Friday, July 31, 2015

የእስረኛው የአንዷለም አራጌ ማስታወሻ “በኢትዮጵያ እውነትና ፍትህ ከትቢያ የተሻለ ቦታ ቢኖራቸው ኖሮ…. ”

ሕዝብ የሉዓላዊ ስልጣኑ ባለቤት በሆነበት ሃገር ፍትህ ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ትቀመጣለች፡፡ እውነትም ምሰሶና ወጋግራ ሆና ፍትህን ዘወትር የመደገፍ እድሏን ትጎናጸፋለች፡፡ በኢትዮጵያ የፍትህና የእውነትን የክብር ቦታና ሚና አፈ-ሙዝ ወስዶታል፡፡ ፍትህና እውነት ደግሞ ትቢያ ላይ ተጥለዋል – ምንም እንኳ እንደወደቁ ባይኖሩም፡፡
በኢትዮጵያ ፍትህና እውነት ትቢያ ላይ ባይጣሉ ኖሮ ለዓመታት ይቅርና ለሰዓታት እንኳን በእስር ቤት ግርጌ መጣል ባላስፈለገንም ነበር፡፡ ፍትህና እውነት በኢትዮጵያ አድራሻ ቢኖራቸው ኖሮ ለዚህ ዓለም እንግዳ የሆኑት ልጆቼ ለዓመታት ሳይሆን ለሰዓታት እንኳን የአባታቸውን ፍቅር በግፍ ባልተነጠቁ ነበር፡፡ ፍትህና እውነት የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን ብትሆን ኖሮ ለዓመታት ሳይሆን ለሰዓታት እንኳን ባለቤቴ ከእኔ ጋር የመኖር ሰብዓዊ መብቷን ተገፋ በወጣትነት እድሜዋ የመበለትነት ህይወት የመግፋት እዳ ባልወደቀባት ነበር፡፡ ፍትህና እውነት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ እንኳን መንሳፈፍ ቢችሉ ኖሮ በሃሰት ዶሴ ከታሰርኩ በኋላም ለዓመታት በእስር ቤት ውስጥ ተጨማሪ የግፍ ፅዋ እንድንጎነጭ ግድ ባልሆነብኝም ነበር፡፡ በኢትዮጵያ እውነትና ፍትህ ከትቢያ የተሻለ ቦታ ቢኖራቸው ኖሮ ረጅም ርቀት አቆራርጠው ሊተይቁኝ የሚመጡ ጠያቂዎቼ የመጠየቅ መብታቸውን ለዓመታት ሳይሆን ለሰዓታት እንኳን ባልተነፈጉም ነበር፡፡
በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊቷ ኢትዮጵያ እኔና ቤተሰቤ ፍፁም ኢሰብዓዊ ከሆኑ ነገሮች ጋር ተላምደን፤ በሞትና በህይወት መካከል ያለው ልዩነት እስኪጠፋን ድረስ በአባቶቻችን፣ በራሳችንና በልጆቻችን ሃገር፤ በህዝባችን ፊት በማናለብኝነት ጥቂት አፄዎች ጢባጢቢ እንዲጫወቱብን ተበይኖብናል፡፡ በውል የማውቀውን የራሴን ጉዳይ በዋናነት ባነሳም የእኔና የቤተሰቦቼ ህይወት የእነ እስክንድር ነጋንና ሌሎች አንባቢ ፈፅሞ የማይዘነጋቸው ኢትዮጵያውያንና ቤተሰቦቻቸውም ፅዋ መሆኑን ፈፅሞ ዘንግቼው አይደለም፡፡ በየትም ቢሆን አንድ ዜጋ የግፍ ፅዋ እንዲጎነጭ ሲገደድ የሚጠጣው የኢ-ፍትሃዊነት ስቃይ ጥልቅ ነው፡፡ በተለይ ግን በሚወደው ህዝቡ ፊትና የእኔ ብሎ በሚኮራበት ሃገሩ እንደርሱ ደምና ስጋ የለበሱ ጥቂቶች ያሻቸውን ሲፈፅሙበት የግፉ ስቃይ ከመቼውም በላይ ይከፋል፡፡ ይህንን ከመሰለው የኢፍትሃዊነት ስቃይ ለአፍታም ቢሆን የሚያሳርፋቸው ግን አንድ ነገር አለ፡፡ አንባቢ የማይዘነጋቸው ወይዘሮ ሮዛ ፓርክስ መቀመጫቸውን ለቀው የኋላ ወንበር ላይ እንዲቀመጡ አሊያም ከአውቶብስ እንዲወርዱ ሲጠየቁ በእግራቸው መሄድን መምረጣቸው ብቻ ሳይሆን ለምርጫቸው የሰጡት አመክንዮ ጥልቅ ትርጉም አለው፡፡ ‹‹በእግርሽ ይሄንን ያህል ማይል መጓዝ ይሻላልን?›› ለሚለው ጥያቄ ‹‹እግሮቼ ይደክማሉ ነፍሴ ግን ታርፋለች›!›› ብለው ነበር፡፡
እኔም በምወዳት ሃገሬ በህዝቤ ፊት ከእነቤተሰቤ የግፍ ሰለባ ብሆንም ህሊናዬን የሚጎረብጠኝ ነገር ባለመኖሩ የእኔም ነፍስ እረፍት አላጣችም፡፡ የሌሎች በግፍ የታሰሩ ጓደኞቼም ህሊናቸውው ፍፁም እረፍት የተጎናፀፈ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ትልቁ የህሊና እዳ በሃሰት ካሰሩኝ በኋላም በግፍ ተግባራቸው የሚመፃደቁት አሳሪዎቼ እንጂ የእኔ አይደለም፡፡ ያልተገባ ዋጋ እንዲከፍል የተገደደ እኔን የሚመስል ዜጋ ሞትንም እንኳን ቢሆን በክብርና በደስታ ለመጋፈት ይዘጋጃል እንጂ ህሊናውን ሰላም በሚያሳጣ ድር ተጠልፎ አይወድቅም፡፡
ውድ አንባቢ በእኔ ጫማ ውስጥ ቢቆሙ ከዚህ የተለየ ምን ሊያደርጉ ይችላሉ? በሃገርዎ፣ በህዝብዎ ከምንም በላይ በህልውናዎና በእጣዎ ላይ የግል አቋምዎን እንዳያራምዱ በሃሰት ዶሴ ተጠርቀው መቀመቅ ቢወርዱ ከዚህ የተለየ አቋም ሊኖርዎት ይችል ይሆን? በሚያምኑበት ጉዳይ ተሸብበው የሚነገርዎትን ብቻ እንዲፈፅሙ ቢነገርዎት ይስማማሉን? የመብቶቹ ባለቤት ላልሆነ ዜጋ ሰው መሆን ማለት ምን ትርጉም ይሰጣል? ይኸ ሁሉ አንሶ በእሾህ በታጠረ የፖለቲካ ሰርጥ ውስጥ በተቦዳደሰ እግርዎ እያነከሱ እንዳይንከላወሱ እንኳን ‹‹እግር በመቁረጥ›› ፈሊጥ የተካኑ ገዥዎች እግርዎን ቢቆርጡት ምን አይነት ስሜት ይፈጥርብዎታል? ጥቂት ዙፋን ላይ የተቀመጡ ባለጊዜዎች ምን ማሰብ እንዳለብዎ እንኳን ሳይቀር ሲወስኑልዎ እና ባጠቃላይ የርስዎ ህልውናና ተፈጥሮአዊ መብትዎችዎ በነሱ መዳፍ ስር ያሉ፤ ከፈለጉ ብቻ ቆንጥረው የሚሰትዎ ካላሻቸው የሚነፍጉት ሲሆን ምን አይነት ትርጉም ይሰጥዎት ይሆን?
አዎ ሀገር በጭቆና ቀንበር ስር ስትወድቅ ድጋፍ ብቻ እንጅ የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት ስርየት የሌለው ሃጢያት ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ለገዥዎች በታጠረው አጥር ውስጥ በድፍረት ለማቋረጥ ሲሞክሩ ‹‹ቀዩን መስመር አልፈዋል›› በሚል አይቀጡ ቅጣት ይቀጣሉ፡፡ በዜጎች ላይ የሚፈፀሙ ግፎች እንደነውር ወይም ግፍ ሳይሆን አገዛዙን ለማስቀጠል የሚያስፈልጉ፤ ከትልቅ አዕምሮ የተቀዱ ልዩ የፖለቲካ ቀመሮች ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡
በአገዛዙና የግፍ ሰለባ በሆነ እኔን በመሰለ ዜጋ መካከል የሚደረገው ትግል ከወትሮው የተለየ ነው፡፡ አገዛዙ እስረኛውን ለማምከን ሲተጋ እኔን የሚመስል እስረኛ በግርግም ውስጥም ሆኖ ደግሞ ህይወት በከንቱ እንዳይባክን ይታገላል፡፡ ለዚህም ነው አገዛዙ እስር ቤት ውስጥ እንኳን ከሌሎች አያሌ እስረኞች በተለየ ግፍ የሚፈፀምብኝ፡፡ እኔም እኔን የመስበር ተልኳቸው ገብቶኛልና ግብግቡን ለማሸነፍ ፍፁም በማይመች ሁኔታ ውስጥ ሆኘ ለሀገሬ ይበጃል ያልኩትን ሀሳብ በሁለት መፅሐፎች ለማድረስ ሞክሬያለሁ፡፡ ከነጉድለቱም ቢሆን ‹‹ያልተሄደበት መንገድ›› ከብዙ ፈተና በኋላ ለአንባቢ ሲደርስ የተሰማኝ ደስታ ወደር የለውም፡፡ አሁን ደግሞ የፈጣሪ ፀጋ በዝቶልኝ ታምር በሚመስል መልኩ ‹‹የሀገር ፍቅር ዕዳ›› የተሰኘውን ሁለተኛ መፅሐፌ ለአንባቢ በመድረሱ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ በሀገር ፍቅር ዕዳ የግል ህይወቴን ጭምር ጨልፌ ለማካፈል ሞክሬያለሁ፡፡ የእኔ የዝቅታ ህይወት የሚሊዮኖችን ኢትዮጵያውያንን ህይወት እንደሚወክል በማመን፡፡ ምንም እንኳ የሚያስኮፍስ ያለፈ ታሪክ ባይኖረኝም ታሪክ የሚያኩራራው ብቻ አይደለምና ከተመላለስኩባቸው ውሃ አልባ ሸለቆዎች አንባቢዎች የሚቃርሟቸው ጥቂት ቁምነገሮች አይጠፉም፡፡ የህይወት ከፍታ ከሩቅ ስለሚታይ ነጋሪ አያሻውም፡፡ ዝቅታን ለማሳየት ግን ጉልበት ይጠይቃልና ለማሳየት በመሞከሬም እንዲሁ ደስታ ይሰማኛል፡፡
በሀገር ፍቅር ዕዳ የእኔን ከፍና ዝቅ ህይወት ብቻ ሳይሆን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያለኝን እይታ ያለምንም ማድበስበስ ለአንባቢ ለማካፈል ሞክሬያለሁ፡፡ ያልተሄደበት መንገድ ላይ በሩቁ የሰማኋቸውን አስተያየቶች በዚህኛው ለማረም ተፍገምግሜያለሁ፡፡ አንባቢ እንደሚረዳው መፅሐፌም እንደኔ ነፃነት የተነፈገ በመሆኑ እንደሌሎች መፅሐፍቶች  ከመታተሙ በፊት በተለያዩ ሰዎች ተገምግሞ እንደገና አርሜው የመውጣት እድሉን አላገኘም፡፡ ስለዚህ ግድፈቶች ካሉ አንዱ መንስኤ ይሄው ነው፡፡
ህይወቴ አንባቢን የሚስያተምሩ፣ ነገሮችን ከተለየ ማዕዘን ለማየት የሚረዱ፤ ከተቻለም ፈገግ የሚያሰኙ ነገሮች እንዲገኙበት ትልቅ ምኞት አለኝ፡፡ በህላዌ ዘመናችን ስንመላለስ የህይወትን ትርጉም ከሚሰጡ ምግባሮች መካከል አንዱን ለመከወን ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ ምን ያህል ተሳክቶልኝ ይሆን? ይህንን ለናንተ ልተወው፡፡
ለዘመናት ልባችን በናፍቆት ለዛለላት የዴሞክራሲና የነፃነት ጀምበር የምትወጣበት ታላቅ የንጋ ቀን ከመቼውም ጊዜ በላይ እየቀረበ መሆኑን በፍፁም በማመን፡፡
አንዷለም አራጌ (ቃሊቲ፤ የህሊና እስረኛ)
http://satenaw.com/amharic/archives/9171

