BD%E1%88%8B%E1%88%8D-%E1%89%B0%E1%89%A3%E1%88%88/a-43025309

‘Ethiopian police killed hundreds of protesters’