Thursday, January 31, 2013


ውሃም በፈረቃ ``ኢትዮጵያ ጂቡቲን ንፁህ ውኃ ልታጠጣ ነው``

በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች የውሃ እጥረቶች እየገጠማቸው መሆኑን ገለጹ። ነዋሪዎች በአካባቢዎቹ የተከሰተው የውሃ እጥረት በእለት ተእለት ህይወታቸው ላይ ተጽእኖ እየፈጠረባቸውን እንደሚገኝ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልገሎት በበኩሉ በአዲስ አበባ በአንዳንድ አካባቢዎች ችግሩ መኖሩንና ለዚህም ውሃን በፈረቃ እያዳረሰ መሆኑን አስታውቋል። በሳምንት ሶስትና ሁለት ሲበዛም አንደ ጊዜ ብቻ ውሃ የሚያገኙ አካባቢዎች እንዳሉም ነው የመስሪያ ቤቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ የተናገሩት።

ከኢትዮጵያ የድንበር ከተማ አንስቶ 70 ኪሎ ሜትር በሚዘረጋ የውኃ ማስተላለፊያ መስመር ኢትዮጵያ ጂቡቲን ንፁህ ውኃ ልታጠጣ ነው፡፡

በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድ የሚመራ የልዑካን ቡድን ባለፈው ሳምንት ይህንን ፕሮጀክት በሚመለከት ከጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ከመከረ በኋላ ይሁንታውን ሰጥቷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት ግንባታውን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ አውጥቷል፡፡

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የሕግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዋሲሁን አባተ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የግንባታው ወጪ በጂቡቲ መንግሥት ይሸፈናል፡፡

ኢትዮጵያ ለጂቡቲ ከምትሰጠው የመጠጥ ውኃ ኪራይ እንደማታስከፍል ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ጂቡቲ ግን ከድንበር እስከ ጂቡቲ ከተማ ለሚዘረጋው የውኃ መስመር የሚወጣውን ወጪ ትሸፍናለች፡፡ ሀዳጋላ የሚባለው አካባቢ የሚገነባው የውኃ ማመንጫ ጣቢያ አንድ መቶ ሺሕ ሜትር ኪዩብ ውኃ የማመንጨት አቅም አለው፡፡

ኢትዮጵያ ለጂቡቲ ውኃ ብቻ አይደለም የሰጠቻት፡፡ ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ውስጥ ሴሮፈታ አካባቢ ስንዴ የሚመረትበት ሦስት ሺሕ ሔክታር መሬት ሰጥታለች፡፡

ይህ መሬት ቀደም ሲል በፕራይቬታይዜሽንና በመንግሥት የልማት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ሥር በሚገኘው የባሌ እርሻ ልማት ድርጅት ይተዳደር ነበር፡፡ መንግሥት ይህንን መሬት በቀጥተኛ ውሳኔ ለጂቡቲ መንግሥት እንዲተላለፍ አድርጓል፡፡ ለስንዴ ምርት ምቹ የሆነው ይህ መሬት ከ60 ሺሕ ኩንታል በላይ ስንዴ እንደሚመረትበት ታውቋል፡፡

‹‹ሴሮፈታ ሞደርን ፋርም ኦፍ ዘ ሪፐብሊክ ኦፍ ጂቡቲ›› በሚል ስያሜ የሚታወቀው ይህ እርሻ፣ በየዓመቱ 2,828 ሔክታር መሬት ታርሶ ስንዴ ይመረትበታል፡፡

ትንሿ የአፍሪካ ቀንድ አገር የሆነችው ጂቡቲ ጠቅላላ ስፋቷ 23,180 ካሬ ኪሎ ሜትር ነው፡፡ ጂቡቲ ለኢትዮጵያ ዋነኛ ወደብ አቅራቢ መሆኗም ይታወቃል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማግኘት ቀዳሚዋ አገር ሆናለች፡፡
    
    Posted By.Dawit Demelash

ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በአራት የሚዲያ ተቋማት ላይ ክሥ መሠረተ

ክሡ ‹‹ሓላፊና ተጠያቂ የሌላቸውን አንዳንድ የመረጃ መረቦች ዋቢ በማድረግ መሠረተቢስ አሉባልታዎችንና የሐሰት ወሬዎችን በማናፈስ የሽግግር ወቅቱ በሰላም እንዳይከናወን ትርምስ መፍጠርና ሕዝብን ማደናገር›› የሚል ነው
‹‹ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀጣይ ጉዞ በማስመልከት ጉባኤዎችን በማድረግ፣ በውስጥም በውጭም ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በመዳሰስና በሐቅ ላይ በመመርኰዝ የ፮ኛው ፓትርያሪክ ምርጫ የሚካሄድበትን ኹኔታ በማመቻቸት ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡›› /የሕዝብ ግንኙነት መመሪያው ለሚዲያ አካላት ካሰራጨው መረጃ/
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት
የመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት መመሪያ ‹‹የሽግግር ወቅቱን በተመለከተ በሚመለከተው አካል መግለጫ ያልተሰጠባቸውን ዘገባዎች እንደተሰጡ አድርገው በማውጣት ግልጽ የኾነ መሠረተቢስ አሉባልታ አናፍሰዋል፤ ሕዝብን አድናግረዋል›› ባላቸው አራት የሚዲያ ተቋማት ክሥ መመሥረቱን አስታወቀ፡፡

ክሥ የተመሠረተባቸው አራቱ የሚዲያ ተቋማት አንድ ሳምንታዊ ጋዜጣ እና ሦስት መጽሔቶች ናቸው፡፡ በስም ዝርዝራቸውም፤
የኛ ፕረስ ጋዜጣ – ዮርዳኖስ ሥዩም ሚዲያ ሓላ/የተ/የግ/ማ
ሎሚ መጽሔት – በዳዲሞስ ኢንትርቴይመንትና ፕሬስ ሥራዎች ሓላ/የተ/የግ/ማ
አርሂቡ መጽሔት – ሳንኮፋ ሓ/የተ/የግ/ማኅበር
ሊያ መጽሔት – ሊያ የኅትመት እና ማስታወቂያ ድርጅት የሚዘጋጁ ናቸው፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ ‹‹የሽግግር ወቅቱን በሰላም ለማሳለፍ ሌት ተቀን ደፋ ቀና›› በማለት ላይ እንዳለ የገለጸው የመምሪያው ደብዳቤ÷ ሕዝብ ክርስቲያኑን ለማደናገር ኾነ ብለው ይንቀሳቀሳሉ ያላቸው ጋዜጠኞች ዓላማ ‹‹በአባቶች መካከል ጸብና ችግር አለ ብሎ አንባቢው እንዲያምንና ቅዱስ ሲኖዶሱን መበታተን›› ነው፡፡ ደብዳቤው አያይዞም እኒህን ጋዜጠኞች ዝም ብሎ መመልከት ‹‹የጥፋታቸው ተባባሪ መኾን ነው፤›› ስለዚህም ‹‹ጉዳያቸውን ወደ ሕግ አካላት ማድረስና ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማተራመስ እያደረጉት ላለው እንቅስቃሴ በሕግ አግባብ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ የግድ ይኾናል፤›› ብሏል፡፡
በሕዝብ ግንኙነት መመሪያ ሓላፊው አቶ እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ኀይለ ማርያም ፊርማ ለሚዲያ አካላት የተሰራጨው ደብዳቤ እንደገለጸው÷ ክሥ የተመሠረተባቸው የግል ሚዲያ ተቋማቱ ‹‹በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም ኾነ በሚመለከታቸው አካላት ማብራሪያና መግለጫ ያልተሰጠበትን›› ዜና የሚያወጡት÷ ‹‹ከልዩ ልዩ የመረጃ መረቦች አግኝተናል›› በሚል ነው፡፡ መመሪያው በስም ለይቶ ያልጠቀሳቸውን ‹አንዳንድ› የመረጃ መረቦች ‹‹ሓላፊና ተጠያቂ የሌላቸው›› ሲል ገልጧቸዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ስማቸውን ለይቶ ያልዘረዘራቸውንና ‹‹ትክክለኛ መረጃን ለሕዝቡ ለማድረስ የሚመለከታቸውን አካላት በማነጋገር እውነተኛ ዜና የሚያስተላልፉ›› የግል ሚዲያ ተቋማትን አድንቋል፤ አመስግኗል፡፡
መረጃን ከትክክለኛው ቦታ በማግኘት ሐቁን ለሕዝብ ማስተዋወቅ ተገቢና ትክክለኛ አሠራር መኾኑን የሕዝብ ግንኙነት መመሪያው ያምናል፡፡ ጎልቶ ከሚሰማውና ብርቱ ሕዝባዊ ግፊት ከሚደረግበት የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነትና ሰላም ጥያቄ አንጻር ‹‹ሐቅ›› የኾነው ነገር አከራካሪ ቢኾንም ሕዝብን ለማሳወቅ፣ ለማስተማር እና ለማሳመን መሥራት የሚገባቸው ሚዲያዎች ትክክለኛ መረጃን ማድረስ እንደሚገባቸው አያጠያይቅም፡፡
ጥያቄው ግና÷ በመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሥር በቅርቡ የተዋቀረውና ስለ ቅ/ሲኖዶሱ ውሎ ይኹን ስለ ጠቅላላ የአስተዳደሩ እንቅስቃሴ መረጃን የመስጠት ግንባር ቀደም ሓላፊነት ያለበት የሕዝብ ግንኙነት መመሪያ በአግባቡ የተደራጀ ነው ወይ? መዋቅራዊ ነጻነት አለው ወይ? መረጃን በተጠየቀ ጊዜ ይኹን በመደበኛ ጊዜ ለመስጠት ብቁ፣ ፍቁድ፣ ድርጁና ዝግጁ ነው ወይ? ከኾነስ ቀጣይነቱን ጠብቆ ቀጥሏል ወይ? የሚሉት ናቸው፡፡
ሌላም ጥያቄ አለ፡፡ በቀናው አስተሳሰብና አሠራር የሚዲያ ጥፋት በሚዲያዊ አሠራርና መንገድ ይታረማል፤ ይቃናል እንጂ በክሥ እና በቅጣት መኾኑ አግባብ ነው ወይ? በተለይም አካሄዷ አስተማሪ እና አርኣያ የኾነችውን ቤተ ክርስቲያናችንን ከሚመራ አስፈጻሚ አካል ክሥንና ቅጣትን ማስቀደም አግባብ ነው ወይ? ከኾነስ የሚዲያ ተቋማቱ መሠረተቢስ የተባለውን መረጃ እንዲያርሙ ትክክለኛው አሠራር ዘርግቶ መረጃውን በመስጠት የሚታረሙበት የትዝብት ጊዜ ተሰጥቷቸዋል ወይ?
ብዙዎች እንደሚያምኑት፣ አስተዳደራዊ አንድነታችንንና የቤተ ክርስቲያናችንን ሰላም በሚመለከት በመስቀለኛ መንገድ ላይ በምንገኝበት በአሁኑ ወቅት÷ በጉዳያችን ላይ ትኩረት ሰጥተው ከሚዘግቡት ሚዲያዎች ጋራ በጎ የሥራ ዝምድናን በሚያሻክር ግንኙነት ውስጥ መገኘት ጎጂነቱ ያመዝናል፡፡ የሰላማዊ ሽግግሩን ይኹን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሎን በተመለከተ ስሕተት የታየባቸው፣ እውነቱን ለመናገር ደግሞ ዘረኝነት የተጠናወታቸውና ከሐቅ የራቁ ዘገባዎች አልታዩም አንልም፡፡ ነገር ግን ተስፋ አለን÷ ጠቅ/ቤተ ክህነቱ ሚዲያዊው ስሕተት በሚዲያዊ አሠራር ይታረም ዘንድ በክሥ የጀመረውን መንገድ እንደሚያጤን፡፡
posted by Dawit Demelash

አብዛኞቹ የተፈናቀሉ የጉራፈርዳ ነዋሪዎች የደረሰቡት እንደማይታወቅ መኢአድ ገለጠ

ጥር ፳፫ (ሀያ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ድርጅቱ ” በጭቆናና በአፈና ስልጣንን ለማራዘም የሚካሄደው ዘመቻ ቀጥሏል” በሚል ርእስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ፣ በጉራፈርዳ ወረዳ የሚፈናቀለው አርሶአደር ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑንና የተወሰኑትም በሚዛን ተፈሪ፣ በጅማ፣ በአንቦ እና በአዲስ አበባ ያለመጠለያ ለልመና መዳረጋቸውን ገልጿል።
ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አርሶአደሮች መሬታቸውን ተነጥቀው የአካባቢው ታጣቂዎች በጨረታ ስም እየተቀራመቱት መሆኑን የገለጠው መግለጫው፣ ወ/ሮ ስንዴ ስጦታው የተባሉ የስምንት ልጆች እናት በጥይት ተደብድበው በመሞታቸው ልጆቻቸው ያለአሳዳጊ መቅረታቸውን አብራርቷል።
ጥር 21 ከሌሊቱ 8 ሰአት ከወረዳው መስተዳደር የተላኩ አራት ወታደሮች ወደ አቶ ኢበሉ ማሞ ጊቢ በመግባት ሁለት በሬዎችና ሶስት በጎችን መውሰዳቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ መግለጫ፣ 32 ሰዎችም እንዲሁ በእስር ቤት ያለምንም ፍርድ እየተሰቃዩ መሆኑን ገልጿል።
መኢአድ ” በጉራፈርዳ ህዝብ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ እየተካሄደ ያለው ወከባ እስራትና እና ግድያ በአገራችን ታይቶ የማይታወቅ ሰብአዊ ረገጣና የአንድን ቋንቋ ተናጋሪ ህዝብን የማጥፋት ዘመቻ አካል ነው ” በማለት ገልጾ፣ ነዋሪዎቹ ከአካባቢው መልቀቅ እንዳለባቸው አለበለዚያ ግን ሁሉንም እንደሚገድሏቸው የወረዳው አስተዳዳሪዎች እና የፖሊስ ሀላፊዎች መግለጻቸውንም ይፋ አድርጓል።
በአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ላይ የተካሄደውን የሌሎች አገራት የዘር ማጥፋት ወደ አገራችን መግባቱን፣ በጉራ ፈርዳ የተፈጸመው ድርጊት እንደሚያመላክት የገለጸው መኢአድ፣ ድርጊቱን  ኢትዮጵያውያን ተረባርበው እንዲያስቆሙት ጥሪ አቅርቧል።
በደቡብ ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እየተባባሱ መምጣታቸው ይነገራል።
posted by.Demelash Demelash