Tuesday, July 28, 2015

በኦባማ ጉብኝት ኢሕአዴጎች ለሁለት ተከፍለዋል “የምርጫው 100% ውጤት የዓለም መሳቂያ አድርጎናል” የሚሉ ካድሬዎች በዝተዋል

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያ መምጣት ጠቅሞናል በሚሉና መሳቂያ አድርጎናል በሚሉ ሃሳቦች የኢሕ አዴግ አባላት ለሁለት መከፋፈላቸውን የዘ-ሐበሻ የውስጥ ምንጮች አስታወቁ::

እንደምንጮቻችን ገለጻ በኢሕ አዴግ ውስጥ የተፈጠረው ክፍፍል የፕሬዚዳንቱን መምጣት ተከትሎ የዓለም ታላላቅ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን ዲሞክራሲና ሰብአብዊ መብት አያያዝ በከፍተኛ ሁኔታ መተቸታቸውና ኢሕ አዴግ 100% አሸንፍኩ የሚለውን ምርጫ መሳቂያ ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው:: በተጨማሪም ኢሕአዴጎች ባራክ ኦባማ እንደ አርበኞች ግንቦት 7 እና ኦነግን የመሳሰሉ መሳሪያ አንስተው ድርጅቱን ለመጣል የሚንቀሳቀሱትን ድርጅቶች አሸባሪዎች እንዲልላቸው ፈልገው የነበረ ቢሆንም ፕሬዚዳንቱ እነዚህን ድርጅቶች በአሸባሪነት አለመፈረጃቸው በኢህ አዴግ አባላት ዘንድ ከፍተኛ የፖለቲካ ክስረትን አስከትሏል::

የኦባማን ወደ ኢትዮጵያ መሄድ ተከትሎ በኢሕአዴግ የይስሙላ የ100% የአሸንፌያለሁ የምርጫ ውጤት የተሳለቁት ከሱዛን ራይስ ጨምሮ የዓለም ታላላቅ ሚዲያዎች ሲሆኑ እነዚህም ሚድያዎች የኦባማን ኢትዮጵያ መሄድ ተከትሎ በምርጫው ውጤት ከመሳለቃቸው በተጨማሪ በሃገሪቱ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብት አያያዝ መዘገባቸው አንዳንድ የኢሕ አዴግ አባላት “የኦባማ መምጣት በውጭ ሚድያዎች አጋለጠን; ለተቃዋሚዎች ጥቂት ወንበር ብንሰጥ ኖሮ ከዚህ ውርደት እንተርፍ ነበር” በሚል አቋም መከፈላቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል::


ሲኤን ኤን; ዘጋርዲያን; ዩኤስ ኤ ቱደይ; ያሁ ኒውስ; ሮይተርስ; ፎክስ; ኤ ኤፍ ፒ: ኤፒ; ኤቢሲ; ኤንቢሲ; ፖለቲኮ; ቢቢሲ; ኤንፒአር; ኤቢሲ; አልጀዚራን ጨምሮ በየዓለማቱ ያሉ ትላልቅ ሚድያዎች የሕወሓት/ኢሕ አዴግን የሰብ አዊ መብት አያያዝና መሳቂያውን ምርጫ የኦባማን ጉብኝት ተከትሎ እያነሱ በሰፊው ተችተውበታል:: በዚህም የኢሕ አዴግ አባላት ደስተኛ እንዳልሆኑ ተገልጿል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45419

