Wednesday, October 12, 2016

ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ጉዳይ ሥጋቷን ገለፀች | VOA

የዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የውጥረት ሁኔታ ሥጋት ያደረባት መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ ቃል አቀባይ ጃን ኪርቢ ዛሬ ከአሜሪካ ድምፅ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ አስታውቀዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የውጥረት ሁኔታ ሥጋት ያደረባት መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ ቃል አቀባይ ጃን ኪርቢ ዛሬ ከአሜሪካ ድምፅ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ላነሷቸው የመሬት መብትና የምርጫ ሕግን ማሻሻያ የመሳሰሉ ብሦቶች መልስ ለመስጠት መንግሥት ቃል መግባቱን ፕሬዚዳንት ሙላቱ መስከረም 20 ለፓርላማው ያደረጉትን ንግግር መንግሥታቸው እንዳጤነው ቃል አቀባዩ ገልፀው የኢትዮጵያ መንግሥት ያቀረባቸውን ሃሣቦች ተግባራዊ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲንቀሣቀስ እንደሚያበረታታ አመልክተዋል፡፡

ኪርቢ በማከልም የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ሣምንት መጨረሻ ላይ የደነገገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ በተለይም ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰዎችን መያዝን፣ ነፃ ሃሣብን መገደብን፣ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ማገድን እና የሰዓት ዕላፊ ገደብ መጣልን የመሳሰሉ የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎቹን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግበትን ሁኔታ ግልፅ እንዲያደርግ መንግሥታቸው እንደሚፈልግም አስረድተዋል፡፡

እነዚህ እርምጃዎች ሥርዓትን ለመመለስ የታሰቡ ቢሆኑ እንኳአሉ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ጃን ኪርቢነፃ ድምፆችን ማፈንና በኢትዮጵያዊያን መብቶች ውስጥ እራስን የሚጎዳ ጣልቃ ገብነት ማድረግ ለብሦቶቹ መፍትኄ ከማግኘት ይልቅ ሁኔታዎችን የሚያባብሱ ነው የሚሆኑት፡፡

ምንጭ:-VOAዋሺንግተን .

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/67489

Monday, October 3, 2016

ሕዝባዊው አመጽ በአምቦ፣ በጊንጪ፣ በሸኖ፣ በመቂ፣ በባሌ ሮቤ፣ በደንቢ ዶሎ፣ በቄለም ወለጋ፣ በም ዕራብ ሸዋና በሌሎችም ከተሞች ተቀጣጠለ


 የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ትናንት በቢሾፍቱ እሬቻን በዓል ለማክበር በወጡ ንጹሃን ላይ በሂሊኮፕተር እና በመትረየስ የታጀበ የዘር ማጥፋት ከፈጸመ በኋላ በተለያዩ ከተሞች ሕዝባዊ አመጹ እንደገና ተቀጣጠለ::

 የደረሱ መረጃዎች እንደጠቆሙት በአምቦ፣ በጊንጪ፣ በሸኖ፣ በመቂ፣ በባሌ ሮቤ፣ በደንቢ ዶሎ፣ በቄለም ወለጋ፣ በም ዕራብ ሸዋና በሌሎችም ከተሞች ተቃውሞው ተቀጣጥሏል::

በተለያዩ ከተሞች በተነሱት በነዚሁ ሕዝባዊ አመጾች የመንግስት መኪኖች ሲነዱ ታይተዋል::
በአምቦ፣ በጊንጪ፣ በሸኖ፣ በመቂ፣ በባሌ ሮቤ፣ በደንቢ ዶሎ፣ በቄለም ወለጋ፣ በም ዕራብ ሸዋ ሕዝብ አደባባይ በመውጣት ተቃውሞውን እያሰማ ሲሆን በመንግስት ንብረቶች ላይ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይም ይገኛል::

በተለይ የሕወሃት ንብረት የሆነው ሰላም ባስ በሃረርጌ ጥቃት እንደተፈጸመበት የደረሰን መረጃ ያመልከታል::
በቄለ ወለጋ ጂማ ሆሮ ወረዳ ኑኑ ከተማ ከፍተኛ የሕዝብ ተቃውሞ ተቅስቅሶ ነገሮች ከቁጥጥር ውጭ እንደሆኑ ሲታወቅ በባሌ ሮቤ ደግሞ ሁሉ ነገር መዘጋጋቱ ተሰምቷል::

በደምቢ ቦሎ ኢንተርኔት በጠቅላላ መቆረጡ ሲታወቅ ተቃውሞውም እንደበረታ ምንጮች ገልጸዋል:: በአምቦም እንዲሁ ተመሳሳይ ተቃውሞዎች ዳግም እንደተቀሰቀሰ የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/66893

Sunday, October 2, 2016

ልጆቿን ያጣችው ቢሸፍቱም አለቀሰች !