Wednesday, January 30, 2013


“የመበስበሱ በሽታ ሁሉም ዘንድ ነው”

ሻዕቢያው በረከት ህወሃትን ሊነዱት ይሆን?
bereket vs sebhat


የአቶ በረከት ስምዖንና የአቶ ስብሃት ነጋ የደፈጣ ውጊያ ገሃድ መውጣቱን የሚያመላክት መረጃ ይፋ መሆኑን ተከትሎ በህወሃት መንደር ውስጥ ከፍተኛ መደናገጥ ተፈጥሯል። ጉዳዩን የሚከታተሉ እንደሚሉት ልዩነቱን ለማርገብ በከፍተኛ ደረጃ ጥረት ቢደረግም ሊሳካ አልቻለም።
ከፍተኛ ስልጣን የያዙትንና አቶ መለስ ለመተካካት ያዘጋጇቸውን አዳዲስ አመራሮች፣ በቅርቡ ደንብና ህግ በመጣስ ሹመት የሰጡዋቸውን ጨምሮ የሰራዊቱን አዛዦችና ደህንነቱን ከጎናቸው ያሳተፉት ክፍሎች የተፈጠረው ልዩነት እልባት ማግኘት ይገባዋል የሚል አቋም መያዛቸውን የሚጠቁሙ ክፍሎች እነማን ተለይተው እንደሚመቱ ለመገመት አስቸጋሪ መሆኑንን ይገልጻሉ።
“ፓርቲያችን ከእንጥሉ በስብሷል” በማለት ከዛሬ አስራአንድ ዓመት በፊት በአገር ክህደት ሊያስወግዷቸው የተነሱትን ጓዶቻቸውን የረቱት መለስ የተጠቀሙበት ዋንኛ ስልት አባይ ጸሃዬን “ከውህዳኑ” ጋር በማሰለፍ ነበር። ዛሬ ለህወሃትና ለትግራይ ህዝብ በትግርኛ ቋንቋ ተጽፎ ተሰራጨ የተባለውና ይህንኑ መረጃ ዋቢ በማድረግ ኢየሩሳሌም አርአያ በተለያዩ ድረገጾች ይፋ እንዳደረጉት አቶ አባይ ጸሐዬ የተመደቡት ወጥመዱ ከተጠመደባቸው ዘንድ ነው።
“ድርጅትህ ኢህአዴግ እስከዛሬ ታግሎ እዚህ አድርሶሃል። በተለይም የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪ የሆነው ባለ ራዕዩን መሪህን በቅርቡ አጥተሃል” የሚል የአምልኮ መሪ ቃል ያለበት የጥሪ ወረቀት “ተቆርቋሪ ለሆናችሁ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ” በማለት ጥሪ አቅርቧል። ኢየሩሳሌም አርአያ ቃል በቃል በትምህርተ ጥቅስ አኑረው ባሰራጩት በዚህ ጉልህ ዜና “እነ አቶ በረከት፣ ወ/ሮ አዜብ፣ ቴዎድሮስ ሃጎስ” ወረቀቱን አዘጋጅተው እንዳሰራጩ ያስረዳል።
በኢየሩሳሌም አርአያ ዜና ላይ እንደተመለከተው እነ አቶ ስዩም መስፍን፣ አባይ ጸሐዬ፣ አለቃ ጸጋዬ ከነባለቤታቸው የትግራይን ህዝብ ለጠላት ለመስጠት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ያወሳል።  “… የኔ የምትላቸው ጅቦች ተነስተውብህ ይገኛሉ” የተጠቀሱትንና ሌሎች ደጋፊዎቻቸውን “ጅቦች” ሲል የሚጠራው መልዕክት፣ “… ከእኛ ኋላ የተፈጠሩና ራሳችን ያሳደግናቸው ሲጠናከሩ ድርጅታችን ግን እየተዳከመ በመሄድ ላይ ነው” ሲል ያሳስባል። እነማን እንደሆኑ በግልጽ ሳይዘረዘር “የተወገዱ ግን በመጥፎ ጎዳና ያልተሰማሩን መልሰን ወደ ፓርቲው ማስገባት አለብን። ይህ ካልሆነ ግን የህዝብ ትግል አውላላ ሜዳ ላይ ጅብ በልቶት ሊቀር ነው ከጠላቶቻችን ጋር እንታረቅ እያሉን ነው” የሚል ማስጠንቀቂያ ያስቀምጣል። በስተመጨረሻ  “ከጀርባ ሆኖ የዚህ አፍራሽ ዋና ቀያሽ መሃንዲስ ስብሃት ነጋ መሆኑን ደርሰንበታል” ይላል።
“የኢህአዴግ ስኬት የመስመር እንጂ የግለሰብ አይደለም” በማለት የመለስን አምልኮ ለመቃወም ቀዳሚ የሆኑት አቶ ስብሃት ኤፈርትን ለወ/ሮ አዜብ ካስረከቡ በኋላ ከድርጅቱ ጋር ያላቸው ግንኙነት የላላ መሆኑን ለማሳየት እንደ ሩቅ ተመልካች አስተያየት ሲሰጡ ባብዛኛው ባልተለመደ መልክ ይዛለፉ ነበር። በተለይም አቶ በረከትን የማኮሰስና ምናምንቴ አድርጎ የማሳየት ስልት ሲጠቀሙ ቆይተዋል። ይህ እንዳለ ሆኖ አለመግባባቱ ሊከሰት ግድ እንደሆነ አስቀድመው የተነበዩም ነበሩ።
“… መለስ ስለሌሉ የወንበር ቡቅሻው የማይቀር ነው። በድርጅቱ አመራሮች ዘንድ የሌባና ፖሊስ፣ የሃይል ሚዛንና ቅኝት፣ አሰላለፍን የማሳመር ሰልፍ እየታየ ነው፤ … የመለስ ማለፍ በድርጅቱ ውስጥ ታፍኖ የቆየውን ቁርሾ ማፈንዳቱ አይቀርም…” ሲሉ ኦክቶበር 25 ቀን 2012 ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ቃለ ምልልስ የሰጡት አሁን በትምህርት ላይ የሚገኙ የኢህአዴግ ሰው፣ የኢህአዴግ ድልድይ ተሰብሯል፤ የጋራ ነጥብም የለውም ብለው ነበር።
አውራምባ ታይምስ በበኩሉ ምንጩን አዲስ አበባ በማለት በተመሳሳይ የህወሃትን አደጋ ውስጥ መውደቅ ሲያበስር በስም ከዘረዘራቸው አመራሮች መካከል አቶ ስብሃት ነጋን አልጠቀሰም። ኢየሩሳሌም አርአያ አቶ በረከት የሚዘውሩትና የእነ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ወገን በዋናነት ለመምታት ያሰበው አቶ ስብሃት ነጋን እንደሆነ ለአባላት ተበተነ የተባለውን የማስጠንቀቂያ ወረቀት በመጥቀስ ይገልጻል።
አውራምባ ታይምስ “እያጣራሁ አቀርበዋለሁ” በማለት ያወጣው ትኩስ ዜና ለህወሃት አባላት ተሰራጨ የተባለውን ደብዳቤ “ማን እንደጻፈው አልታወቀም” በማለት ብዥታ የሚያጭር መልክት ሲያስተላልፍ፣ ኢየሩሳሌም አርአያ ከአውራምባ ድረገጽ ባለቤት አቶ ዳዊት ከበደ በተለየ መልኩ ዜናውን በትነው አስረድተዋል። በሁሉም በኩል እንደተጠቀሰው ህወሃት ቀውስ ውስጥ ተነክሯል።
በየካቲት ወር በሚደረግ ድርጅታዊ ግምገማ ጠራርገው እንደሚያስወግዷቸው እንደ ከባድ ሚዛን ቦክስ ቀጠሮ በመያዝ እነ አቶ ስብሃት፣ ስዩም፣ አባይና አለቃ ጸጋዬን በመጥቀስ የተሰራጨው  ወረቀት በስተመጨረሻ ስብሃት ነጋ ላይ ክርኑን አስደቁሶ እንደሚያበቃ የህዋሃትን ጓዳ አስመልክቶ በተደጋጋሚ ለየት ያለ ዜና የሚያስነብቡት ኢየሩሳሌም አርአያ ያበቃሉ።
ጎልጉል ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው የነበሩት የኢህአዴግ ሰው ይህንን ዜና አስመልክተው ምን አስተያየት እንዳላቸው ጠይቀናቸው ነበር። “በሌሎቹም አቻ ድርጅቶች ውስጥ በተመሳሳይ ይህ ሁኔታ ይከሰታል። የመበስበሱ በሽታ ሁሉም ዘንድ ነው” በማለት መልሳቸውን ይጀምራሉ። ለጊዜው ደኢህዴንና ብአዴን አንድ ላይ መሆናቸውን ያስታወቁት እኚሁ አስተያየት ሰጪ የኦህዴድ አቋም አለመጥራቱን ነው የሚናገሩት።
“የድጋፉ ጉዳይ የፎርሙላ ነው። ዶ/ር ደብረጽዮንና በረከት ስለላውን፣ ጦር ሃይሉን፣ የፖሊስና የልዩ ሃይሉን ሙሉ በሙሉ ስለተቆጣጠሩት በአሸናፊነት እንደሚወጡ ጥርጥር የለውም” ካሉ በኋላ አቶ ስብሃት ሰሞኑን “አማራውን ከሰደብኩ እኔ ታምሜያለሁ ማለት ነው ሆስፒታል መሔድ አለብኘኝ” በማለት የሰጡት መግለጫ ሲዘልፉትና ሲረግሙት የኖሩትን አማራና ብአዴንን ተለሳልሶ ለመቅረብ ያደረጉት እንደሆነ በተዋረድ ለብአዴን አባሎች መገለጹን እንደሚያውቁ አስረድተዋል።
“ምንም ተባለ ምን በመከላከያውና በደህንነቱ ሃይል ተጠቅመው የፈለጉትን መወሰንና የማስወሰን፣ ባላቸው በሚሰራው የፖለቲካ መዋቅር እስከታች መመሪያ በማውረድ የእነ በረከት ወገን ባለድል እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ቀድሞ ታጋይ የነበሩ፣ የደህንነት ሃይሉን እየረዱ ብር የሚያመርቱ ግርግሩ ስለማይመቻቸው ሃይል ካለው ወገን ጋር በመሆናቸው እነ ስብሃትን ያቀላጥፏቸዋል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ግለሂስ አድርገው አርፈው ለመቀመጥ ካልተስማሙ ብቻ ነው” በማለት አስተያየታቸውን ይደመድማሉ፡፡
ይህንን መረጃ በሚያጠናክር መልኩ ከዚህ በፊት ከጻፍናቸው ዜናዎች መካከል አቶ በረከትና አቶ ሃይለማርያም የመለስ የቅርብ ሰዎች መሆናቸውንና አቶ መለስ ወደ ውጪ ሲወጡ የሥልጣኑን ቁልፍ የሚሰጡት ለአቶ በረከት እንደሆነ፤ የአቶ ሃይለማርያም ሹመት መነሻውም በዚሁ ቀደም ሲል በተፈጠረ “የቤተሰብ መሰል” ግንኙነት መሆኑን በመናገር ስማቸው ሳይጠቀስ ቃላቸውን ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ የሰጡ የኦህዴድ ሰው ጠቅሰን መጻፋችን የሚታወስ ነው፡፡ አቶ መለስ በሞቱ ማግስት ከኢህአዴግ ምክርቤት እና ከፓርላማው ውሳኔ በፊት አቶ ሃይለማርያም ጠ/ሚ/ር ሆነው እንደሚቀጥሉ በመናገር የተጠባባቂ ጠ/ሚ/ርነት ሥልጣን ይዘው እንደሚሠሩ አቶ በረከት በወቅቱ በሰጡት ቃለምልልስ መናገራቸው የሚታወስ ነው፡፡ አቶ ሃይለማርያም ለፎርማሊቲ በፓርላማ ፊት ቀርበው ምህላ እንደሚፈጽሙ አቶ በረከት በግላቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መናገራቸው ይህንኑ ቤተሰባዊ ግንኙነት የሚያጠናክር መሆኑን መዘገባችን የሚጠቀስ ነው፡፡
Posted By .Dawit  Demelash