Saturday, July 25, 2015

የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ

በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ በሽብርተኝነት የተከሰሱት 16 የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ሀምሌ 17/2007 ዓ.ም የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ አመራሮቹ ሀምሌ 1/2007 ዓ.ም በጠበቆቻቸው በኩል የክስ መቃወሚያና የዋስትና ጥያቄ አቅርበው፣ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም አቃቤ ህግ ለጥያቄው መቃወሚያ እንዲያሰማ ቀጠሮ ተሰጥቶት ተቃውሞ ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ በመሆኑም የተከሳሾቹ ጠበቃዎች ደንበኞቻቸው በሽብር ወንጀል ያልተሳተፉ በመሆናቸው በሽብር ወንጀል መከሰሳቸው ትክክል አለመሆኑን፣ ቢቻል ክሱ ተዘግቶ እንዲሰናበቱ፣ ይህ ባይሆን እንኳ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆላቸው በውጭ ሆነው እንዲከራከሩ ያቀረቡትን ጥያቄ መሰረት አድርጎ ብይን እንዲሰጥላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ለዛሬ ተቀጥሮ ነበር፡፡ ይሁንና ዛሬ ሀምሌ 17/2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቤት 14ኛ ምድብ ችሎት በዋለው ችሎት ፍርድ ቤቱ ‹‹በመረጃ የሚረጋገጥ ይሆናል›› በሚል ጠበቆች ያቀረቡትን መቃወሚያ ውድቅ አድርጓል፡፡

ፍርድ ቤቱ የክስ መቃወሚያውን ውድቅ ካደረገ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ በጠየቀው መሰረት 16ቱም አመራሮች የተከሰሱበትን ወንጀል አልፈፀምንም ሲሉ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ ከተከሳሾቹ መካከል የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አቶ አግባው ሰጠኝ‹‹የታ ሰርኩት የመተማ መሬት ለሱዳን መሸጡን በመናገሬ ነው፡፡ ትናንትም መሬቱ መሸጡን ስናገር ቆይቻለሁ፡፡ ወደፊትም እናገራለሁ፡፡ የተከሰስኩት በመሬቱ ጉዳይ ነው እንጅ አሁን የተከሰስኩበትን ወንጀል ፈጽሜ አይደለም፡፡›› ሲል የእምነት ክህደት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ ተከሳሾቹ የመኢአድ፣ የቀድሞው አንድነትና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ናቸው፡፡
በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ የተከሰሱት አመራሮች፡-

1ኛ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን
2ኛ በላይነህ ሲሳይ
3ኛ አለባቸው ማሞ
4ኛ አወቀ ሞኝሆዴ
5ኛ ዘሪሁን በሬ
6ኛ ወርቅየ ምስጋናው
7ኛ አማረ መስፍን
8ኛ ተስፋየ ታሪኩ
9ኛ ቢሆነኝ አለነ
10ኛ ተፈሪ ፈንታሁን
11ኛ ፈረጀ ሙሉ
12ኛ አትርሳው አስቻለው
13ኛ እንግዳው ቃኘው
14ኛ አንጋው ተገኘ
15ኛ አግባው ሰጠኝ
16ኛ አባይ ዘውዱ ናቸው፡፡



በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ የተከሰሱት 16 የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የአቃቤ ህግን ምስክር ለመስማት ለነሃሴ 12ና 13/2007 ዓ.ም ተቀጥረዋል፡፡ በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት በልደታ ፍርድ ቤት የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ተቀጥረው የነበሩት እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለሀምሌ 28/2007 ዓ.ም ተቀጥረዋል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45344

Thursday, July 23, 2015

ርዕዮት ዓለሙ ምስጋና አቀረበች ፡፡

የፕሬስ ነፃነትን በማፈንና የሰብአዊ መብትን በመርገጥ የሚታወቀው የኢህአዴግ መንግስት የፈፀመብኝን እስር በመቃወምና በማውገዝእንዲሁም ያለቅድመ ሁኔታ እፈታ ዘንድ በመጠየቅ ከጎኔ ለነበራችሁ በሙሉ ምስጋናዬን የማቀርበው በታላቅ ትህትናና አድናቆት ነው፡፡
ርዕዮት ዓለሙ ከእህቷ እስከዳር ዓለሙ ጋር ከ እስር ከተፈታች በኋላ

በነዚያ የጨለማ ቀናት አብሮነታችሁ ያልተለየኝ አለምአቀፍና ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡
ዩኔስኮ፣ አለምአቀፍ የሴቶች ሚዲያ ፋውንዴሽን፣ ሚዲያ ሌጋል ዲፈንስ ኢንሼቲቭ፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ ሂዩማን ራይትስዎች፣ ሲፒጄ፣ ፔን ኢንተርናሽናል፣ ዶሀ ፍሪደም ሴንተር፣ አርቲክል 19ንና ሌሎች ያልጠቀስኳችሁ በርካታ አለምአቀፍ ድርጅቶች ለጉዳዬ የሰጣችሁት ትኩረት በኢትዮጵያ ያለውን አምባገነን ስርዓት በማጋለጥ በኩል ትልቁን ድርሻ ተጫውቷልና ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርብላችኋለሁ፡፡


መፈታቴን እንደራሳቸው ጉዳይ ቆጥረው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እንደ ማርቲን ሽቢዬ፣ፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም፣ አና ጎሜዝ፣ ናኒ ጃንሰን፣ ክርስቲያን አማንፑርና ሌሎች ዘርዝሬ መጨረስ የማልችላቸው በርካታ ግለሰቦች ለጉዳዩ የነበራቸውን ጠንካራ መሰጠት አብዝቼ አደንቃለሁ፡፡

ምንም እንኳን በአስከፋ ሁኔታ ተገልዬ የቆየሁባቸውና ጤናዬ ተቃውሶ የነበረባቸው መጥፎ ጊዜያትን ያሳለፍኩ ቢሆንም ከእስር የወጣሁት ግን ሁኔታዎቹ ሞራሌን ሳይሰብሩትና ይልቁንም ለዲሞክራሲ በተለይ ደግሞ ለፕሬስ ነፃነት መከበር የምችለውን ሁሉ ለማድረግ የበለጠ ቁርጠኝነት ኖሮኝ ነው፡፡

በመሆኑም ለዲሞክራሲ ስለታገሉና ሀሳባቸውን ስለገለፁ ብቻ በኢትዮጵያ እስር ቤቶች ካለምንም ጥፋታቸው ታስረው የሚሰቃዩ በጣም ብዙ አርበኞችና ጓዶች ከሀሳቤ አይለዩም ፡፡ ኢፍትሀዊነትን አምርራችሁ የምትጠሉ ኢትዮጵያዊያንም ሆናችሁ የሌላ ሀገራት ዜጎች ለነዚህ ሰዎች መፈታት ያላሳለሰ ጥረት ታደርጉ ዘንድ እጠይቃለሁ፡፡

በድጋሚ አመሰግናለሁ
ርዕዮት አለሙ


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45297


Wednesday, July 22, 2015

የነአብርሃ ደስታ ክስ መከላከያ እና በእነ ወይንሸት ላይ የተጠየቀው ይግባኝ ውድቅ ተደረገ !