* ተቃውሞን በጠመንጃ ለመግታት አይቻላችሁም
*
መግደል ይቁም !
ከረፋድ ጀምሮ የታዬ የተሰማው ሁሉ ሰቅጠጭ ግፍ ለማመን ያስቸገረኝ ግን የሆነ እውነት ነውለማመን ከቸገረኝ ካልኩት በተከታታይ ከደረሰኝ መረጃ እንዲህ የሚል ይገኝበታል ” …በዓሉ ከተጀመረበት ከጠዋት ጀምሮ የተቃዋሞ ድምጽ ነበር ፓሊስ አካባቢውን ከበበ ህዝብና ፖሊስ ገጠሙ አስለቃሽ ጭስ ወደኋላም ጥይት መተኮስ ጀመረ ህዝቡ ጭስና ጥይቱን ሲሸሽ በጥይት የተመታው ተመታ የሸሸው በግምት እስከ 10 ሜትር ድንጋያማ ገደል ውስጥ ከመውደቅ አላመለጠም …” በቦታው የነበሩ የአይን እማኝ ካካፈሉኝ መረጃ ቅንጫቢው ነው 

መንግሥት ላለፉት በርካታ አመታትና በተለይም በተከታታይ ወራት የህዝብን ድምጽ ለማፈንና ለማክሸፍ በወሰደው እርምጃ የታሰረ የቆሰለ የተሰደደውን ሳንቆጥር በሽህ የሚቆጠር የንጹሃን ዜጎች ነፍስ ተቀጥፏል ይህ ሁሉ እየሆነ ለእልቂቱ የሚሰጠው ስምየአሸባሪዎችሴራ የሚል ነው ዳሩ ግን በከባቢው እያሸበረ ያለው ጠመንጃ የታጠቀ የመንግስት ኃይል እንጅ ጣት የሚቀሰርባች አሸባሪዎች በከበቢው የሉም !

ከሁሉም የሚያሳዝነው እንዲህ እየገደሉ እስከ መቸ ሊገዙ እንደሚፈልጉ አለማወቃቸው ነው ! ከሁሉም የሚያሳዝነው የሚገድሉት ንጹህ ዜጋ ሚኒሶታ ሆኖ የተቃውሞውን መረጃ የሚያቀብለው የፖለቲካ ተንታኙ ጆሃር መሀመድ ጦር አድርጎ መገመታቸውና ማስነገራቸው ነው ከሁሉም የሚያስገርመው ከብርሃን ፍጥነት መረጃው እውነትን እያሳዬ መዋሸት መቅጠፋቸው ነው ! ከሁሉም የሚያሳዝነውየአስተዳደር በደል ፈጽመዋልእየተባለ የበደሉት ተቃወመ ብለው እያሳደዱ ያሳሰሩ የገደሉት በክበር ከስልጣን ገለል ሲደረጉ በእነሱ ጫማ እየተረገጠ የከረመው ግንባር ግንባሩን እየተባለ ሲገደል ማየት እጅግ ያማል  ጥይት ተቃውሞን አይገተውምና ዜጋው በመላ ሀገሪቱ በሚባል ሰፊ ይዞታ ተቃውሞውን እያጋጋለው መገኘቱ የሚያሳየው እውነታ በኃይል ድምጽን ማፈን አለማስቻሉን ግን ገዥዎች መማር አልቻሉም !

የንጹህ ዜጋን ዲሞክራሲያዊ የመብት ጥያቄ በጠመንጃ መመከት የመንግስትን ጭፍን አንባገነንነት ከማሳየትና ተቃውሞን ከማጎልበት ባለፈ ፋይዳ የለውም ! ዛሬ የቢሸፍቱ ተራ ሆኖ ቢሸፍቱ ልጆቿ በግፍ ተገድለው አልቅሳለች ትግሉን ግን ጭፍጨፋው እንደማያስቆመው ሳስብ በክፉ አንባገነን መሪዎቿ ሰርክ የምታነባዋ ሀገረ ኢትዮጵያ ታሰዝነኛለች እኛም ልጆችዋ እናሳዝናለን 🙁 ደሩ ግን የዚህ ሁሉ ንጹህ ደም ዋጋ የትንሳኤው ቀን ያቀርበው እንደሁ እንጅ አያርቀውም ! ፈጣሪ ሁሉንም ያያል ! ይፈርዳልም !

እጅግ በጣም ያሳዝናል ልብ ይሰብራል 🙁 በቢሸፍቱ ላለቁት ወገኖቸ የተሰማኝ ሃዘን ጥልቅ ነው የሞቱትን ነፍስ ይማር 

http://www.satenaw.com/amharic/archives/22323