የአቶ በረከት ስምዖንና የአቶ ስብሃት ነጋ የደፈጣ ውጊያ ገሃድ ወጣ


የአቶ በረከት ስምዖንና የአቶ ስብሃት ነጋ የደፈጣ ውጊያ ገሃድ መውጣቱን የሚያመላክት መረጃ ይፋ መሆኑን ተከትሎ በህወሃት መንደር ውስጥ ከፍተኛ መደናገጥ ተፈጥሯል። ጉዳዩን የሚከታተሉ እንደሚሉት ልዩነቱን ለማርገብ በከፍተኛ ደረጃ ጥረት ቢደረግም ሊሳካ አልቻለም።
ከፍተኛ ስልጣን የያዙትንና አቶ መለስ ለመተካካት ያዘጋጇቸውን አዳዲስ አመራሮች፣ በቅርቡ ደንብና ህግ በመጣስ ሹመት የሰጡዋቸውን ጨምሮ የሰራዊቱን አዛዦችና ደህንነቱን ከጎናቸው ያሳተፉት ክፍሎች የተፈጠረው ልዩነት እልባት ማግኘት ይገባዋል የሚል አቋም መያዛቸውን የሚጠቁሙ ክፍሎች እነማን ተለይተው እንደሚመቱ ለመገመት አስቸጋሪ መሆኑንን ይገልጻሉ።
“ፓርቲያችን ከእንጥሉ በስብሷል” በማለት ከዛሬ አስራአንድ ዓመት በፊት በአገር ክህደት ሊያስወግዷቸው የተነሱትን ጓዶቻቸውን የረቱት መለስ የተጠቀሙበት ዋንኛ ስልት አባይ ጸሃዬን “ከውህዳኑ” ጋር በማሰለፍ ነበር። ዛሬ ለህወሃትና ለትግራይ ህዝብ በትግርኛ ቋንቋ ተጽፎ ተሰራጨ የተባለውና ይህንኑ መረጃ ዋቢ በማድረግ ኢየሩሳሌም አርአያ በተለያዩ ድረገጾች ይፋ እንዳደረጉት አቶ አባይ ጸሐዬ የተመደቡት ወጥመዱ ከተጠመደባቸው ዘንድ ነው።
“ድርጅትህ ኢህአዴግ እስከዛሬ ታግሎ እዚህ አድርሶሃል። በተለይም የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪ የሆነው ባለ ራዕዩን መሪህን በቅርቡ አጥተሃል” የሚል የአምልኮ መሪ ቃል ያለበት የጥሪ ወረቀት “ተቆርቋሪ ለሆናችሁ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ” በማለት ጥሪ አቅርቧል። ኢየሩሳሌም አርአያ ቃል በቃል በትምህርተ ጥቅስ አኑረው ባሰራጩት በዚህ ጉልህ ዜና “እነ አቶ በረከት፣ ወ/ሮ አዜብ፣ ቴዎድሮስ ሃጎስ” ወረቀቱን አዘጋጅተው እንዳሰራጩ ያስረዳል።
በኢየሩሳሌም አርአያ ዜና ላይ እንደተመለከተው እነ አቶ ስዩም መስፍን፣ አባይ ጸሐዬ፣ አለቃ ጸጋዬ ከነባለቤታቸው የትግራይን ህዝብ ለጠላት ለመስጠት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ያወሳል። “… የኔ የምትላቸው ጅቦች ተነስተውብህ ይገኛሉ” የተጠቀሱትንና ሌሎች ደጋፊዎቻቸውን “ጅቦች” ሲል የሚጠራው መልዕክት፣ “… ከእኛ ኋላ የተፈጠሩና ራሳችን ያሳደግናቸው ሲጠናከሩ ድርጅታችን ግን እየተዳከመ በመሄድ ላይ ነው” ሲል ያሳስባል። እነማን እንደሆኑ በግልጽ ሳይዘረዘር “የተወገዱ ግን በመጥፎ ጎዳና ያልተሰማሩን መልሰን ወደ ፓርቲው ማስገባት አለብን። ይህ ካልሆነ ግን የህዝብ ትግል አውላላ ሜዳ ላይ ጅብ በልቶት ሊቀር ነው ከጠላቶቻችን ጋር እንታረቅ እያሉን ነው” የሚል ማስጠንቀቂያ ያስቀምጣል። በስተመጨረሻ “ከጀርባ ሆኖ የዚህ አፍራሽ ዋና ቀያሽ መሃንዲስ ስብሃት ነጋ መሆኑን ደርሰንበታል” ይላል።
“የኢህአዴግ ስኬት የመስመር እንጂ የግለሰብ አይደለም” በማለት የመለስን አምልኮ ለመቃወም ቀዳሚ የሆኑት አቶ ስብሃት ኤፈርትን ለወ/ሮ አዜብ ካስረከቡ በኋላ ከድርጅቱ ጋር ያላቸው ግንኙነት የላላ መሆኑን ለማሳየት እንደ ሩቅ ተመልካች አስተያየት ሲሰጡ ባብዛኛው ባልተለመደ መልክ ይዛለፉ ነበር። በተለይም አቶ በረከትን የማኮሰስና ምናምንቴ አድርጎ የማሳየት ስልት ሲጠቀሙ ቆይተዋል። ይህ እንዳለ ሆኖ አለመግባባቱ ሊከሰት ግድ እንደሆነ አስቀድመው የተነበዩም ነበሩ።
“… መለስ ስለሌሉ የወንበር ቡቅሻው የማይቀር ነው። በድርጅቱ አመራሮች ዘንድ የሌባና ፖሊስ፣ የሃይል ሚዛንና ቅኝት፣ አሰላለፍን የማሳመር ሰልፍ እየታየ ነው፤ … የመለስ ማለፍ በድርጅቱ ውስጥ ታፍኖ የቆየውን ቁርሾ ማፈንዳቱ አይቀርም…” ሲሉ ኦክቶበር 25 ቀን 2012 ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ቃለ ምልልስ የሰጡት አሁን በትምህርት ላይ የሚገኙ የኢህአዴግ ሰው፣ የኢህአዴግ ድልድይ ተሰብሯል፤ የጋራ ነጥብም የለውም ብለው ነበር።
አውራምባ ታይምስ በበኩሉ ምንጩን አዲስ አበባ በማለት በተመሳሳይ የህወሃትን አደጋ ውስጥ መውደቅ ሲያበስር በስም ከዘረዘራቸው አመራሮች መካከል አቶ ስብሃት ነጋን አልጠቀሰም። ኢየሩሳሌም አርአያ አቶ በረከት የሚዘውሩትና የእነ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ወገን በዋናነት ለመምታት ያሰበው አቶ ስብሃት ነጋን እንደሆነ ለአባላት ተበተነ የተባለውን የማስጠንቀቂያ ወረቀት በመጥቀስ ይገልጻል።
አውራምባ ታይምስ “እያጣራሁ አቀርበዋለሁ” በማለት ያወጣው ትኩስ ዜና ለህወሃት አባላት ተሰራጨ የተባለውን ደብዳቤ “ማን እንደጻፈው አልታወቀም” በማለት ብዥታ የሚያጭር መልክት ሲያስተላልፍ፣ ኢየሩሳሌም አርአያ ከአውራምባ ድረገጽ ባለቤት አቶ ዳዊት ከበደ በተለየ መልኩ ዜናውን በትነው አስረድተዋል። በሁሉም በኩል እንደተጠቀሰው ህወሃት ቀውስ ውስጥ ተነክሯል።
በየካቲት ወር በሚደረግ ድርጅታዊ ግምገማ ጠራርገው እንደሚያስወግዷቸው እንደ ከባድ ሚዛን ቦክስ ቀጠሮ በመያዝ እነ አቶ ስብሃት፣ ስዩም፣ አባይና አለቃ ጸጋዬን በመጥቀስ የተሰራጨው ወረቀት በስተመጨረሻ ስብሃት ነጋ ላይ ክርኑን አስደቁሶ እንደሚያበቃ የህዋሃትን ጓዳ አስመልክቶ በተደጋጋሚ ለየት ያለ ዜና የሚያስነብቡት ኢየሩሳሌም አርአያ ያበቃሉ።
ከጎልጉል ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው የነበሩት የኢህአዴግ ሰው ይህንን ዜና አስመልክተው ምን አስተያየት እንዳላቸው ጠይቀናቸው ነበር። “በሌሎቹም አቻ ድርጅቶች ውስጥ በተመሳሳይ ይህ ሁኔታ ይከሰታል። የመበስበሱ በሽታ ሁሉም ዘንድ ነው” በማለት መልሳቸውን ይጀምራሉ። ለጊዜው ደኢህዴንና ብአዴን አንድ ላይ መሆናቸውን ያስታወቁት እኚሁ አስተያየት ሰጪ የኦህዴድ አቋም አለመጥራቱን ነው የሚናገሩት።
“የድጋፉ ጉዳይ የፎርሙላ ነው። ዶ/ር ደብረጽዮንና በረከት ስለላውን፣ ጦር ሃይሉን፣ የፖሊስና የልዩ ሃይሉን ሙሉ በሙሉ ስለተቆጣጠሩት በአሸናፊነት እንደሚወጡ ጥርጥር የለውም” ካሉ በኋላ አቶ ስብሃት ሰሞኑን “አማራውን ከሰደብኩ እኔ ታምሜያለሁ ማለት ነው ሆስፒታል መሔድ አለብኘኝ” በማለት የሰጡት መግለጫ ሲዘልፉትና ሲረግሙት የኖሩትን አማራና ብአዴንን ተለሳልሶ ለመቅረብ ያደረጉት እንደሆነ በተዋረድ ለብአዴን አባሎች መገለጹን እንደሚያውቁ አስረድተዋል።
“ምንም ተባለ ምን በመከላከያውና በደህንነቱ ሃይል ተጠቅመው የፈለጉትን መወሰንና የማስወሰን፣ ባላቸው በሚሰራው የፖለቲካ መዋቅር እስከታች መመሪያ በማውረድ የእነ በረከት ወገን ባለድል እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ቀድሞ ታጋይ የነበሩ፣ የደህንነት ሃይሉን እየረዱ ብር የሚያመርቱ ግርግሩ ስለማይመቻቸው ሃይል ካለው ወገን ጋር በመሆናቸው እነ ስብሃትን ያቀላጥፏቸዋል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ግለሂስ አድርገው አርፈው ለመቀመጥ ካልተስማሙ ብቻ ነው” በማለት አስተያየታቸውን ይደመድማሉ፡፡
ይህንን መረጃ በሚያጠናክር መልኩ ከዚህ በፊት ከጻፍናቸው ዜናዎች መካከል አቶ በረከትና አቶ ሃይለማርያም የመለስ የቅርብ ሰዎች መሆናቸውንና አቶ መለስ ወደ ውጪ ሲወጡ የሥልጣኑን ቁልፍ የሚሰጡት ለአቶ በረከት እንደሆነ፤ የአቶ ሃይለማርያም ሹመት መነሻውም በዚሁ ቀደም ሲል በተፈጠረ “የቤተሰብ መሰል” ግንኙነት መሆኑን በመናገር ስማቸው ሳይጠቀስ ቃላቸውን ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ የሰጡ የኦህዴድ ሰው ጠቅሰን መጻፋችን የሚታወስ ነው፡፡ አቶ መለስ በሞቱ ማግስት ከኢህአዴግ ምክርቤት እና ከፓርላማው ውሳኔ በፊት አቶ ሃይለማርያም ጠ/ሚ/ር ሆነው እንደሚቀጥሉ በመናገር የተጠባባቂ ጠ/ሚ/ርነት ሥልጣን ይዘው እንደሚሠሩ አቶ በረከት በወቅቱ በሰጡት ቃለምልልስ መናገራቸው የሚታወስ ነው፡፡ አቶ ሃይለማርያም ለፎርማሊቲ በፓርላማ ፊት ቀርበው ምህላ እንደሚፈጽሙ አቶ በረከት በግላቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መናገራቸው ይህንኑ ቤተሰባዊ ግንኙነት የሚያጠናክር መሆኑን መዘገባችን የሚጠቀስ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Posted By.Dawit Demelash

Tuesday, January 29, 2013

ቤተ ክህነት የፓትርያርክ ምርጫን ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀሱትን አስጠነቀቀች

- በአንዳንዶቹ ላይ ክስ መሥርታለች፤

(ሪፖርተር ጋዜጣ)፦ የቀድሞውን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስን ሕልፈት ተከትሎ፣ ስድስተኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ ሰላማዊ የሽግግር ጊዜውን ለማደናቀፍ የሚገኙ ቡድኖችን፣ የመገናኛ ብዙኅንና ግለሰቦችን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስጠነቀቀ፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔን በማሟላት የቤተ ክርስቲያኗ ቀኖና በሚያዘው መሠረት፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን በመምራት በሕጉ መሠረት መንበሩን የሚጠብቁ አባት በመሰየም ቀጣይ ጉዞ ሰላማዊ ለማድረግ እየተሠራ ባለበት በአሀኑ ጊዜ፣ ከውስጥና ከውጭ ያሉ በጐ አመለካከት የሌላቸው ግለሰቦች አፍራሽ ተግባር እየፈጸሙ እንደሚገኙ ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል፡፡
የስድስተኛውን ፓትርያርክ አሿሿም በሚመለከት ሕገ ደንብ ወጥቶ ምርጫውን ተግባራዊ ለማድረግ በእንቅስቃሴ ውስጥ መሆኑን የሚያውቁ አንዳንድ የመገናኛ ብዙኅን፣ ከውስጥ አፍራሽ ኃይሎች የሚቀበሉትን ፀረ ሰላምና ከእውነት የራቀ አሉባልታ ከድረ ገጽ ያገኙ በማስመሰልና ‹‹ምንጮቻችን›› እያሉ በውጭና በአገር ውስጥ ያለውን ምዕመናን እያወናበዱ በሚገኙት ላይ፣ ቤተ ክህነት ክስ መመሥረቷን ጽሕፈት ቤቱ ገልጿል፡፡