በእነ ዘላለም ወርቃገኘው የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻቸው ላይ በቀረበባቸው የክስ ማስረጃ ላይ ያቀረቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው ተከሳሾቹ ሀምሌ 1/2006 ዓ.ም ተይዘው ከሶስት ወር በኋላ ጥቅምት 7/2006 ዓ.ም ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተገኘ የተባለ መረጃ ከአቃቤ ህግ ማስረጃዎች ማስረጃ ዝርዝርነት እንዲወጣ፣ ተከሳሾቹ ለፖሊስ መረጃ የሰጡበት መንገድና ፖሊስ የሰነድ ማስረጃዎችን የያዘበትን መንገድም አቃቤ ህግ ህጋዊ መሆኑን ስላላረጋገጠ በደንበኞቼ ላይ በማስረጃነት እንዳይያዝ ሲሉ መቀወወሚያ አቅርበው ነበር፡፡

ከተከሳሾቹ መካከል በዛሬው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹መቃወሚያው የቀረበው ከተከሳሾች እጅ ተገኙ የተባሉት ማስረጃዎች በህጋዊ መንገድ የተገኙ ስለመሆናቸው አቃቤ ህግ በማስረጃ ስላላረጋገጠ ነው›› ሲል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን እንዲቀበለው ጠይቋል፡፡ ሆኖም ዛሬ ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መቃወሚያውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በነፃ ይሰናበቱ ወይንም ይከራከሩ የሚለውን ለመወሰን ለብይን ለነሀሴ 14/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡


በዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም 9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ ከጥብቅና በመታገዳቸው ምክንያት ሰባቱም ተከሳሾች በዛሬው ችሎት ያለ ጠበቃ ቀርበዋል፡፡ በዚህ መዝገብ ተከሰው አቶ ተማም መቃወሚያ ካቀረቡላቸው መካከል አቶ የሸዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሽ ይገኙበታል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45237

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45259

Saturday, July 18, 2015

ማሰር፣ ማሽበር፣ ማወክ የማይሰለቸው ግፈኛ አገዛዝ


ገዢው ፓርቲ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ማሻሻያዎች አድርጎ ለብሄራዊ መግባባት ራሱን እንዲያዘጋጅ ከተለያዩ ማእዘናት ጥሪ ቀርቦለታል። የሕሊና እስረኞችን እንዲፈታ በተደጋጋሚ ተጠይቋል። ሆኖም አገዛዙ እንኳን ሊሰማ እንደዉም በጣም እየባሰበት መጥቷል። ዜጎችን በማሰርና በማሸበር የሚረካው አገዛዝ ዛሬም በወገኖቻችን ላይ የሰቆቃ በትሩን እየያሳረፈ ነው።

ወደ ብሄራዊ መግባባት እንዲመጣ በስፋት ጥሪ እየቀረበለት ቢሆንም አገዛዙ እንደ አበደ ዉሻ፣ እንደዉም ጭካኔዉንና ግፈኝነቱ በጣም ጨምሯል። ዜጎችን ማሰር፣ መግደል፣ ማሸበሩን አጧጡፎታል። ብዙዎች ያለ ምንም ማስርጃ ታስረው በወህኒ እየማቀቁ ነው። ከነዝኢኡህ መካከል አንዱ የሁለት ልጆች አባትና የአንዲት መልካም ኢትዮጵያዊት ባለቤት ስንታየሁ ቸኮል ነው።

ስንታየው ድብቅ ነገር አይወድም። ንግግሩ ቀጥተኛ ነው። ሐሳቡን የመሰለዉን ከመናገር ወደ ኋላ የማይል ነው። ሞትና መታሰርን በጭራሽ የማይፈራ ፣ አገሩን የሚወድ ጀግና ኢትዮጵያዊ ። እርሱ በመታፈኑ፣ በዜጎች ስቃይ የሚደሰቱ እንደመሆናቸው፣ አሳሪዎቹ ሊደሰቱ ይችሉ ይሆናል። በሺዎች የምንቆጠር የትግል አጋሮቹ ደግሞ ልናዝን እንችላለን። ከስንታየው ጋር ወዳጅ ነኝ። ስለ ስንታየሁ ብዙ አወቃለሁ። አንድ ነገር አስረግጬ የምናገረው ነገር ቢኖር፣ ስንታየው ለአገርና ለህዝብ ሲል መታሰርን እንደ ትልቅ ጸጋና ክብር የሚቆጠር፣ ወኔና ጀግንነት የተሞላ ኢትዮዮጵያ ካፈራቻቸው ብርቅዬ ታጋዮች መካከል አንዱ መሆኑን ነው።

ስንታየሁ ወያኔ ራሱ በጠራው ሰልፍ ላይ አምጽ ቀስቅሰሃል በሚል ነው ያሰሩት። ምንም አይነት የሕግ ጁደት ሳይደረግ፣ ምስክሮች ሳይሰሙ ነው የስድስት ወራት እስራት በጥቂት ቀናት ዉስጥ የተፈረደበት። ቤተሰብ እንዳይጠይቀው፣ የአዲስ አበባ ንዋሪ ሆኖ ሸዋ ሮቢት ወስደው አሰሩት። (የጎንደርና የጎጃምምም እስረኞችን አዲስ አበባ አምጥተው እንደሚያስሩት) ።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ስንታየው ቸኮሎች፣ አሏት። «ታጋይ ቢሞት ትግል አይሞትም» ነበር የሚባለው። ታጋይ ቢታሰርም ትግል አይታሰርም። ብርቱካን ሚደቅሳን አሰሩ፤ እነ አንዱዋለም፣ እነ እስክንደር ተነሱ ። እነ አንዱዋለም ሲታሰሩ እነ ሃብታሙ ፣ ዞን ዘጠኞች ተነሱ። እነ ሃብታሙ ሲታሰሩ ደግሞ እነ መሳይ ምትኩ እነ ስንታየሁ ተነሱ። የሕዝብ መሰረታዊ የለዉጥ ጥያቄ በኃይል ማፈን በጭራሽ አይቻልም።

ለተቀረነው እንዲህ እላለሁ። ብናዝን ማዘናችን ተገቢ ነው። ሆኖም የነስንታየው መታሰር፣ እኛ አዝነን እንድንቀመጥ ሳይሆን ለነጻነት የሚደረገዉን ትግል የበለጠ አጧጡፈን እንድንቀጥል ሊገፋፋን ይገባል። የበለጠ አንድነታችን እያጠናከርን፣ ገዢው ፓርቲ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ከሁላችንም መስማት መጀመር አለበት። በየቀበሌያችን ፣ ትምህርት ቤታችን፣ ሰፈራችን፣ እድሮቻችን … እየተደራጀን እንቅስቃሴዎችን እናድርግ። እንመካከር። እንነጋገር። ሀዘናችንን ወደ ተግባር እንለዉጥ።
የሕሊና እሥረኞች በሙሉ እስኪፈቱ ትግሉ ይቀጥላል !!!!!
http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/18213#more-18213

Friday, July 17, 2015

ከደርግ የባሰ ግፍ በጎንደር

ወያኔ/ኢሕአዴግ “ብሶት ነው የወለደኝ” በሚል ደርግን በሚዋጋበት ጊዜ፣ መንገድ አሳልፎ ወደ መሃል አገር እንዲገባ ያደረገው የጎንደር ሕዝብ ነበር። በመላኩ ተፈራና በደርግ መከራን ያየና በመከራ የተማረረ ህዝብ፣ የተሻለ ሊመጣ ይችላል በሚል ነበር ወያኔን አሳልፎ ያስገባው።

ሆኖም ጎንደሬው ከደርግ የባሰ ግፍና መከራ እየደረሰበት ነው። ደርግ ያላደረገው በደል ህዝቡ እየተፈጸመበት ነው። ገበሬው ከምርታማ የጎንደር መሬት በኃይል እየተፈናቀለ ፣ ለአገዛዙ ቅርበት ላላቸው ኢንቨርስትሮች መሬቱ እየሰጠበት ነው። ሰሊጥ የመሳሰሉት የሚያበቅለው ለምለሙ መሬት በኢንቨርስተሮች ሕግ ወጥና ጸረ-ሕዝብ በሆነ መንገድ እየተወረረ ነው። ይሄን አይነት ዜጎችን ማፈናቀል ደርግ እንኳን ያልፈጸመው ግፍ ነው።
በምእራብ ወያኔ ገበሬዎችን ቀምቶ የጎንደርን መሬት ለሱዳን አሳልፎ እየሰጠ ነው። ይሄንን በደርግ ጊዜ ያልታየ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥም መቆም ሳይሆን አገርን መሸጥ መሆኑን የሚያሳይ ነው።
ሕዝቡ ለመብቱ፣ ለክብሩ፣ ለነጻነቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄ ሲያነሳ ደግሞ እየተደገደል፣ እየታሰረ፣ ክፍተኛ እንግክትና መከራ እየደረሰበት ነው። በኢትዮጵያ በሰለጠነ መልኩ በሰላም ለዉጥ እንዲመጣ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጋዮች ብዙዎቹ ሲሰደዱ፣ ብዙዎቹ ወህኒ ወርደዋል። በአንድነት ፓርቲ ሥር በጎንደር ክፍል ሃግር ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ ጀግና ወገኖቻችን መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።