በአንድነትና በመደማመጥ መንፈስ እየሠራ የሚገኘውን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ አሉባልታ በመንዛት ትርምስ እንዲፈጠር ለማድረግ የሚንቀሳቀሱት ቡድኖችም ሆኑ ግለሰቦች ከቃላት ያለፈ ተግባር መፈጸም የማይችሉ ቢሆንም፣ ዝም ብሎ መመልከቱ ድርጊታቸውን እንደመደገፍ ስለሚቆጠር፣ በቀጣይም በመገናኛ ብዙኅኑም ላይ ሆነ በግለሰቦቹ ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ቤተ ክህነት በዝግጅት ላይ መሆኗን፣ የቤተ ክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እስክንድር ገብረ ክርስቶስ አስታውቀዋል፡፡
ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት ወይም የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ማብራሪያና መግለጫ ሳይሰጡ፣ ምስላቸውንና እነሱ እንደተናገሩ በማስመሰል በአንዳንድ ድረ ገጾችና የመገናኛ ብዙኅን እየተገለጸና እየተጻፈ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ ሕዝቡ ወደ ትርምስና አላስፈላጊ ሁኔታ ውስጥ እንዳይገባ የሚያደርጉትን አመስግነዋል፡፡ ቤተ ክህነት ትክክለኛ መረጃ ለሕዝብ እንዲደርስ የምትፈልግና የምትደግፍ መሆኑን አክለው፣ ያልተባለን ተብሏል ብሎ ፎቶን በማስደገፍ ባገኙት ቦታ መለጠፍ የሚያስጠይቅ ከመሆኑም ባሻገር ተገቢ አለመሆኑንም አስረድተዋል፡፡

POSTED BY. DAWIT DEMELASH

Federalism or Internal Colonialism: The Ethiopian situation

by Yilma Bekele
“The tragic reality of today is reflected in the true plight of our spiritual existence. We are spineless and cannot stand straight.“ Ai Weiwei – Chinese dissident.
As a concept there is nothing wrong with Federalism as a system of government. There are plenty of examples of such arrangement like as in the USA, Canada, Germany, Mexico and India among others where it has shown to work. That is the system TPLF under Meles and company told the Ethiopian people that they are attempting to construct. It has been over twenty years now since the work has started and the question in front of us is, how is it going?
How is Federalism working in our country? I will tell you about a specific powerful institution in Ethiopian and you the reader, be the judge. The governmental body I have in mind is one of the most important and key sector of our economy and it is currently named Ethio Telecom. Here is a brief description of the history of the telephone in Ethiopia.
The first telegraph line was between Harar and Addis Abeba in 1889. Emperor Haile Sellasie established the Imperial Board of Telecommunications of Ethiopia in 1952. Derge reorganized it as Ethiopian Telecommunication Service and later on as Ethiopian Telecommunications Authority (ETA) in 1976 and 1981. In 1996 TPLF replaced that with Ethiopian Telecommunications Corporation. It was born again as Ethio Telecom in 1910. The Ethiopian Telecommunications Corporation is the oldest Public Telecommunications Operator (PTO) in Africa.
In our country Ethiopia the Federal Government owns the country including resources, land and most of the vital economy. Communication tools such as television, radio, telephone and Internet are fully owned and operated by the Federal Government. The Ethiopian government is the number one employee in the country. Controlling all this assets give the Federal Government total power on every aspect of the people and country. For the Woyane regime Ethio Telecom is a weapon to amass large amount of money, spy, control, create anxiety and bully the citizen. How TPLF was able to control ETC is the story of what happened to our country. The group known to us as TPLF organized as an ethnic based party took over the political, economic, security sectors of the country called Ethiopia in a very systematic and deliberate way. This assertion can be proved in more ways than one cares to count. Please read Ginbot7 publication on the domination of the military by Tigrean ethnic group.
Ethio Telecom is another key sector of the economy and a very powerful weapon that was targeted by TPLF for complete take over. How they were able to do that is the history of what happened to the rest of the country. Ethio Telecom encompasses the trial and tribulations of our country and people. In my opinion Ethio Telecom is where Weyane’s star shined.
It took TPLF for years (1991 -1995) to figure out the inner workings of such a large and old organization. In 1996 they restructured it as a Corporation and were able to get rid of ‘trouble makers’ and install their own people in key positions. Its importance did not manifest until around 2000 with the advent of the World Wide Web. Before that TPLF was content collecting spare change. The Internet changed the whole ball game. Communication became the driving force of change. As a totalitarian regime highly motivated to control the flow of information the TPLF saw the dangers of unrestricted access to information and knowledge.
In 2010 Ethio Telecom emerged. The birth of Ethio Telecom was a painful moment in the history of our country. People were played upon, dangled around, set against each other and humiliated. Such a powerful and modern organization in the life of our country was made to look like a failed and useless outfit. The twelve thousand strong body was completely dismantled by the TPLF. Guess who was in charge of this tragedy. None other than current Deputy Prime Minister Dr. Debretsion. He was the architect and enforcer of this desecration of an Ethiopian home grown building block.
To avoid doing the dirty job TPLF gave management services to a subsidiary of French Telecom – Orange (telecommunications). Orange is a third rate multi- national corporation and an easy prey for TPLF to push around. Without input from the workers, without consulting those affected Orange and the TPLF Politburo said ‘we got a deal you cannot refuse.’ They created five categories named N1-N5. N1 included the French team and Ethiopian management personnel. Over half of the twelve thousand employees were dumped on the road side. There was no explanation, no discussion and no review. One of those that was found to be superfluous was the head of the Union Ato Adisse Bore. You see the beauty of Woyane justice? There was no one left to speak for the workers! You can tell the whole idea was nothing but a naked assault on our people when you see that among the personnel the new organization is purported to keep the list included some dead and some on exile. This is how Ethio Telecom was born.
Why do you think Ethio Telecom is a prized asset of the minority TPLF regime? It is because communications is the key to the future. The media opens our eyes to situations and places we will not even dream of. The media is the first causality of a repressive regime. Do you notice the first target of any coup d’état is the control of the radio and television transmission sites? Ethio Telecom is the gate keeper. Ethio Telecom sustains the dictatorship.
Thus they got rid of half of the employees of ETC and made it in their own image. They trained a few, they imported a few of their own from the Diaspora and they either blackmailed or bought the rest. Today Ethio Telecom is a cash cow to the dictatorship and a very powerful security apparatus to safeguard a few while abusing the many. Here is the composition of the N 1 Group managing the enterprise they established.
TPLF Group managing the enterprise they established
Please let us keep it real here. This is not some one’s imagination gone haywire, nor a just made up figure. It is real and we treat it as such until proven otherwise. Is this what federalism is all about? Ethnicity is the corner stone of Woyane rule. The above chart is based on Woyanes’ own classification of our people.
This investigative study at its best came out two weeks ago. Fellow Ethiopians took time and effort to find and compile such information so we can have a clear view of the actual situation in our homeland. As they say talk is cheap but facts speak for themselves. After all is said and done the above picture does not lie. It is based on the TPLF’s definition of who is who in today’s Ethiopia.

Why do you think the TPLF regime under Debretsion finds communications important enough to control as a monopoly? It is because communications is the key. Leaders like Meles and now Debretsion are aware of the value of information. They are spin doctors. When it comes to a closed society like ours they make sure they are the only source of information. Our country Ethiopia is the last in any measure of technological advancement, why do you think that is so? They don’t allow it, they don’t foster it, and they don’t encourage it because the more we know the less we think of them.
The Federalism TPLF is building in our country is Apartheid. In the former South Africa the 9.6% white ruled over the 79% black population. In Ethiopia, today the 6.1% from Tigrai region are dominating the economic political and military life of the country. This is a very difficult statement to make and it is a very ugly thought to cross one’s mind. But it is also unfair and being a coward not to face reality. The situation in the military, the situation in Ethio Telecom is not something to ignore. It did not happen by accident. The TPLF party in a deliberate and callous manner created this Apartheid system in our country. The above pie chart showed the so called N 1 group in higher management what do you think N 2 looks like?
The Federalism TPLF is building
Knowledge is power. Knowing what the TPLF party is doing to our country and people helps us realize the problem, discuss the ramifications if left to continue and find a lasting solution so we can all move forward as one people. Uncovering such crime is not ethnic bating. Discussing such unfair and ugly reality is not hating on individuals or groups. It is real and it has to be dealt with. Dr. Debretsion and his friends have to answer why there is such naked discrepancy in the organization they are entrusted to administer in the name of the people. They have to explain to us the people why there are more from their own ethnic group in position of real power and influence than the rest. Is it because they couldn’t find a Gambelan, a Sidama, a Kenbatan, an Oromo or an Amhara to fill such slots? If there is a reasonable explanation we are all ears but changing the subject or accusing one of ethnic bating is not the way to go.
Now they have inserted their own people in key positions what do you think they are doing with the new and improved Ethio Telecom? Are they using it to connect the country, use the new found digital technology to jump start our economy and education system and usher an era of peace and prosperity? I am afraid a mind that relies on ethnicity and village mentality to get ahead cannot be expected to soar like an eagle but slither like a snake biting all that crosses its path. That is exactly what Ethio Telecom is, a venomous snake attacking our people and country every chance it gets. Check out our double digit growing economy.
Ethio Telecom is, a venomous snake attacking
It is clear the regime is not interested in using the new technology to help our country join the community of nations. No question ethnic mentality and government monopoly stifles innovation, kills individual initiative and keeps our people in darkness. Here is a finding by Reporters Without Borders (RWB).
“Ethiopia’s only ISP, State owned Ethio Telecom has just installed a system for blocking access to the Tor network, which lets users browse anonymously and access blocked websites. In order to achieve such selective blocking Ethio Telecom must be using Deep Packet Inspection (DPI) an advanced network filtering system.”
Think about it, the ruling junta is willing to invest such huge amounts of money to spy on its citizens instead of using the money to wire schools and libraries. They use Chines technology to block any and all Internet, radio and our ESAT news broadcast. The few decide what is good for the many. It is not healthy. It does not end well. We have seen what a single ethnic domination does to people and country. Rwanda was just yesterday and South Africa will suffer the legacy of Apartheid for decades to come. The current arrangement in our country will not ensure a strong and vibrant Ethiopia where her children will prosper under one roof but rather a weak and divided Ethiopia that one day will fall prey to outsiders that will exploit the division.
At the beginning of this article I quoted the Chinese dissident Ai Weiwei speaking about the character of his people suffering under the totalitarian system. We in Ethiopia should know exactly what he is talking about. Under the weight of TPLF abuse we harbor deep seated animosity towards each other, instead of fighting the common enemy we point fingers at each other. There is no association, organization club where we Ethiopians relate to each other with respect and dignity. Our political organizations have become places of division. Even our church is not immune from this sickness. We see our Muslim brother resisting and we learn the power of steadfastness and unity of purpose. That is one group of citizen with anti Woyane virus shot.
One fact that should be made clear is that the TPLF party is not practicing this criminal behavior all by itself. We have to look at the enablers that grease the wheels to hurt our own people and destroy our country. Those Amharas’, Oromos’, Wolaitas’, Tigreans’, Hararis’ and others in position marginal power and the willing Diaspora that invests on stolen land and fake buildings are part of this national degraedation. What are going to tell your children when Ethiopia becomes another Somalia, the future Iraq or a dying Syria? When they ask you why didn’t you do something daddy or mommy how are you going to answer? You cannot say I did not know because that would be a lie. You cannot claim I tried because that would not be true. No one would say I did not stand up straight because I am spineless. When you go to sleep tonight think about it, please?
This article is based on the following works

Posted By.Dawit  Demelash

ምርጫ ቦርድ እንደተጠበቀው ተጨማሪ የመመዝገቢያ ቀን ሰጠ

ጥር ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በተመዝጋቢዎች ድርቅ የተመታው መጪው የወረዳና የአካባቢ ምርጫ ምዝገባ ለሁለት ቀናት የተራዘመ ሲሆን፣ ኢህአዴግ ካድሬዎች በዩኒቨርስቲዎች ሳይቀር እየገቡ፣ ግለሰቦች እንዲመዘገቡ ካልሆነ ግን ችግር እንደሚደርስባቸው እየገለጡ ነው።
የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ካድሬዎቹ በዩኒቨርስቲዎች እየዞሩ ሰራተኞችን ተመዝግባችሁዋል አልተመዘገባችሁም እያሉ ሲጠይቁ ውለዋል።
የኢህአዴግ ካድሬዎች በምርጫው ያልተመዘገቡትን ” ከእኛ ጎን ናችሁ ወይስ ከአሸባሪዎች ” በማለት እያስፈራሩ እንደሚገኙ ኢሳት ያነጋገራቸው በርካታ ሰዎች መግለጻቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
33 የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ለኢህአዴግ ምርጫ አጃቢዎች አንሆንም በማለት ራሳቸውን ለማግለል መወሰናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢህአዴግ በበኩሉ ተቃዋሚዎች በምርጫው የማይሳተፉት ጥቅም ስለማያገኙበት ነው በማለት ተቃዋሚዎች ለወሰዱት እርምጃ መልስ ሰጥቷል።
ምርጫ ቦርድ የተመዝጋቢዎች ቁጥር በእቅዱ የተቀመጠውን ያሟላ ነው በማለት ቢገልጽም ፣ ኢሳት ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው እስካሁን የተመዘገበው ህዝብ ከታቀደውም ከግማሽ በታች ነው።
Posted By.Dawit Demelash