1. ኣንጋው ተገኝ (ሰሜን ጎንደር)
2. አባይ ዘዉዱ (አብርሃ ጅራ ጎንደር)
3. እንግዳው ዋኘው (አብርሃ ጅራ ጎንደር)
4. በላይነህ ሲሳይ (መተማ ጎንደር
5. አለባቸው ማሞ (መተማ ጎንደር)
6. አለበል ዘለቃ ሃይማኖት አየና ( ውሮታው፣ ደቡብ ጎንደር)
7. ጸጋዬ ገበይየሁ (አርማጭሆ)
8. መምህርት ግዛው ( ሰሜን ጎንደር)
9. አውቀ ብርሃኑ (ጎንደር)
10. ማሩ አሻግሬ ( የአርማጭሆ ተወላጅ፣ የዞኑ የአንድነት አመራር – ቀይ የለበሰው))
11. አለላቸው አታለለኝ ( የሰሜን ጎንደር አንድነት ሰብሳቢ)
12. አስቴር ስዩም ( በጎንደር የምእራብ አርማጮሆ የአንድነት አመራር)
http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/18207

Thursday, July 16, 2015

ፌደራል ፖሊስ ባራክ ኦባማ ላይ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ተዘጋጅተው ነበር ያላቸውን አሰረ በክሱ ውስጥ ጋዜጠኛ ይገኛል


የአሜሪካው ፕሬዘዳንት የኢትዮጵያ ጉብኝት ሰርግና ምላሽ በኢትዮጵያ ከወዲሁ የተወሰኑ እስረኞችና በመፍታትና ብዛት ያላቸውን የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን በማሰር ወደ ቀኑ እየገሰገሰ ይገኛል፡፡የሰማያዊና የቀድሞው አንደነት አመራሮችና አባላት ኦባማ ወደ አገራችን ሲመጡ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እያሴራችሁ እንደሆነ ደርሰንበታል በማለት ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ባሳለፍነው ሐሙስ የሞያ አጋሮቹ መፈተታት የፈጠረበትን ደስታ አጣጥሞ ሳይጨርስ በቁጥጥር ስር የዋለው ጋዜጠኛ ሐብታሙ ምናለ ከአምስት ቀናት የእስር ቤት ቆይታ በኋላ ዝግ ችሎት ተሰይሞ በፖሊስ የ15 ቀናት የምርመራ ጊዜ ተጠይቆበት ያቀረበው የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደርጎበት ወደ እስር ቤት እንዲመለስ መደረጉ አይዘነጋም፡፡



የአንድ ሳምንት የህትመት ብርሃን ካየች በኋላ በስርዓቱ ስልታዊ አፈና ዕድሜዋ እንዲቀጭ የተደረገችውን ‹‹ቀዳሚ ገጽ››ጋዜጣ በስራ አስኪያጅነት የመራት ሐብታሙ ‹‹የሚልዮኖች ድምጽ ››ጋዜጣ ላይ በሪፖርተርነት ሰርቷል፡፡አስቂኙ የእስር ክስ እንደቀረበበት ከመደመጡ አስቀድሞም ‹‹ለጥያቄ እንፈልግሃለን››ባሉት ደህንነቶች ተይዞ ቃሉን እንዲሰጥ ከተደረገ በኋላ መለቀቁ ይታወሳል፡፡ የሞያ አጋራቸው ከታሰረበት ዕለት አንስቶ የእስሩን ምክንያት ለማወቅ ሲታትሩ የነበሩት ጋዜጠኞች ኤልያስ ገብሩና ኢዮኤል ፍስሐ ለማመን የከበዳቸውን የፈጠራ ክስ ከራሱ ከሐብታሙ አንደበት አዳምጠው ተመልሰዋል፡፡ሐብታሙ ‹‹የአልሻባብ የሽብር ቡድን አባል በመሆን የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ጥቃት ለመፈጸም ስትንቀሳቀስ ነበር››መባሉን ነግሯቸዋል፡፡ የፈጠራ ክስ በገዛ ዜጎቹ ላይ በማቅረብና በማስወንጀል የዳበረ ሪከርድ ያለው የፌደራሉ ፖሊስ ጋዜጠኛውን ለሽብር ድርጊቱ ተዘጋጅተው ያዝኳቸው ካላቸው 44 ተጠርጣሪዎች ጋር በአንድ መዝገብ ማቅረቡም ነገሩን አሳዛኝም አሳፋሪም ያደርገዋል፡፡ከተጠርጣሪዎቹም መካከልም የሶሪያና ሶማሌያዊ ዜግነት ያላቸው ስዊዲናዊያን እንደሚገኙበት ኦባማ ላይ ጥቃት ለማድረስ አሴረሃል የተባለው ሐብታሙ ተናግሯል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45091

Wednesday, July 15, 2015

በሕወሓት $5 ሺህ ዶላር የተደለለው ድምፃዊ ደረጀ ደገፋው በዲሲ ከፍተኛ መገለል እየደረሰበት ነው

የሕወሓት መንግስት በሰሜን አሜሪካ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ላይ አንጃ በመፍጠር በስርዓቱ ደጋፊ በሼህ መሀመድ አላሙዲ ሌላ ፌዴሬሽን አቋቁመው በኢትዮጵያውያን ቦይኮት መደረጋቸው ይታወሳል:: ከአንድ ዓመት በፊት የወያኔ መንግስት በሚኒሶታ ባዘጋጀው የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ትናንት ሃገር ወዳድ በመምሰል ስለታማኝ በየነ ጀግንነት እያወደሰ ሲዘፍን የነበረው ድምፃዊ ደረጀ ደገፋው ከአላሙዲ የተከፈለው 5 ሺህ ዶላር በልጦበት ሃገር ወዳዱን ኢትዮጵያዊያን ክዶ ተገኝቶ ነበር::

ይህ ድምፃዊ ለገንዘብ ራሱን በማስገዛቱ እጅጉን በ”መጸጸቱ” በዲሲ ባሉ ራድዮኖችና ዲሲን መሠረት ባደረጉ ሚድያዎች እንዳይዘገብበት አርቲስት ታማኝ በየነ እና አበበ በለው እግር ስር መውደቁ ይነገራል:: በወቅቱ የደረጀ ደገፋው ለገንዘብ ሲል ለወያኔ ፌስቲቫል ማድመቂያ መሆኑን እነዚሁ ሚድያዎች ዝም ብለውለት አለፉ:: ሆኖም ግን ሕዝቡ ዝም አላለም:: ይበላበት የነበረበት ሬስቶራንትና የሚውልበት አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያውያን ለገንዘብ ሲል ለወያኔ ራሱን የሸጠ እያሉ ማግለል ጀመሩ::

ድምፃዊው ቀጥሎም የአምናው ሳያንስ ዘንድሮም ሕወሓት በአላሙዲ ስፖንሰርነት ዴንቨር ላይ ባደረገውና ቦይኮት በተደረገው ኳስ ጨዋታ ላይ ዘፍኖ ተመልሷል:: ትናንት እነ አቦነሽ አድነውን ቦይኮት አስደርገው ሬስቶራንቷን እንድትዘጋ ያደርጉ የዲሲ ራድዮ ጣቢያዎችና አክቲቭስቶች ደረጀ ደገፋውን ዝም ቢሉትም ሕዝቡ ግን ድምፃዊውን ከማግለል አልተመለሰም:: በዲሲ ብዙ ጊዜ ከሚዝናናበት ካፌ ከሕዝቡ በሚደስበት ተቃውሞ ለመቅረት ተገዷል:: በአሁኑ ወቅት ይህ ድምጻዊ ራሱን ከኢትዮጵያውያን እየደበቀ ለታማኝ ዘፍኖ ያገኘውን ክብር በሕወሓት $5 ሺህ ዶላር ሸጦታል::


ማሳሰቢያ በተለይ ለዲሲ ራድዮኖችና አክቲቭስቶች:- ከወያኔ ጋር ያበረውን ድምፃዊም ሆነ አርቲስት ቦይኮት ማድረጋችሁን እኮራበታለሁ:: ሆኖም ግን ከአንድ አካባቢ ነው የመጣነው በሚል ከወያኔ ጋር ያበረውን አርቲስትም ዝም አትበሉት:: ዘር ቆጠራ ውስጥ ከገባችሁ እናንተም ከወያኔ አትሻሉም::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45049

Monday, July 13, 2015

የአንድዋለም ወንጀል አገሩን መዉደዱ ነው

አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ በነአንዱዋለም አራጌ ላይ ክስ ያቀረበ አቃቤ ሕግ ነው። ይህ የሕግ ሰው ነኝ ባይ ካድሬ፣ በወያኔ ኢቲቪ ቀርቦ «አንዱዋለም አራጌን በተመለከተ፣ የግንቦት ሰባትን ተእልኮ ለማስፈጸም አገር ዉስጥ በሕቡእ (ስዉር) ይንቀሳቀሳል። በሰላማዊ ትግል እንታገላለን የሚሉ የፓርቲዎችን ሽፋን አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረ በመሆኑ በቂ ማስረጃ አቅርበናል» ሲል ነበር የተናገረው።

አንዱዋለም ያደረጋቸው የነበሩ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ሲያደርግ የነበረው በግልጽና በገሃድ ነዉ። ለተለያዩ ፓልቶክ ክፍሎች፣ አገር ዉስጥና በዉጭ ለሚገኙ ሜዲያዎች በርካታ ቃለ መጠይቆችን ሰጥቷል። በአገር ቤት፣ በአንድነት ፓርቲ ዉስጥ ሆነ በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ ዉይይቶችና ስብሰባዎች ያቀረባቸው ንግግሮች በሙሉ የተደበቁ አይደሉም። ዉጭ ካሉ ኢትዮጵያዊያን ጋር ብዙ ጊዜ በስልክ ሃሳቦችን ተለዋዉጧል። በስልክ ያደረጋቸው ንግግሮችም፣ 24 ሰዓት የሰላማዊ ተቃዋሚ መሪዎችን ስልክ በሚጠልፈው ቴሌ ዘንድ የተሰሙ ናቸው። ቤቱና ቢሮዉ ከላይ እስከ ታች ተበርብረዉ ፣ የሚስጥራዊ የኮሚኒኬሽን መሳሪያዎች፣ ቦምቦች፣ ፈንጂዎች፣ ሚስጥራዊ ሰነዶች አልተገኙም። ኤሜሎቹ በሙሉ ተነበዋል። አንዱዋለምን ከግንቦት ሰባት ጋር የሚያገናኝ፣ በሕቡእ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ የሚያመለክት አንዳች መረጃ አቃቤ ሕግ አላቀረበም። መረጃዎች ቢኖሩ ኖሮ፣ «እንኳን ዘንቦብሽ ድሮም ጤዛ ነሽ» እንደተባለ፣ ዜጎችን በማዋረድና በማሳነስ የሚታወቀዉ የወያኔ ኢቲቪ፣ ይሄን በስፋት ያወራልን ነበር።

አንዱዋለም አራጌ ከታሰረ በኋላ አቃቤ ሕጎች መረጃ ማቅረብ ባለመቻላቸው፣ የዉሸት መረጃዎች ማሰባሰብ የግድ ሆነባቸው። የታሰሩ ሌሎች የአንድነት አባላትን ማግባባት ጀመሩ። «በአንዱዋለም ላይ እኛ ተናገሩ የምንላችሁን ከተናጋራችሁ እንፈታቹሃለን» ብለው እጆቻቸዉን ጠመዘዙ። ብዙዎች በአንዱዋለም ላይ የዉሸት መረጃ ማቅረቡ ሕሊናቸውን ስለከበደው ፍቃደኛ አልሆኑም። ነገር ግን ተስፋሁን አናጋው፣ የሚባል ደካማ ሰው ተገኘና የዉሸት ምስክርነት ቀረበ። እንግዲህ በአገዛዙ ካድሬዎች ተቀናብረው ከቀረቡ የዉሽት ምስክርነቶች ዉጭ፣ ቅንጣት የምታክል፣ አንዱዋለምን ሽብርተኛ ወይንም ከግንቦት ስባት ጋር የሚሰራ መሆኑን የሚያሳይ መረጃ አልቀረበም። ወያኔዎች በዉሽት ምስክርነት ነው የእድሜ ልክ እስራት የበየኑበት።

የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ለአገር ማሰብ፣ ለመብት መቆም፣ “አንዲት ኢትዮጵያ” ማለት ወንጀል የሆነበት ኢትዮጵያ ናት። ብርቅዬ የተማሩ፣ ከራሳቸው ይልቅ ለሌሎች የሚያስቡ ልጆቿ ወደ ወህኒ የሚወረወሩባት አገር ናት። አሳዛኝ አገር ሆናለች።

ሆኖም ተስፋ የሚሰጡ ብዙ ነገሮች እየታዩ ነው። አንዱዋለም አራጌ ቢታሰርም፣ እጅግ በጣም ብዙ አንድዋለም አራጌዎች ፈርተዋል። እንደ ሃብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ አንጋው ተገኝ፣ ገበየሁ ሲሳይ፣ ስንትየሁ ቸኮል፣ ሃዲያ ሞሃመድ፣ መሳይ ተኩ ..የመሳሰሉ የአንድነት ሰዎች አንዱዋለም አራጌን በወህኒ ተቀላቅለዋል። ሆኖም ሌሎች ብዙ ከየቦታው እየተነሱ ነው። ታጋይ ቢታሰር ትግል አይቆምም። ጥቂቶችን በማሰር የነጻነትና የለዉጥ ጥያቄን ማፈን አይቻልም።

በመሆኑም ከአንዱዋለም አራጌ ጎን እንቆማለን። አላማው አላማችን ነው። እነርሱን “ሽብርተኛ” ቢሉትም ለኛ ወንንድማችን፣ ጀግናች፣ መሪያችን ነው። እኛም አንዱዋለም አራጌዎችን ነን። እርሱ በአካል ድምጹን ማሰማት ባይችልምም፣ እኛ እርሱን ሆነ የነጻነትና የፍትህ ድምጽ እንደ መብረቅ እናስተጋባለን።



አንድዋለም አራጌና ሌሎች ጀግኖቻችን በሙሉ እስኪፈቱ፣ አገራችን ኢትዮጵያም ራሷ እስክትፈታ ትግሉ ይቀጥላል!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45004

Sunday, July 12, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ እስሩ ቀጥሏል

በአዲስ አበባና በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ እስሩ ቀጥሏል፡፡ ትናንትናው ዕለት በሸዋ ሮቢት የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች የሆኑት አቶ ዘነበ ደሳለኝ፣ አቶ መንግስቱ ተበጀ፣ አቶ ቴዎድሮስ ሀብቴ እንዲሁም አዲስ አበባ ውስጥ አቶ ደብሬ አሸናፊ ታድነው የታሰሩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አቶ መርከቡ ሀይሌና አናኒያ ኢሳያስ ለእስር ተዳርገዋል፡፡

መርከቡ ሀይሌና አናኒያ ኢሳያስ ዛሬ ሀምሌ 4/2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ አራት ኪሎ አካባቢ በፖሊስና ደህንነቶች ተይዘው ታስረዋል፡፡ እነ መርከቡ በተያዙበት ወቅት ፖሊስና ደህንነቶች ‹‹ብጥብጥ ልታስነሱ እየጣራችሁ መሆኑን ደርሰንበታል›› እንዳሉዋቸው ተገልጾአል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ስለሽ ደቻሳ ሀምሌ 1/2007 ዓ.ም ከቤቱ በደህንነትና በፖሊስ ታፍኖ ከፍተኛ ድብደባ ከተፈፀመበት በኋላ ታስሯል፡፡ ስለሽ ደቻሳ በተፈፀመበት ድብደባም እጅና እግሩ ላይ ስብራት እንደደረሰበት ታውቋል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢ የነበረው አስፋው ጀማል በትናንትናው ዕለት በፖሊስ ተይዞ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ መርከቡ ኃይሌና አናኒያ ኢሳያስ በአራዳ ፖሊስ መምሪያ እንዲሁም ስለሽ ደቻሳ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደታሰሩ ታውቋል፡፡