     Tigray People's Democratic Movement (TPDM) in Action







ሕወሐት ለሁለት ተሰነጠቀ፤ ወረቀት ለአባለት ተበተነ

ከኢየሩሳሌም አርአያ
ዛሬ በመቀሌ ለአባላ ትና አልፎም ለህዝቡ በተበተነ የትግርኛ ፅሁፍ እነ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ፀጋዬ በርሔ ከነባለቤታቸው እንዲሁም ሌሎች ከድርጅቱ እንዲባረሩTigray People Liberation Front Split በተበተነው መግለጫ ተጠቁሞዋል። በመግለጫው፥ ከጀርባ አሉ የተባሉትና « የዚህ መኅንዲስ» ተብለው የተፈረጁት ስብሃት ነጋ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተባሉት መካከል በዋነኛነት ተፈርጀዋል። እነ ቴውድሮስ ሃጎስ፣አዜብ መስፍንና በረከት እጃቸው እንዳለበት የተነገረለት ይኸው መግለጫ ተከታዩን ይመስላል፤
«ተቆርቋሪ ለሆናችሁ የትግራይ ተወላጆ በሙሉ፤

«ድርጅትህ ሕወሐት እስከ ዛሬ ታግላ እዚህ ደረጃ አድርሰሃለች። በተለይም የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪ የነበረው ባለ ራዕይው መሪህ በቅርብ ጊዜ አጥተኽል።
ዛሬ እነዚህን ደካማ ጐኖች ተጠቅመው ለጠላት አሳልፈው ሊሰጡህ የሚፈልጉ ያውም ደግሞ የእኔ የምትላቸው ጅቦች ተነስተውብህ ይገኛሉ። ይህንን ግልፅ ለማቅድረግ አሁን በቅርብ ጊዜ በመቀሌ የድርጅቱ ማ/ኰሚቴ ስብሰባ አካሄደን ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ ነው እንግዲህ ተከታዩ ነገር የተነሳው። ይኽውም፥ እነ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ፀጋዬ ከሚስቱ ጋርና ሌሎችም ያሉበት ይህን አሉ፤
«ድርጅታችን ጨርሶ ተዳክሞዋል። እኛ የኢትዮጲያ ሕዝብ ትግል መስራች ሆነን ሳለ ወደኋላ ተገፍትረን በአንፃሩ ሌሎች ከእኛ ኋላ የተፈጠሩና ራሳችን ያሳደግናቸው ሲጠናከሩ ድርጅታችን ግን እየተዳከመ በመሄድ ላይ ነው። ባዛው መጠን ሕዝባችን እየተጎዳ ነው። ስለዚህ አሁን ካጋጠመን አደጋ መውጣት ካለብን ከድርጅቱ -የተወገዱትን ግን በመጥፎ ጎዳና ያልተሰማሩትን መልሰን ወደ ፓርቲው ማስገባት አለብን። ይህ ካልሆነ ግን የሕዝብ ትግል አውላላ ሜዳ ላይ ጅብ በልቶት ሊቀር ነው።» በማለት ከጠላቶቻችን ጋር እንታረቅ እያሉን ነው።
“ሕዝባችን አስተውል። በዚህ አይነት ዳግመኛ በድርጅታችን ተኃድሶ እንደሚያስፈልገን ነው የተገነዘብነው። በሚቀጥለው የካቲት ወር በሚካሄደው ጉባኤያችን ይህንን ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶና አጥርቶ (ውሳኔ አሳልፎ) እንደሚወጣና እነዚህንና መሰሎቻቸው ከሚያራምዱት አቋም ጋር ጠራርጐ እንደሚያስወግድልን ተስፋ እናደርጋለን። በዚህም እያንዳንዱ እንደከዚህ ቀደሙ የተለመደ አስተዋፅኦ (ሚና) እንደሚያበረክት አንጠራጠርም።
በተጨማሪ ከጀርባ ሆኖ የዚህ አፍራሽ ዋና ቀያሽ መሃንዲስ ስብሃት ነጋ መሆኑን ደርሰንበታል።”
ከመቀሌ…
Posted BY.Dawit Demelash

Monday, January 28, 2013

የኦሮሞ ተወላጆች የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ጠየቁ

ጥር ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በኦሮሞ ጥናት ማኅበር፣ በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ድርጅት፣ የኦሮሞ ወጣቶች ራስ አገዝ ማኅበር፣ የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግና የኦሮሞ ድጋፍ ቡድን የተዘጋጀው ደማቅ የተቃውሞ ሰልፍ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ኦልባና ሊሌሳን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
የአሜሪካ ድምጽ እንደዘገበው ከአቶ በቀለ ገርባ እና ከአቶ ኦልባና ሌሊሣ በተጨማሪ በስም የተጠቀሱት ወልቤካ ለሚ፣ አደም ቡሣ፣ ሃዋ ዋቆ፣ ሞሐመድ መሉ፣ ደረጀ ከተማ፣ አዲሱ ምክሬ እና ገልገሎ ጉፋ በእሥር ላይ እንደሚገኙ የሠልፉ አስተባባሪዎች ተናግረዋል፡፡x

የኦሮሞ ተወላጆች ሠልፍ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት
የኢትዮጵያ መንግሥት አቶ በቀለ ገርባን፣ አቶ ኦልባና ሌሊሣን፣ እንዲሁም ሌሎቹንም ሰባት የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ በፖለቲካ ምክንያት ተይዘው የረዥም ዓመታት እሥራት የተፈረደባቸውን ሰዎች ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ መንግሥት የኢትዮጵያን ሕገመንግሥት እንዲያከብር፣ ከፍርድ ውጭ የሆኑ ግድያዎችንና ንፁሃን ሰዎችን ያለክስ ለተራዘመ ጊዜ ማሠሩን እንዲያቆም የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ጫና እንዲያደርግ ጠይቀዋል።


ከዚህ በተጨማሪ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የምጣኔ ኃብት ድጋፍ ከመስጠቷ በፊት የፖለቲካ እሥረኞች ሁሉ እንዲፈቱ አስገዳጅ ጫና እንድታደርግ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የኦሮሞን ሕዝብና የሌሎቹንም ሰብዓዊ መብቶች፣ ሃሣብን የመግለፅና የመደራጀት ነፃነቶችን እንዲያከብር አሜሪካ እንድትጠይቅ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረታዊ የሆኑ የዜጎችን መብቶች የሚጥሱ አዳዲስ ሕግጋትን ሁሉ፣ በተለይ ፀረ-ሽብር የሚባለውን ሕጉን፣ የፕሬስ ሕጉን፣ የረድዔት ድርጅቶች በሃገሪቱ ውስጥ እንደልባቸው እንዳይንቀሣቀሱ የሚገድበውን የሲቪል ማኅበራት ማቋቋሚያ ሕጉን፣ እንዲሁም ስካይፕንና ሌሎችም የሚድያ አገልግሎት ዘዴዎችን መጠቀምን ሕገወጥ የሚያደርገውን በቅርብ ያወጣውን ሕጉን እንዲሠርዝ እንዲሁም መንግሥት የሃይማኖት ነፃነትን እንዲያከብር እና በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ውስጥም ጣልቃ መግባት እንዲያቆም የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት እንዲጠይቅ የሚሉ ጥያቄዎች መቅረባቸውን ሬዲዮው ዘግቧል።x

የኦሮሞ ተወላጆች ሠልፍ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት
ድርጅቶቹ ለኢሳት በላኩት መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት ደግሞ የአሜሪካ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ ላኢ ትርጉም ያለው ጫና ማሳደር ካልቻለ የኢትዮጵያ መንግስት በኦሮሞ እና በሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት ይቀጥላል።


የኦሮሞ ተወላጅ ለስቴት ዲፓርትመንት በቀጥታ ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በግልባጭ በላኩት ደብዳቤ ላይ አናሳው የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት ( ህወሀት) 40 በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን ህዝብ በሚወከለው የኦሮሞ ህዝብ ላይ ጥቃት እየፈጸመ ነው ብለዋል።
ደብዳቤው የሬቻን በአል ለማክበር በቢሸፍቱ የተገኙ 200 የኦሮሞ ተወላጆች ላለፉት አራት ወራት መታሰራቸውንና አሁንም አለመፈታታቸውን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በየጊዜው ላለፈው አንድ አመት በየሳምንቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እንደሚታሰሩ፣ በቅርቡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተነሳው የዘር ግጭት 99 ተማሪዎች አብዛኛኦቹ የአሮሞ ተወላኮች መታሰራቸውን አውስተዋል። እንዲሁም የህወሀት አገዛዝ ባለፉት 21 አመታት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ በአብዛኛው የአሮሞ ተወላጆችን ሲያስር፣ ሲያሰቃይና ሲገድል መቆየቱን ገልጸዋል።
በቃሊቲ እስር ቤት ከታሰሩ እስረኞች ውስጥ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት የኦሮሞ ተወላጆች መሆናቸውን ከእስር ቤት ፖለቲከኞች መናገራቸው ይታወቃል።
  Posted By Dawit Demelash

Sunday, January 27, 2013

ሰራዊታችን ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ፡ ብዛት ያላቸው ሴት ታጋዮችም ግንባሩን ተቀላቀሉ!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ነበልባል ጦር ጥር 17-2005 ዓ.ም በወልቃይት ጎብለል በተሰኘ የወያኔው መከላከያ ካምፕ ላይ በወሰደው ድንገተኛ ማጥቃት በካምፑ የሚገኙ የመከላከያ አባላትን ደምስሷል። በውጤቱም 25 ሙት 36 ቁስለኛ እንዲሁም 20 ክላሽንኮፍ ጠብመንጃ ፣ 4 የእጅ ቦንብና 1 ስናይፕር ጠብመንጃ ከነ ሙሉ ትጥቁ በመማረክ በማግስቱ ማለትም በትናንተናው እለት በቀጠለው የነበልባል ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት በወልቃይት ጠበቆ በተባለ ቦታ 24 የአገዛዙ ታጣቂዎች ሙትና 29 ቁስለኛ ሆኗል። በድምሩ በሁለት ቀናት ውጊያ በጠቅላላው 49 ሙት 65 ቁስለኛ ሲሆን፦ የአምባገነኑ አገዛዝ ሰራዊት የአርበኛውን ጡጫ መቋቋም ተስኖት እግሬ አውጭኝ ብሎ ከመፈርጠጡም ባሻገር የውጊያ ሞራሉ ክፉኛ በመዳከሙ ምክንያት በአድጎሹ ፣ አደባይ፣ሁመራና እድሪስ አካባቢ የሚገኙ የጦር አመራሮች በመሰባሰብ የመልሶ መቋቋም እንቅስቃሴ ላይ እንደተወጠሩ ታውቋል።
ነበልባል በመባል የሚታወቀው ልዩ ኮማንዶ የኢህአግ ሰራዊት በአርማጭሆ፣ ጠገዴና ወልቃይት ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት በመፈፀምና ሕዝቡን በማንቃት እንዲሁም በማስታጠቅ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ሴት ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ያሉበት በርካታ ወጣቶችን ወደ ትግሉ ጎራ እንዲቀላቀሉ አስችሏል።
ግንባሩን በጥር 18-2005 ዓ.ም የተቀላቀሉ ሴት አርበኞች የወቅቱን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያም እኛ ሴቶች አገራችን ኢትዮጵያ አይታው በማታውቅ ሁኔታ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው መስክ አዘቅት ውስጥ እንደምትገኝ አብራርተው የእነሱ የትጥቅ ትግልን የመጨረሻ አማራጭ አድርገው የደም፣ የአጥንት፣ የጊዜ፣ የጉልበት፣ የእውቀት ብሎም የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን ለመቀላቀል ኢትዮጵያዊነት ስሜታቸውና ሕሊናቸው እንዳስገደዳቸው በመግለፅ መላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ዘር፣ ቋንቋ፣ ሐይማኖትና ፆታ ሳይለይ ከትግሉ ጎራ በመሰለፍ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ከጥፋት ሃይሉ የእብሪተኛ ቡድን የምናላቅቅበት ወቅት አሁን ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርን በጥር 18-2005 ዓ.ም የተቀላቀሉ ሴት አርበኞች አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር
posted by Dawit Demelash

29 ፓርቲዎች ነገ ባለ 15 የመግባቢያ ነጥብ ያፀድቃሉ

የካናዳው ‹‹ቃሌ የኢትጵያውያን የውይይት መድረክ›› ከጎናችሁ ነኝ ብሎናል


29ኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመታገል ባለ አስራ አምስት ነጥብ የመግባቢያ ሰነዱ ላይ ነገ ተወያይተው እንደሚያፀድቁት የተገለፀ ሲሆን አገሪቱንና ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የፓርቲዎቹ ሰብሳቢ አስታወቁ፡፡ የመግባቢያ ሰነዱ የህዝብ የበላይነት እንዲሁም ዲሞክራሲያዊ መብቶች የተከበረበት ዘላቂ ህገ መንግስታዊ የመድብለ ፓርቲ ድሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባትን ዓላማ ያደረገ እንደሆነና ውይይቱ ፓርቲዎቹን ወደ አንድ ፓርቲነት ሊያመጣቸው እንደሚችል ተገልጿል፡፡ የመድረክ የስራ አስፈፃሚ አባልና የፓርቲዎች ሰብሳቢ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ እንደጠቆሙት፤ ለሃያ ዘጠኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመግባቢያ ሰነዱ የተበተነላቸው ሲሆን ፓርቲዎችም በባለ 15 የመግባቢያ ነጥቦች ላይ በመስማማታቸው፣ በነገው ዕለት ውይይት አድርገው በሰነዱ ላይ ለመፈራረም ተዘጋጅተዋል።
የመግባቢያ ሰነዶቹ በዋናነት የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅሞች የሚነኩ ጉዳዮችንና መንግስት በሚወስዳቸው የሀገርና የህዝብ ጥቅም በሚጎዱ እርምጃዎች ላይ የጋራ አቋም መያዝ፣ የመግባቢያ ሰነዱን የሚፈርሙ ፓርቲዎች አባላት ከመንግስትም ሆነ ከገዥው ፓርቲ የሚደርስባቸውን የተለያዩ ህገወጥ ርምጃ በጋራ መታገል፤ ምርጫን በተመለከተ የጋራ ስትራቴጂ መቀየስ፤ ፓርቲዎቹ በሚያደርጉት ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ሁሉ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ወጥነት ያለው አቋም መያዝና ትግላቸው ለማቀናጀት እንዲችሉ የህዝቡን የአንድነት መንፈስ የሚያጐለብቱ እርምጃዎችን በጋራ መውሰድ፣ አፍራሽ የመከፋፈል የማጋጨት እርምጃዎችን መከላከል፣ ትብብሩን ወደ ላቀ የፓርቲ አደረጃጀት ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ መቀየስ እና ሌሎች አገራዊና ህዝባዊ ነጥቦች ላይ በጋራ ለመስራት ያለሙ ሲሆን ለዚህም አብይ ኮሚቴና የተግባር ኮሚቴ እንደሚዋቀር ታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሃያ ዘጠኙ ፓርቲዎች አመራር አባላት በካናዳ አገር ከሚገኘው ‹‹ቃሌ የኢትጵያውያን የውይይት መድረክ›› ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይና የፖለቲካ ሁኔታ ላይ በፓልቶክ ውይይት ያደረጉ ሲሆን መድረኩ በማቴሪያል፣ በፋይናንስና በዲፕሎማሲ ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ሰብሳቢው አስታውቀዋል፡፡ የካናዳው ‹‹ቃሌ የኢትጵያውያን የውይይት መድረክ›› በምታደርጉት ሰላማዊ ትግል ከጎናችሁ ነን ብሎናል ብለዋል – አቶ አስራት፡፡ መድረኩ ይሄን ስያሜ ለራሱ የሰጠው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር የነበረችውን የወ/ሮ ብርቱካን ሚደቅሳን ‹‹ቃሌ›› ዝግጅት ለማስታወስ ይሆናል ያሉት አቶ አስራት፤ አንድነት ፓርቲ ከዚህ በፊት በየወሩ “ቃሌ የጥበብ ምሽት” በሚል የሻማ ማብራትና የውይይት መድረክ ያካሂድ እንደነበርና አሁን ግን ‹‹ቃሌ ምሽት››ን ቀይሮ ‹‹የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ምሽት›› በሚል በየወሩ የሻማ ማብራትና ውይይት እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
Posted by: Dawit Demelash