በተመሳሳይ እስሩ በየ ክፍለ ሀገሩን የቀጠለ ሲሆን በከፋ ዞን ጨላ ወረዳ 8 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ‹‹ማዳበሪያ አልወስድም ብለዋል›› በሚል ለእስር እንደተዳረጉ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በማዳበሪያ ሰበብ ድብደባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የገለጹት የዞኑ የፓርቲው አስተባባሪዎች ነሲብ አደነ የተባለ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት ሆስፒታል ውስጥ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

http://satenaw.com/amharic/archives/8587

Wednesday, July 8, 2015

በወልቃይት ማይምቧ በተባለ አከባቢ የተከፈተው ከበድ ያለ ውጊያ ለ6ኛ ቀን ዛሬም ቀጥሏል

ውጊያው ለ6ኛ ቀን ቀጥሏል በወልቃይት ማይምቧ በተባለ አከባቢ ከበድ ያለ ውጊያ መደረጉን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት መረጃ ክፍል የደረሰን ዜና ያመለክታል:: በትላንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ በ12 አውቶብሶች የተጫኑ ወታደሮች ወደ ወልቃይት በተለይም ውጊያው ወደበረታባቸው አከባቢዎች እንደተጓጓዙ ለማወቅ ተችሏል:: በቃፍቲያ እና አብርሃጅራር የማጥቃት እርምጃ ተውስዶ በመንግስት ሰራዊት ላይ ጉዳት መድረሱን የአከባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል:: በሰሜን ኢትዮጵያ የጦርነት እንቅስቃሴ እየታየ ነው::

በወልቃይት ማይምቧ በተባለ አከባቢ ከበድ ያለ ውጊያ መደረጉን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት መረጃ ክፍል የደረሰን ዜና ያመለክታል:: በትላንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ በ12 አውቶብሶች የተጫኑ ወታደሮች ወደ ወልቃይት በተለይም ውጊያው ወደበረታባቸው አከባቢዎች እንደተጓጓዙ ለማወቅ ተችሏል::


አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ጥቃት ለኤርትራ መንግስት ሸለሙት:: የኢትዮጵያን ህዝብ አስፈቅደን እርምጃ እንወስዳለን አሉ::የመከላከያ ሰራዊት አባላት አፈሙዛቸውን ወደ አፋኙ ስርዓት ማዞር አለባቸው የሚል ጥሪ እየቀረበ ነው:: ከኤርትራ መሬት ተነስቶ እየተፋለመ ወዳለው የኢትዮጵያ የነጻነት ሃይል ጥይት መተኮስ እንደሌለባቸው ከየአቅጣጫው ጥሪ እየቀረበ ነው::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44887

Tuesday, July 7, 2015

በአፋር ክልል ወጣቶች ለውትድርና በግዴታ እየታፈሱ ነው


በአፋር ክልል የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ መንግስት የአፋር ህዝብን ደካማ ጎኑን በመጠቀም ወጣቶችን ለውትድርና እያፈሰ ይገኛል።

አለም አቀፍ የምግብ ተረድዖ ድሪጅት በእንግለዘኛ ምህጻሩ WFP ( worlid food program ) ለኢትዮጲያ ህዝብ የሚሰጠው የእርዳታ እህል ለውትድር መደልያ በመጠቀም በአፈር ክልል በብዙ ወረዳዎች እርዳታን ለማገኘት ከአንድ አባወራ ቢያንስ አንድ ሰው ለውትርና መመዝግብ አለበት።

የወያኔ መንግስት የመዕራባዊያን ድጋፍ ላለማጣት የገዛ ወታደሮቹን በሰላም አስከባሪነት ሽፋን በሶማሊያ እና በዳርፎር በማሰማራት እየፈጃቸው መሆኑን የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አፈሳው እየተካሄደ ይገኛል።

በአፋር ክልል 80% የሚሆን ህዝብ ከውጭ በሚገኘው እርዳታ የሚተዳደር ሲሆን ወያኔ ይህን ደካማ ጎናቸውን በመጠቀም እርዳታ ለማገኘት አንድ ሰው ከአንድ አባወራ ለውትድርና ስልጠና መመዝግብ አለበት ይላል።

በአፋር ክልል ይህ ህገ ወጥ ድርግት ተግባራዊ የሚሆነው በአብደፓ የአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ መሪነት ስሆን በየቀበሌው አስተዳደሮች አማካኝነት ትዕዛዙ ወደ ህዝብ እንዲወርድ እየተረገ ይገኛል።


በአፋር ክልል ባሉ በ32 ወረዳዎች ይህ ጉዳይ ወቅታዊ እና አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል።


ከአኩ ኢብን አፋር

 http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44858

Friday, July 3, 2015

100% የአንድ ፓርቲ አሸናፊነትን ያረጋገጡትን የምርጫ ቦርድ ቁልፍ ሰው የነበሩትን ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሔርን የኢትዮጵያ ፓርላማ የኢትዮጵያ ሰብኣዊ መብት ኮምሽን ኮምሽነር አድርጎ ሾመ፡፡

ዶ/ር አዲሱ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ቢሆኑም ከህወሃት/ኢህአዴግ ቀጥተኛ መመሪያ በመቀበልና በማስፈጸም ረገድ ቁልፍ ሰው መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ 

በተለይ ተቃዋሚዎች እንዲዳከሙና ትንንሽ ልዩነቶቻቸውን በማጦዝ ፓርቲዎች እንዲናጉና እንዲፈርሱ ከኢህአዴግ ጋር እየተናበቡ የሚሰሩ ሲሆን ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚያቀርቡትንም አቤቱታ በማድበስበስ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡ 

የቦርዱ ሰብሳቢ ፕ/ር መርጋ በቃና፤ ዶ/ር አዲሱ የሚሰጡዋቸውን መመሪያ ተከትለው ከማስፈጸምና ይህንንም የቦርዱ ውሳኔ በማስመሰል ለመገናኛ ብዙሃን ከመናገር በላይ አቅም እንደሌላቸው የጠቆሙት ምንጮቹ ብዙውን ጊዜ ዶክተሩ፣ ፕሮፌሰር መርጋን ከፊት ለፊት በማጋፈጥ ከጀርባ ሆኖ መስራትን የሚመርጡ መሆናቸው ታውቋል፡፡

የምርጫ ቦርድ አባላት በጠ/ሚኒስትሩ አቅራቢነት በፓርላማው የሚሾሙ ዘጠኝ አባላት ያሉት ሲሆን፣ ከነዚህ የቦርድ አባላት መካከል ግማሽ ያህሉ እንኩዋን ብቁ ተሳትፎ እንደሌላቸው ነገር ግን የሚሰጡ ውሳኔዎች እየተላከላቸው እንደሚፈርሙ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ይህ ክንውን ደግሞ በዶ/ር አዲሱ የሚፈጸም ነው ተብሎአል፡፡ 

ዶ/ሩ በቦርዱ ከተሾሙ በሃላ ሁለት ምርጫዎችን በማስፈጸም ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ 99 ነጥብ 6 እና 100 በ 100 እንዲያሸንፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሲሆን ፣ የዛሬው ሹመት ለዚህ ውለታ የተሰጠ ሳይሆን እንደማይቀር ዘጋቢያችን ገልጿል። 