ሒትለርና አይሁድ፤ መለስና፤ ስብሀት አማራ


ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛና ደራሲ)
ውድ አንባቢያን “ዘራፊ ሚሊየነሮች” ለሚለው ጽሁፍ ካደረሳችሁኝ መልሶች አጠር ያለውን አንዱን እንመልከትና ወደሚቀጥለው ጉዳይ እናመራለን። “ ወዳጄ ስለነዚህ እርጉም ሰዎች የጻፍከዉን ከማህደሬ አዉጥቼ ዛሬ አነበብኩት። እግዜር ይስጥህ። ምን እላለሁ። አፍዝ አደንግዝ እንደተደረገብን ሁሉ ዝም ብሎ ማየት ሁኗል ።ጉርሻ በሚሸጥበት አገር ሰዉ በቁንጣን አለቀ ሲሉን ለማመን ይዳዳናል። ምን አይነት እርጉም ወራዳ ትዉልድ እንደሆንን ነዉ የሚያሳየዉ።
የትግሬ እና የሻቢያ ምሁራን ቀጥፈዉ ዋሽተዉ በድፍረት የሌለ ታሪክ ታሪክ አድርገዉ ተከታዮቻቸዉን እያሳመኑ ነዉ። የእኛ ምሁራን ደግሞ ሲሞዳሞዱ ጥቅም አይቅርብን ብለዉ ሲልከሰከሱ ስለኢትዮጵያ ከሞላ ጎደለ የሚጽፈዉ ያዘነልን ነጭ ሁኗል። ቢያስቡት ቢያስቡት መልስ የሌለዉ ነገር ነዉ። ነገር ግን ትግሬን ምን አደረግነዉ? ትግሬ ከሌሎች ወገኖች በላይ የደረሰበት በደል ምንድነዉ? ኢትዮጵያን ሊያጠፋ የተነሳበት ምክንያት ምንድነዉ? የሚለዉ ነገር ሁልጊዜ ጥያቄ ዉስጥ ይከተኛል።
የሚገርመዉ በኢትዮጵያ አንድነት ከምንም በላይ ተጠቃሚ የነበረዉ ትግሬ እና ጉራጌ ነበር። ምክንያቱም ካካባቢያቸዉ ወደሌላዉ የኢትዮጵያ ክፍል እየተዘዋወሩ ይጠቀሙ ነበር። ታድያ እነዚህ ከተንኮል ድርና ማግ የተሰሩ ዘወትር ቢላ እየሳሉብን እኛ ስንገነባ እነሱ ሲያፈርሱን እዚህ ደርሰናል። በጽሁፍህ ያልተስማመሁበት የትግራይ ህዝብ ከፍተኛ በደል ላይ እንዳለ ጠቁመሀል።፡በዉነቱ ለእነሱ የዚህ አይነት አባባል ከማሳቅ አልፎ ሌላዉን ሽንታም እያሉ ያላግጡበታል። ከእዉነታዉ ጋር ስለማይዛመድላቸዉ አያምኑትም። የትግራይ ህዝብ በጣም ደስተኛ ነዉ። በፖሊሲ ደረጃ አቦይ ስብሀት አላማችን ለሚቀጥለዉ 10 አመት የትግራይን ህዝብ ወደ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ ማሸጋገር ነዉ ብሏል። መቀሌ ዛሬ ደረጃዋ ከአዉሮፓ እኩል ነዉ። ለግንዛቤ እንዲረዳህ ተከታታይ እዛ የሚሰራ የአገር ቤት ትያትር ስላለ እሱን መመልከት ነዉ። የነጻ ትምህርት እድል 100% የሚሰጠዉ ለትግሬ ነዉ ይህም በስዉር አይደለም መለስ ዜናዊ አማራዉ ቀደም ባለዉ ጊዜ ስለተጠቀመ ነዉ ብሎ መልሷል። እዉነትነቱን እንድትመረምር ላንተ ትቸዋለሁ። ወደ አሜሪካ እና አዉሮፓ እየተዘዋወሩ የሚነግዱት ትግሬዎች ናቸዉ። ከትግራይ መጥተዉ ቦታ ተስጥቷቸዉ ሽጠዉ እንዲጠቀሙ የተደረጉት ትግሬዎች ናቸዉ። ብዙ ብዙ ብዙ ማለት ይቻላል። ትግሬ ተጠቃሚ ነዉ ያለዉንም መንግስት በጣም ይደግፋል። ተበድለናል ካሉም እነሱ እራሳቸዉን ለመከላከል ብቃቱ ስላላቸዉ እነሱዉ ይንገሩን እንጅ እኛ የሌለ በደል ባንፈጥርላቸዉ ጥሩ ነዉ። ያለበለዚያ ምንም አልበደልንም ማለት ነዉ በማለት ልጓሙን ያጠብቁብናል። አንዳንድ የዋሆች አዲስ አበባ ደርሰዉ ሲመለሱ ለማኙ ሁሉ ትግሬ ነዉ ይላሉ። እንዴት ያስቃል ያ በትግርኛ የሚለምነዉ ሰዉ ሚስቱን ተቀምቶ የተባረረ የወልቃይት እና ጠገዴ ህዝብ እንጂ ትግሬ አይደለም።
በተረፈ ጽሁፍህ አንጀት ያርሳል። ጽሁፍህም የደረሰኝ በትግሬዎች አማካኝነት ነዉ። የዛን አይነት ድረ ገጽ እንኳን ለማዘጋጀት አልታደለንም። አብረሀ በላይ የፈለገዉን ያወጣል የፈለገዉን ይጥለዋል። ለምሳሌ ፐሮፌሰር ጌታቸዉ ስለ ምንሊክ እና ዮሀንስ የጻፉት በግማሽ ቀን ዉስጥ ተሰርዟል። የዮሀንስን ክፉነት ስላመላከቱ።”
ውድ እንባቢያን ለደብዳቤዎቻችሁ ሉላችሁንም አመሰግናለሁ። ዛሬ ለመንገር ወደፈለኩት ጉዳይ እንሂድ፤ እነሆ…
እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር ጃንዋሪ 30 1939 ዓም አዶልፍ ሒትለር ሬግታንግ ጀርመን ውስጥ ንግግር ሲያደርግ “ከንግዲህ ጦርነት የሚነሳ ከሆነ ከጀርመን ውስጥ አይሁዳውያንን ነው የማጸዳው። አይሁዳውያን ናቸው ከምድርገጽ የሚጠፉት” ብሎ ተናግሮ ነበር።
እነመለስ ስብሀት ትግል ሲጀምሩ በፕሮግራማቸው ጽፈው ካስቀመጡት ነገር አንዱ “አማራው ካልተመታ.. የትግራይ ነጻነት የማይታሰብ ነው። መጀመሪያ አማራው መመታት አለበት.. መንበርከክ አለበት” ብለው ነበር።”..አማራ..አማራ.አማራ..አማራ.. አማራ…” ሆነ ህልምና ቅዠታቸው ከውልደት እስከ እለተሞቻቸው።
“”Holocaust History” በሚል ፕሮጀክት አይሁዶች ያለቁበትን ሁኔታ የሚያጠና የታሪክ ተቋም www.holocaust-history.org “ለምንድነው ያሁሉ እልቂት በአይሁዶች ላይ የተፈጸመው?” የሚል ጥያቁ ባቀረቡለት ቁጥር የሚሰጠው መልስ “ሒትለር አጥብቆ ስለሚጠላቸው ብቻ ነበር” የሚል ነው። ቀጥሎ አንግዲህ የሚነሳው ጥያቄ “ለምን ነበር ሂትለር አይሁዶችን የጠላቸው” የሚለው ሆነ።
በተመሳሳይ ሁኔታ መለስ ስብሀት ወደስልጣን አንደመጡ ባይሳካም(ለምን እንዳልተሳካላቸው ወደፊት እናወጋለን) ፍጅቱን ባማሮች ላይ ጀምረውት ነበር፤ “ለምንድነው አማራውን ሕዝብ ሊጨርሱ የተነሱት?” የሚል ጥያቄ ይህ ድርጅት ቢገጥመው “ መለስ ስብሀት አማራዎችን ስለሚጠሉአቸው ስለሚፈሩአቸው ብቻ ነው።” የሚል መልስ እንደሚሰጥ እኔ አልጠራጠርም። “ለምን አማራን ጠሉት?..ፈሩት?” ሁላችሁም የሚመስላችሁን ተናገሩ።
ሂትለር አይሁዶችን የጠላበት የፈራበት ሁኔታ ሲነገር፤ ያንን ያክል ጥፋት የሚያስደርስ ነው ባይባልም፤ የታሪክ ተመራማሪዎቹ አንዲህ ይላሉ። በመጀመሪያ ደረጃ በ1930 ዎቹ ውስጥ በጀርመንም ሆነ በአውሮፓ ጸረ አይሁድነት አስተሳሰብ የተንሰራፋ ችግር ነበር።ለዚያም መሰረቱ በመጽሀፍ ቅዱስ ታሪከ ክርስቶስን የሰቀሉ ናቸው የሚለው መንፈሳዊ ትምህርት ዋናው ያስተሳሰብ ዘዋሪ እምነት ነበር። ሁዋላ ላይ ግን ያን ሀይማኖታዊ ጥላቻ አንዳንዶች ወደ ፖለቲካ አጀንዳ ለውጠውት ለእኩይ የፖለቲካ አላማ ህዝብን በስራቸው ማሰባሰቢያ ፕሮፓጋንዳ አደረጉት። (አሁን ባገራችን የጎሳ ባህላዊ ግጭቶችን ወያኔዎች የፖለቲካ ልዩነት ቅርፅ ለመስጠት እንደሚሞክሩት አይነት) አይሁዳውንያን በጀርመንም ሆነ ባውሮፓ የላቁ ምሁራን፤ የላቁ ሀኪሞች፤ ፕሮፌሰሮች ፖለቲከኞች በሁሉም መስክ የተዋጣላቸው ሰዎች ስለነበሩ፤ ብዙ ፖለቲከኞች ይፈሯቸው፤ ይቀኑባቸው፤ ይጠሏቸውም ነበር።ሂትለርም አንዱ እንደነበር ታሪኩ ያወሳል። ጀርመን በአንደኛው የአለም ጦርነት የተጠቃችው በነሱ ምክንያት እንደሆነ ያምን ነበር።”በስለላና በመረጃ ጠላትን እያገለገሉ..” ይላል። እናም አንዳንዶች ይህን በመላው አውሮፓ የነበረ ጸረ-ሴማዊነት ወረርሽኝ አንደ መሰረት አድርገው ሂትለር ያንኑ ነው ያጠናከረው የሚሉ አሉ።
ሌላው ወገን ደግሞ ሂትለር አይሁዶችን የጠላበት ምክንያቱ ቪየና ውስጥ አንድ የስነጠበብ ትምህርት ቤት ለመማር ፈልጎ፤ተቋሙ፤ “ትምህርቱን መከታተል የሚያስችልህ ተሰጥኦና ችሎታ የለህም” ብሎ ማመልከቻውን ውድቅ አደረገበት። የኮሌጁ መምህራንና አስተዳዳሪዎች ባብዛኛው አይሁዳውያን ስለነበሩ በዚያው ቂምና ጥላቻ ቋጠረ።
ገሚሱ ደግሞ እንደሚለው ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ቀድሞ ሂትለር ከመነሳቱ በፊት በነበረችው ጀርመን ህብረተሰብ ውስጥ፤ አይሁዳውያን በማናቸውም መስክ የተዋጣላቸው (አሁን በአሜሪካ እንዳሉት ማለት ነው) የተሳካላቸው ስለነበሩ፤ ከቁጥራቸው ማነስ አንጻር ከሌላው የጀርመን ዜጋ ጋር ሲያስተያዩዋቸው፤ በትምህርት፤ በንግድ፤ በማናቸውም የስራ መስክ የላቀውን ስፍራ ይዘው ሰለነበር፤ በሂትለር አስተሳሰብ በተንኮልና በሻጥር መላውን የጀርመን ዜጋ ቁልቁል ይዘው እነሱ የበላይ ሆኑ ብሎ ያምን በዚያም ምክንያት ይጠላቸው አንደነበር ተጽፏል።አሁን በኢትዮጵያ መለስ ስብሀት ከልት ስለ አማሮች እንደሚያስበው ማለት ነው። እርግጥ የአማራውን ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተለየ ተጠቃሚም ሆነ ተጎጂ የሚያደርገው ምንም ነገር የለም። ድህነትና ጭቆና የዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ የጋራ እሴት ናቸው።
ናዚ ሂትለር ወደ ስድስት ሚሊዮን የሚሆኑ አይሁዳውያንን የፈጀበት ድርጊት ትምህርትነቱ ይላል ይኸው ፍጅቱን የሚያጠናው ተቋም፤ “በተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል ጥላቻ የተመረዙ ግለሰቦች ወደ ስልጣን ሲመጡ፤ ሀገር የመምራት እድል ካገኙና አንድ ችግር ከተፈጠረባቸው፤ ለዚያ ችግር ምክንያቱ ነው ብለው የሚያምኑት ያ የሚጠሉት የህብረተሰብ ከፍል ስለሚሆን ሂትለር ባይሁዶች ላይ እንዳደረገው ተመሳሳይ እልቂት ሊፈጽሙ አንደሚችሉ ይታመናል” ይላል ሰነዱ።
“ያንድ ህብረተሰብ ክፍል ጥላቻ ይዘው ወደ ስልጣን የመጡ…” የሚለው ነገር በቀጥታ ወደ እኛው ጉዶች ያመጣናል። መለስ ስብሀት የሚመሩት የወያኔ መሪዎች ቡድን አማራውን ከዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ ነጥለው ለምን ይጠሉታል? ለምን ይፈሩታል? ያኔ በረሀ የነበሩ ጊዜ እንኳ “መላ ኢትዮጵያን ተቆጣጥረን ይህን እድል እናገኛለን” ብለው የሚያስቡ ስላልነበረ ያሻቸውን ይበሉ። ባለፉት ሀያሁለት አመታት ወደደም ጠላም የኢትዮጵያ ሕዝብ እጃቸው ላይ የወደቀ ህዝብ ነው። ሐገር አስተዳድራለሁ የሚል መንግስት የሚያስተዳድረውን ህዝብ አንዱን እያሞገሰ አንዱን ባደባባይ እየሰደበ የሚኖር ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው። “.. ገድለን የቀበርነውን አማራ አታንሱብኝ…..” ጀነራል ሳሞራ ዮኒስ። ‘’.. ለትምክተኛ አማራ ስልጣኑን አንለቅም….” መለስ ዜናዊ። “…ስልጣኑን ካማራና ከኦርቶዶክስ እጅ አውጥተነዋል…..” ስብሀት ነጋ። ‘’ ..ሱማሌ የከብት ጭራ መከተል እንጂ ራሱን ማስተዳደር አይችልም ይሏችሁ ነበር።… ዛሬ እራሳችሁን ማስተዳደር እንደምትችሉ አሳዩአቸው…ነፍጠኞችን..” ታምራት ላይኔ ጂጂጋ 1983። (አሁን እራሳቸው ጌቶቹ የጁን ሰተውታል፤..አያሳስብም)
ልብ ይሏል፤ መለስ ዜናዊ አማራውን አንዴት ይጠላ እንደነበር። የወያኔ መሪዎች ስብሀት ነጋና ሌሎቹም ሁሉ፤.. ዋና ዋና የጦሩን አዛዦች ጨምሮ.. በዚህ ህዝብ ላይ ያላቸው ጥላቻና ፍራቻ ከቁጥጥራቸው ውጭ የወጣ በመሆኑ በያጋጣሚው በአንደበታቸው ሲገልጹት መስማት እንግዳ ነገር አይደለም። ሀያ ሁለተኛ አመታቸው። ለምን?.. መቼ ነው የሚማሩት? ..መቼ ነው የሚታረሙትስ? የኢትዮጵያ ህዝብ እነሱን ትምህርት ቤት ለመጨመር፡ ይህን የደንቆሮ ጡንቻቸውን ለማምከን እንደገና ጦርነት መክፈት ሊኖርበት ነው?
ለምሆኑ የጥላቻቸው መሰረት ምንድነው?
ሂትለር ሁለተኛው የአለም ጦርነት አካባቢ፤ “ጦርነት ከእንግዲህ በሗላ ከተቀሰቀሰ” አለ “አይሁዶችን አያድርገኝ”… እንዳለውም መጀመሪያ እራሱ ፖላንድን በመውረር ጦርነቱን ሲባርከው ሶስት ሚሊዮን የሚሆኑ አይሁዳውያን በቁጥጥሩ ስር ወደቁ። ከዚያ ወደ ሶቬት ሲዘምት ያንኑ ያህል ህዝብ እጁ ገባ። እነሱን እየመነጠረ ወደ መቀቀያ ካንብ ይሰበስባቸው ጀመር። ገድሎ ገድሎ መጨረስ ሲያቅተው።
እነመለስ ስብሀት በጦርነቱ ወቅት፤ ጦርነቱ ሰልችቶት የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት በገፍ እየሄደ ሲማረክላቸው፤ “አማራ ነን” ያሉትን የዋሀን እየመረጡ በመርዝም በጥይትም ይፈጇቸው ነበር። ከባድ የጉልበት ስራ እያሰሯቸው ጉርጓድ እስር ቤት እያጎሯቸው ሰውነታቸው እስኪተላ እየደበደቧቸው ይገሏቸው ነበር።
ሂትለር ስልጣኑን ከተቆጣጠረበት ጃንዋሪ 1933 ዓም ጀምሮ በአይሁዳውያን ላይ ባደባባይና በሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን ሽብር መንዛት ጀመረ።ባይሁዳውያንና በሌሎች የጀርመን ዜጎች መካከል የልዩነት ግንብ መገንባት ጀመረ።
በተመሳሳይ ሁኔታ እነመለስ ስብሀት መላ አገሪቱን ተቆጣጥረው የሽግግር መንግስት መሰረትን ብለው አዲስ አበባ ምክር ቤት ገብተው፤ መለስ ዜናዊ ምክር ቤት ውስጥ ለተሰበሰቡት የዘር ድርጅቶች በሙሉ፤ ለነባሮቹም ወዲያው አዳዲስ ለተፈለፈሉትም ሁሉ ወንበር ሲያድል፤ አማራውን አላስጠጉትም ነበር። ሁሉም መንግስት ናችሁ ሲባሉ ዘለሉ፤ ጨፈሩ፤ ያለወያኔ በአለም ላይ ሰው አልተፈጠረም አሉ።የብሄር ብሄረሰብ ተወካዮች። አንዳንዶቹ “በቃ ከንግዲህ እንደብርቅየ አራዊተ ታየን” አሉ። ኖርናት ።ሗላ ላይ ወያኔ እንደ አራዊቱ እያደነ ሊበላቸው። በገሀድ ግንቡ ያኔ መገንባት ተጀመረ።
ሂትለር ስልጣኑን እንደተቆጣጠረ አይሁዳውያንን በገፍ ከስራ ከትምህርት ተቋማት ከማናቸውም መስክ ማፈናቀሉን ተያያዘው።
እነመለስ ስብሀትም በተመሳሳይ ሁኔታ አማሮችንና ያማሮቹን አስተሳሰብ ይጋራሉ ያሏቸውን አርባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራንና ፕሮፌሰሮችን በማባረር የሂትለርን ስራ ደገሙት።ጀመሩት።እስከመጨረሻው ተያይዘውታል።
ሂትለር ወደ ስልጣን እንደመጣ ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ሽፋን የተሰጠው ስራ አይሁዳውያን በጀርመን ህዝብ ዘንድ እንዲጠሉ ለማድረግ ሀያ አራት ሰአት የፕሮፓጋንዳ ስራ መስራት ነበር።እኛ ቤትም ወያኔያዊው ፕሮፓጋንዳ ባጼ ሚኒሊክ ጀምሮ መላውን አማራ ነፍጠኛ እያለ ስድብና የውሸት ታሪክ ያዘንብበትና ወደ ታዋቂ ግለሰቦች ተራ በተራ በመሄድ የሚያታክት ፕሮፓጋንዳ ይሰራ እንደነበር አይዘነጋም። እነ ጥላሁን ገሰሰ፤ እነ ፐሮፌሰር አስራት ወልደየስ፤ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪአም፤ ሚትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ፤ ሁሉንም መዘርዘር አይቻልም፤ በሀገሪቱ ውድ ዜጎች ላይ ይነዛ የነበረው ስም የማጥፋትና የማጥላላት ፕሮፓጋንዳ በነጻው ፕሬስ ጀግኖች ከመመታቱ በፊት ምን ያህል አማራው ላይ ያነጣጠረ እንደነበረ ኢትዮጵያውያን የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ስለሆነ መደጋገም አያሻም።
ሂትለር በአይሁዳውያን ላይ ያንን ሁሉ እልቂት ሲያደርስ ጀርመናውያን ባለመቃወማቸው ለድርጊቱ ተባባሪ መሆናቸውን አመልክተው ነበር። እርግጥ የኛ ህዝብ ከወያኔ ጋር አልተባበረም።
የሂትለር ድርጊቱ የራሱ ብቻ የሆነ ግለሰባዊ እቅድ ከመሆን አልፎ የፓርቲው ማለትም የናዚ ሶሻሊስት ፓርቲ መርህ እንዲሆን በመደረጉ፤ በወቅቱ ጀርመናውያን ባብዛኛው የፓርቲው አባልና ደጋፊ እንዲሆኑ በመገደዳቸው፤ እናም ባንድ አንባገን ግለሰብ የሚመሩ በመሆናቸው የፓርቲያቸውን አቋምና ፍልስፍና ሊቃረኑ አልቻሉም። እንደ ሕውሀት ግንባር አባላት ደደብነት ማለት ነው።
ይህ የህውሀት ሶሻሊስት ግንባር አባላትን ከመምሰሉ ባሻገር አሽከሮቻቸውን ደርበንላቸው ኢህአደግ እንበላቸውና፤ ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት ህውሀት ያን ሁሉ ግፍ ባማሮች ላይ ሲፈጽም የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙበት ጊዜ ነበረ? ከጉራፈርዳ ከሀያ ሺህ በላይ አማሮች ንብረታቸውን ተቀምተው ሲባረሩ ድርጊቱ እንዲቆም ወይም ልክ አይደለም ሲል የተደመጠ የኢህአደግ አባል ድርጅት አለ? የናዚ ፓርቲ አባላትም በዚህ መልኩ ነበር በአይሁዳውያን ላይ የደረሰውን የደገፉት። ኢህአደጎችስ ለምን? የህውሀት ፍልስፍና አማራውን በማጥፋት ላይ የተመሰረተ ስለሆነ መቃወም ተግባራቸው አይደለም? ወይንስ ለራሳቸውም የህሊና ባሮች ሰለሆኑ በጌቶቻቸው ቡራኬና ይሁንታ የሚጣልላቸውን ትርፍራፊ እየበሉ መኖር ብቻ ነው።
በሂትለር እምነት አርያን የሚባለው የጀርመን ህዝብ ዝርያ በመላው ጀርመን ከሚገኙ ዘሮች ሁሉ የበላይነት አለው። ስለዚህ ሁሉም ዘሮች በስሩ ማደር አለባቸው። ሌሎቹ ዘሮች ስላቮችና ፖልስ የሚባሉት ዝቅ ያለ የሰውነት ደረጃ ስላላቸው ለአርያን ዘሮች ነው ማገልገል ያለባቸው። አይሁዶች ጭራሹኑ ጥገኛ ተውሳካት ስለሆኑ መጥፋት ነው ያለባቸው። ሂትለር ያኔ በሚፈልጋት የጀርመን አይነት እንደተመኘው ሁሉ በመለስ ስብሀት ሰራሿ ኢትዮጵያም እነሆ ሀያ ሁለት አመታት ወያኔ መላው ኢትዮጵያ በትግሬ ስር ነው ማደር ያለበት ብሎ እንዳመነና እንደተነሳ፤ ሁሉ በመንግስቱ ስራ ፈላጭ ቆራጭ ቀጣሪ አባራሪ፤ ትግሬ። በግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ፈላጭ ቆራጭ ተቆጣጣሪ ሰሪ ፈጣሪ፤ ትግሬ። በውትድርናው ዘርፍ ፈላጭ ቆራች ዘማች አዝማች መሪ ትግሬ፤ ሆንና አፈፍነው። እንደ ሂትለር ምኞት አርያኖች አልተሳካላቸውም። የመለስ ስብሀት ምኞት ግን በሚገባ ተሳክቷል።ለጊዜውም ቢሆን የኢትዮጵያ ህዝብ በነሱ ስር ወድቋል።
ዛሬ በህይወት የሚገኙ የናዚ ወንጀለኞች ለፍርድ በሚቀርቡበት የኑረንበርግ ችሎት ላይ ኤሪክ ቮን ዴም የተባሉ ባለ ሶስት ኮከብ ጀነራል፡ በአይሁዳውያን ላይ ስላደረሱት እልቂት የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ሲጠየቁ “….ያ ፍጅት ሊቀር የማይችል የናዚ ፓርቲ ፍልስፍና መርህ ነበር ወይ?” ሲባሉ እንዳሉት “…ለአመታት…ለአስርት አመታት ስላቮች ከሰው በታች የሆኑ ፍጡራን መሆናቸውን ሰው እንዲያምን ተደርጎ ከተሰበከ፤ አይሁዶችም ጭራሽ ሰውም አይደሉም ብሎ ሰው እንዲያምን ከተሰበከ ያ እልቂት ሊቀር የማይችል ክስተት ነበር” ብለው እራሳቸው የጭፍጨፋው ተሳታፊ መሰከሩ። ሕውሀት ስለ አማራው ክፉ ነገር የሰበከውን ያህል የሰማው ኢትዮጵያዊ አለመኖሩ መበጀቱ፤ የከፋ ነገር ማድረግ እንዳይችል አድርጎታል።
እርግጥ ህውሀቶች የሂትለርን ድርጊት ካሁን ቀደም ባርሲ አርባጉጉ፤ በበደኖ፤ ባሰቦት ደብረወገግ ገዳም ከኦነጎች ጋር በመተባበር በሚገባ ጀምረውት ሞክረውት ዳር አልደረሰላቸውም። አማራውን በመጥላት የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያግዛቸው አልቻለም። በኢትዮጵያ የሚገኙት ሰማንያ አንዱም ብሄረሰቦች ተፋቅረው ተከባብረው የሚኖሩና የኖሩ በመሆናቸው። የነመለስ ስብሀት ፕሮጀክት አልሰራም። ወደፊትም አይሰራም። የራሳቸው መጥፊያ ግን ይሆናል። የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ሩዋንዳ ህዝብ ጎረቤት በጎረቤቱ ላይ አይነሳም። ተራ የጀርመን ዜጎች ሳይቀሩ አይሁዶችን በማሳደድ በመግደል ሂትለርን አግዘውታል። እኛ ፍቅር በፍቅር በመሆናችን ይህ በሽታ የለብንም። ይህ በሽታ ያለው በወያኔዎችና አንዳንድ በዘር ተደራጅተው ከሚገኙ ደደቦች ደም ውስጥ ነው። ነቀርሳ ነው።
ለምሆኑ የወያኔ ጥቂት መሪዎች የአማራውን ሕዝብ ሊጠሉ የቻሉበት ምክንያት ምንድነው? ወደ ዘመነ መሳፍንት መለስ ብለን እስቲ አንድ ተያይዞ ሊመጣ የሚችል ነገር እንመልከት። በነበረው የርስበርስ ጦርነት ባጼ ቶዎድሮስ የተጀመረው ያሸናፊነት እና የበላይነት በአጼ ሚኒሊክ ሁሉንም ድል ማድረግ ሲጠናቀቅ፤ የየአካባቢው ንጉሶችና መሳፍንት የአሮሞውም የትግሬውም የከንባታውም ሁሉም ተሸንፈው ግዛቶቻቸው በአንድ ንጉሰነገስት ስር ሲወድቁ፤ አጼ ሚኒሊክ አገር የማቅናቱን ግዛት የማስፋቱን እርምጃ ቀጥለውበት ነበር። እናም በደቡብም በምስራቅም በየትም አቅጣጫ የሚልኩት ሰራዊት አብዛኛው አማርኛ ተናጋሪ ስለነበረ ተሸናፊዎቹ ቢገብሩም አማራውን አንደ ወራሪ መቁጠራቸውና መጥላታቸው አልቀረም ነበር።ያንኑ ጥላቻቸውን በህዝቡ ውስጥ ማሰራጨታቸውም አልቀረም።
ወደ ትግራይ በሽተኞች የመጣን እንደሆነ ዛሬ ያሉት አንጋፋ የህውሀት መሪዎች የሞተውን ጨምሮ አያቶቻቸውና አባቶቻቸው ወገናቸውንና ሀገራቸውን ከድተው ለጣሊያን ያደሩ አሽከሮችና ባንዳዎች ነበሩ። አባቶቻቸው እንዳወረሷቸው የጥላቻ ወሬና የፈጠራ ታሪክ፤ የአድዋው ድል የሚኒሊክ ድል፤ በነሱ አስተሳሰብ ሚኒሊክ አማራ ስለሆኑ ያማራ ድል ነው። በሁለተኛው የአለም ጦርነትም ባምስት አመቱ የወረራ ዘመን የነመለስ ስብሀት ወላጆችና ቤተሰቦች የጣሊያን ተላላኪዎችና አሽከሮች ሆነው፤ በሰላም እነዚህን ዛሬ የሚያቃጥሉንን ከሀዲዎች ለማሳደግ ጎንበስ ቀና ሲሉ፤ አርበኞች (በነሱ እምነት አማሮች) ጌቶቻቸውንም እነሱንም በዱር በገደል አናስወጣ አናስገባ ብለው ጣሊያንን አባረው የኢትዮጵያን ነጻነት ስላስመለሱ፤ ባንዳነቱ የቀረባቸው ወገኖች በአማራው ላይ የመረረ ጥላቻ ይዘው፤ በዚያው ጥላቻ ልጆቻቸውን ኮትኩተው አሳደጉ። ጣሊያንን ያባረረው ግን መላው የኢትዮጵያ ጀግና ነው። ኦሮሞ፤ አማራ፤ ትግሬ ወላይታ ወዘተ….ቢሆንም የእነመለስ ስብሀት ወላጆች ጌቶቻቸውን ያባረሩባቸው አማሮች እንደሆኑ አድርገው፤ ልጆቻቸው በአማራ ጥላቻ ተኮትኩተው እንዲያድጉ አደጉ። አሳሳቢው ነገር እነዚህ ሰዎች ካባቶቻው የወረሱትን ጥላቻ እነሱም ላልታደሉት ልጆቻቸው ማውረሳቸው ነው። ያም አልበቃ ብሎ የትግራይን ህዝብ ለመመረዝ ባለመታከት ስለ አማራ ህዝብ ክፉ ሲናገሩ መደመጣቸው ነው። መልካሙ ነገር ህዝቡ ከነሱ የቀደመ በመሆኑ ሊሰማቸው አይችልም። ምክንያቱም አማራ የሚባለው ሁሉ እንደ ትግሬ ደሀ ነው። እንደ ኦሮሞ ድህ ነው። እንደሶማሌ ድሀ ነው። እንደ አፋር፡ እንደ ከምባታ፡ እንደሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ድሀ ነው። ምን አይነት አማራ ነው ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ጠላት ነው ብለው የሚያስተምሩት? አማርኛው ቋንቋ የመንግስት የስራ ቋንቋ ስለሆነ ይሆን? ለልጆቻቸው አዝናለሁ። ገንዘብና ጥላቻን ለሚያወርሷቸው። አእምሮአቸው ተጋርዶ ለሚያመልኳቸው አዝናለሁ። ጥላቻን ለሚወርሷቸው፤ እናም በሰብአዊ ፍጡር ጥላቻ ታውረው ሕይወታቸውን ለሚያጨልሙ። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚጠላ ዘር የለም። የሚጠላ እና መጥፋት የሚገባው ገዢ ቡድን እንጂ።
እርግጥ የወያኔ መሪዎች የሚወዱት ወይም የቆሙለት የህብረተሰብ ክፍል አለ ማለት አይደለም። የሚወዱትም ራሳቸውን ነው። የቆሙትም ለጥቅማቸው ነው። አማራውን ብቻ ሳይሆን ኦሮሞውንም ጉራጌውንም ከንባታውንም አፋሩንም ሁሉንም በየጊዜው ይጨፈጭፉታል። እራሱን የትግራይን ህዝብም አይወዱትም። ሁለት ቀላል ማስረጃ እነሆ።
በጦርነቱ ዘመን የትግራይ ህዝብ እጅግ የከፋ ድርቅና ረሀብ ሲፈራረቅበት፤ ከመሀል አገር የእርዳታ እህል እንዳይደርሰው መንገድ በመዝጋት፤ እነሱ በተቆጣጠሩት አካባቢና ባልተቆጣጠሩትም አካባቢ “እኛ ነን ለህዝባችን ረድኤት ድርጅቶች የሚያቀርቡትን እርዳታ ማደል ያለብን” ብለው የተባበሩት መንግስታትን አስጨንቀው ለረሀብተኛው እንዲያከፋፍሉ መድሀኒትና ምግብ ይሰጣቸው ጀመር። ያንን በብዙ ሚሊዮን የሚገመት የእርዳታ እህልና ቁሳቁስ ከአረብ ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር በቀጥታ ባህር እያሻገሩ በመሸጥ፤ በኩንታሎች አሸዋ እየሞሉ ለጋሾችን በማታለል እንዲገዙአቸው በማድረግ፤ በሚሊዮን ዶላር ሲንበሸበሹ፤ የጦር መሳሪያ ሲሸምቱ፤ የትግራይ ህዝብ እንደቅጠል ይረግፍ ነበር። እነሱ በየጫካው ከሰራዊቱ እየተሸሸጉ አረቄ ጠግበው ከውሽሞቻቸው ጋር ከረቦ እየደለቁ እየጨፈሩ ይዳሩ ነበር። ሱዳን እየሄዱ ውድ ሆቴሎች ውስጥ ይዝናኑ ነበር።
ሕጻናት፤ እናቶች፤ አባቶች፤ በረሀብ ሲረግፉ፤…ለመዋጋት አቅም የነበራቸውን ልጆችና አዋቂዎች በእርዳታው ምግብ እያማለሉ ወደውጊያ ሲያስገቡአቸው፤ የቀሩት ሕጻናት፤ድኩም እናቶችና አባቶች በሙሉ፤… እንዲያልቁ አደረጉ። ይህ በሆነበት አካባቢ እነመለስ ስብሀት በዚያን ጊዜ አንድም ተቆጣጣሪ አካል ወይም የውጭም ሆነ የውስጥ ጋዜጠኛ እንዳይደርስ አድርገው የትግራይ ወገናችንን አስፈጁት። ይህንን አላደረግንም ካሉ በቀጥታ የዚህን ጽሁፍ አቅራቢ መሞገት ይችላሉ። እኔም ያደረጉትን በማስረጃ ማመላከት እችላለሁ።
ሁለተኛው፤ የአውዚንን ጭፍጨፋ እንዴት አንዳቀነባበሩት ማየት ነው። በተባለው ቀን አውዚን ከተማ ገብተው ጉባኤ አንደሚያካሂዱ ወሬው በቅድሚያ እንዲሰራጭና ደርግ ጆሮ እንዲደርስ አደረጉ። አስራ ሁለት ሰዎች ሱዳን ሄደው በቪዲዮ ካሜራ ቀረጻ እንዲሰለጥኑ ተደረገ። ሁሉም ዝግጅት ከተጠናቀቀ በሗላ አንድ ቀን በጠራራ ጸሀይ በአውዚን ሞቅ ያለ የገበያ ቀን፤ በተለያየ አቅጣጫ የህውሀት ሰራዊት ተሰልፎ እየተኮሰ ከተማ እንዲገባና ወደገበያው እንዲያመራ ተደረገ። ወዲያውም የኢትጵያ አየር ሀይል በነሱ ላይ ጥቃት መሰንዘር ሲጀምር፤ ታጋዮቹ በያቅጣጫው እየተሯሯጡና እየተኮሱ ገበያተኛውን እንዲቀላቀሉ ተደረገ። ሕዝቡንም ተቀላቀሉ ። ያ ሁሉ ትርምስና እልቂት ሲፈጸም እነዚያ በቪዲዮ ቀረጻ የሰለጠኑት ተዋጊዎች ዶኩመንታሪ ፊልማቸውን ያነሱ ነበር።በዚያው እለት ነበር ወደ ሱዳን ልከው ድርጊቱ ለአለም መገናኛ ብዙሀን እንዲዳረስ ያደረጉት። ያ እንግዲህ በነሱ ተንኮል ላይ የደርግ ደደብነት ተጨምሮበት በህዝባችን ላይ የደረሰ መከራ ነበር። ታዲያ አነዚህ ለማን ነው የቆሙት? እና እነዚህ አማራውን ብቻ ነው የሚጠሉት? መልሱን ለአንባብያን እተወዋለሁ።
http://www.ethiopiazare.com
posted by Dawit Demelash