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን በኮምሽነርነት ሲመሩ የቆዩት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ፣ በተለይ ኢትዮጵያ የምትወቀስባቸውና የምትታወቅባቸውን አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ደጋግመው በመካድ የሚታወቁ ሲሆን በተለይ የእስረኞች አያያዝና የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በሚመለከት “ቦታው ድረስ ሄደን አረጋግጠን ችግር የለባቸውም» በማለት በተደጋጋሚ የመንግስትን ድክመት በመከላከል የሚታወቁና የኢህአዴግ ባለውለታ ናቸው። 

http://satenaw.com/amharic/archives/8262

Thursday, July 2, 2015

በምስራቅ ጎጃም ዞን አርሶ አደሮች በጅምላ እየታሰሩ ነው ዜጎች በፖለቲካ አመለካከታቸው ከቀያቸው እየተፈናቀሉ ነው

በምስራቅ ጎጃም ዞን አርሶ አደሮች ‹‹የማዳበሪያ ዕዳ አልከፈላችሁም›› በሚል በገፍ እየታሰሩ መሆኑን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ ወስዳችኋል የተባሉትን የማዳበሪያ እዳ እንዲከፍሉ እየተጠየቁ እንደሆነ የገለጹት ምንጮች በአንድ ቀበሌ ብቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮች በጅምላ መታሰራቸውን ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮች እነሱ ወስደውታል የተባለውን ብቻ ሳይሆን በሞት የተለዩትን ዘመዶችን ዕዳ ጭምር ካልከፈላችሁ ተብለው ለእስር እየተዳረጉ መሆኑም ተሰምቷል፡፡ የጅምላ እስሩ ከሰኔ 15/2007 ዓ.ም እንደተጀመረ የገለፁት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ለሳምንት ያህል የታሰሩት አርሶ አደሮች ሰኔ 21/2007 ዓ.ም ቢለቀቁም ሌላ ዙር እስር በመጀመሩ በርካታ አርሶ አደሮች ለእስር ሰለባ ሆነዋል ብለዋል፡፡

ከእስር በተጨማሪ ‹‹ቤታችሁን እናፈርሳለን!›› የሚል ማስጠንቀቂያ እየደረሳቸው መሆኑን የገለፁት አርሶ አደሮቹ የሚፈፀምባቸው በደል ከምርጫው ጋር የተያያዘና ኢህአዴግን አይደግፍም በሚል ቂም በቀል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል በምስራቅና ምዕራብ ጎጃም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ማሰርና ማዋከብ አሁንም የቀጠለ ሲሆን የእንገድላችኋለን ማስፈራሪያ የደረሳቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ቀያቸውን ጥለው ለስደት መዳረጋቸው ገልጸዋል፡፡ የቀበሌ ሚሊሻና ከወረዳው የተላኩ ቡችሌዎች በሚያደርሱባቸው ዛቻና ማስፈራሪያ ከቀያቸው እንደተፈናቀሉ የገለጹት ቄስ ዋልተንጉስ የሳሙኤል አወቀን አይነት እጣ ፈንታ እንዳይገጥማቸው በመስጋት መሰደዳቸውን ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡ ኢህአዴግን ትቃወማለህ በሚል ከፍተኛ ዛቻ እንደደረሰባቸው የገለፁት ቄስ ዋልተንጉስ ‹‹ከፍተኛ ዛቻና ማስፈራሪያ ሲያደርሱብኝ ቆይተዋል፡፡ አሁንም ቤቴ ድረስ እየመጡ እየፈለጉኝ እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ የሳሙኤል አወቀ አይነት እጣ ፈንታ እንዳይገጥመኝ በመስጋቴ ልጆቼን፣ ሀብትና ንብረቴን ጥዬ መጥቻለሁ›› ብለዋል፡፡


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44761

Wednesday, July 1, 2015

ኢህአዴግ ዲያስፖራውን ለመያዝ ያደረገው ጥረት መክሸፉን ተከትሎ አዳዳስ ስልቶችን እየቀየሰ ነው


ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ዲያስፖራውን በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች ለመያዝ ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት መክሸፉን ተከትሎ ፣ የዲያስፖራውን ቀልብ ሊስቡ ይችላሉ ያላቸውን አዳዲስ ዘዴዎች እያሰላሰለ ነው። 

በቅርቡ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የዲያስፖራ ሳምንት ዝግጅት ዙሪያ አስመልክቶ ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በክልልና በፌደራል ደረጃ ከሚገኙ የዲያስፖራ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ሃላፊዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ፣ በዲያስፖራው በኩል ይታያሉ የተባሉ በርካታ ችግሮች ተዘርዝረው ቀርበዋል። 

የትግራይ ክልል የዲያስፖራ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ገብረመድህን፣ ” ከፍተኛ ወጪ አውጥተን የትግራይ ዲያስፖራዎች /ተጋሩ ዲያስፖራ/ መቀሌ እና አዲስ አበባን ያካለለ የጉብኝት እና የትሃድሶ ፕሮግራም ብናዘጋጅላቸውም የወጣውን ወጪ የሚተካ አንድም የልማት አጋር ማግኘት ሳንችል ቀርተናል ብለዋል።

 በመቀሌ እና አዲስ አበባ ቦታ ለማግኘት ከተመዘገበው ነዋሪ እያስቀደምን የቤት መስሪያ ቦታ እየቆረስን ብንሰጣቸውም፣ በአንድ ጊዜ ሰርተው ሊልኩ የሚችሉትን የቦታ ክፍያ ወደ ቤተሰቦቻቸው አዛውረውት ሂደዋል ሲሉ አክለዋል። 

ትግራይ በአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ ለዲያስፖራ ምቹ የልማት ቦታ ባይሆን እንኳን፣ የትግራይ ዲያስፖራ የሪል ስቴት ግንባታ ማካሄድ ይችል ነበር ያሉት ባለስልጣኑ፣ የእኛ ዲያስፖራ እንደ እስራኤል በበረሃ ማልማትን አለተማረም ሲሉ በምሬት ተናግረዋል። አቶ አብርሃም በአክሱም ብቻ 23 የሚደርሱ የትግራይ ተወላጅ ዲያስፖራዎች በሆቴል ሎጅ እና ቱሪዝም ለመሰማራት መሬት ቢወስዱም ስኬታማ የሆነ ስራ መስራት አልቻሉም ብለዋል።

 በኤምባሲዎች የተመደቡ ዲፕሎማቶች ከዲያስፖራው ጋር ተቀራርበው እንደማይሰሩ የገለጹት አቶ አብርሃም፣ ኤምባሲዎቹና የቆንፅላ ፅህፈት ቤቶቹ የሐበሻ ማህበረሰብ ባለበት አካባቢ ሁሉ ድጋፍ ማድረግ ይገባችሁዋል ብለዋል። 

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ፌይሰል አሊይ ኤምባሲዎችና ቆንፅላ ጽህፈት ቤቶች ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ጋር በቋሚነት የሚገናኙባቸው መድረኮች እስካሁን አለመፈጠራቸውንና ለወደፊቱ እንዲፈጠርና በጋራ ተቀራርበው እንዲሰሩ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ብለዋል። ዳይሬክተሩ በሪፖርታቸው ዲያስፖራውን በተመለከተ ክልሎች መረጃዎችን በወቅቱ አጠናክሮ የመላክ ችግሮች አሉባቸው ያሉ ሲሆን፣ ከትግራይ ክልል በስተቀር በሌሎች ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች አንዳንድ መመሪያዎችን በአፋጣኝ ተቀብሎ ወደ ተግባር በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ ችግሮች አሉ ሲሉ ወቅሰዋል።

 ሪፖርቱን ያቀረቡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ተሳትፎ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ፈለቀ መኮንን በ2007 በጀት አመት ለአባይ ግድብ ግንባታ ከዲያስፖራው ማህበረሰብ በቦንድ ሽያጭና በስጦታ 6 ሚሊዮን 744 ሺ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ መሰብሰቡን ተናግረዋል። ይህ ገቢ በውጭ ከሚኖረው 2 ሚሊዮን 500 ሺ ህዝብ ጋር ሲነጻጻር ኢምንት ነው።

 ኢህአዴግ የዲያስፖራ ቀን በሚል ከነሐሴ 4-10 ድረስ ለማክበር አቅዷል። ወደ አዲስ አበባ ለሚሄዱ ዲያስፖራዎች፣ ከኢምባሲ የድጋፍ ደብዳቤ ካመጡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 50 በመቶ ቅናሽ ያደርግላቸዋል። ኦሮምያ ክልል ደግሞ ለበአሉ ለሚሄዱ የኦህዴድ አባላትና ደጋፊዎች የሆቴል ወጪ እንደሚሽፍን መረጃዎች ያመለክታሉ። 

http://satenaw.com/amharic/archives/8243