Saturday, February 28, 2015

ሰበር ዜና: የወያኔ ሰላይ አለማየሁ ስንታየሁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሆላንድ ተባረረ።

ከመሃል ያለው ኢዛና (እስራኤል ገደቡ) ለ’ኢንቨስትመንት” አዲስ አበበ ያለፈው ወር በሄደ ጊዜ

ሂሩት መለሰ – ከሮተርዳም

ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል።

የሮተርዳም ከተማ ፍርድ ቤት በአለማየሁ ላይ የተመሰረተውን የስለላ ክስና ማስራጃ ለረጅም ጊዜ ሲመረምር ከቆየ በኋላ የግለሰቡ የመኖርያ ፈቃድ እና ቤት እንዲነጠቅ፣ የሆላንድን ምድርም በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ውሳኔ አስተላልፏል። ከሆላንድ የምመራ ቡድን እንደተረዳነው ከሆነ – የግለሰቡ ቤት ሲፈተሽ ወያኔ የሰጠው እውነተኛ መታወቂያ እና በርካታ የስለላ ሰነዶች ተገኝተውበታል። በእርዳታ ስም የተቋቋመለት ድርጅትም ተፈትሾ ማስረጃዎች እንደተገኙ ለማወቅ ተችሏል።
ይህ ሰው ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፎላ ይባላል። በደርግ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባል ሆኖ ለረጅም አመታት አገልግሏል። ወያኔ ስልጣን ሲቆጣጠር ለፖለቲካ ተሃድሶ አዋሳ ደቡብ ጦር ቅጥር ግቢ ተላከ። በተሃድሶ በነበረበት ጊዜ ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ የሰራዊቱ አባላትን ለወያኔ በማጋለጥ ታማኝነቱን ሲያሳይ እንደነበር የዚህ ዜና ዘጋቢ እማኝ ነው። የበርካታ ኢትዮጵያውያን ደም በእጁ ያለው አለማየሁ ከተሃድሶው ከወጣ በኋላ እስራኤል ገደቡ (የፓልቶክ ስሙ ኢዛና) ከተባለ ወታደር ጋር በመሆን የሰላም ተጓዥ ነኝ ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ሲታይ ነበር። አለማየሁ እና ኢዛና በየሃገሩ እየዞሩ ስለ አዲሱ ስርዓት መልካምነት ሲሰብኩ ከረሙ። ከዚያም አስመራ ድረስ ተልከው የሻእቢያውን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂን በወታደሩ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።

አለማየሁ እና ኢዛና ለወያኔ በሰሩት ውለታ ሆላንድ ገብተው እንዲቀሩ ተደረገ። ይህም የተደረገበት ምክንያት በአውሮፓ የሚኖሩ ኢዮጵያውያንን ተቃዋሚ በመምሰልና በረቀቀ መንገድ እንዲያበጣብጡና እንዲሰልሉ ነው።

በሆላንድ ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ ለወያኔ ቡድን የስለላ ስራ መስራት ወንጀል ነው። አለማየሁ የሆላንድ ዜግነት ቢኖረው ኖሮ ቅጣቱ የከፋ ይሆን እንደነበር ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ የህግ ባለሙያዎች ተናግረዋል።


የአለማየሁ መባረር በተሰማ ግዜ በሮተርዳም ያሉ የህወሃት ደጋፊዎች የአቤቱታ ደብዳቤ በመጻፍ ፊርማ ማሰባሰብ ቢጀምሩም ሊሳካላቸው አልቻለም። የአቤቱታ ደብዳቤው ግለሰቡ እዚህ የተወለዱ ሁለት ለጆቹን እየመጣ እንዲጎበኝ ይፈቀድለት የሚል ነበር። 


አለማየሁ ስንታየሁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሆላንድ ተባረረ። ኢዛና ግን አሁን የተቃዋሚ ጭንብሉን አውልቆ በግልጽ ወያኔ መሆኑን መናገር ጀምሯል። ኢዛና የሆላንድ ዜግነት ቢኖረውም በሆላንድ ሃገር ስራ ሰርቶ አያውቅም። የቀንና ማታ ስራው በፓልቶክ ላይ ነው። ባለፈው ወር ኢትዮጵያ የተጓዙ ዲያስፖራ ኢንቨስተሮችን እየመራ በቴሌቭዥን መግለጫ ሲሰጥ አይተነዋል። ይህ ትርኢት የወያኔ ኢንቨስተሮች በጨበጣ እንደሚንቀሳቀሱም ያሳየናል።


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39392

ከሐረር እስከ ጎዴ እንዲሁም ሃርጌሳ አፈሳው እና አፈናው ተጥውጡፏል


(ምንሊክ ሳልሳዊ) ባለፉት ቀናቶች ውስጥ ወያኔ እና የኦጋዴን አማጺ ሃይሎች ያደረጉትን ጦርነት ተከትሎ ከግድያው በተጨማሪ ከሃረር እስከ ጎዴ ያካልለ የመንገድ ላይ አፈሳ እና የቤት ለቤት አፈና እየተካሄደ እንደሆነ ከሰራዊቱ እስጥ የሚገኙት ወታደራዊ ደህንነቶች ተናግረዋል::


በልዩ ሃይል መሪነት እና በሕወሓት ጦር ተባባሪነት እየተፈጸመ ያለው አፈሳ እና አፈና የወያኔ ጦር ባልውፉት ቀናት የደረሰበትን ሽንፈት እና ኪሳራ ለማካካስ የጀመረው ሲሆን እስካሁን የቤት እመቤቶችን ጨምሮ ከ400 ሰዎች በላይ ተይዘው መታሰራቸው ሲነገር ዋና ዋና ናቸው የተባሉ የኦጋዴን አማጺ ሃይሎች አባላት ወደ መሃል አገር መላካቸው ታውቋል::በዚህም መሰረት የስለላ ስራ ያካሂዳሉ የተባሉት አጋስ መሃመድ አብደላ እና አብዱላዚዝ አብዶ ቀሽር የተባሉ የአማጺ አባላት ይገኙበታል::አፈሳው እና አፈናው በሃረር በጎዴ በቀብሪበያህ በቀብሪ ደሃር በጅጅጋ በሃርሸክ እና በሰሜን ሱማሊያ ሃርጌሳ እየተካሄደ እንደሆነ ምንጮቹ ገልጸዋል::

በአንድ በኩል እንደራደር እያለ በአንድ በኩል በውጊያ የሚጠዛጠዘው ሰው በላው ወያኔ ምን ያህል የፖለቲካ ኪሳራ እና መበስበስ እንደሚጠቁም እና የኦጋዴንን ነዋሪዎች እያፈነ እና እያሰቃየ በየትኛው የሞላር ሚዛን ድርድር ላይ እንደሚቀመጥ እና ከነማንስ ነው የሚደራደረው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ አስነስቷል::


ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በኦጋዴን አማጺ ሃይሎች እና በወየኔ ጦር መካከል በኦጋዴን ደገሃቡር አከባቢ ከፍተኛ ውጊያ መካሄዱ ሲታወቅ በሰጋጋ አከባቢ የኦጋዴን አማጺ ሃይሎች ኮማንደር ተገለዋል:: የአማጺ ሃይሎች ተዋጊዎች በአከባቢው ከሚገኘው ልዩ ሃይል ተብሎ ከሚጠራው እና በወያኔ ጦር ጋር የአከባቢው ነዋሪዎች መታፈናቸውን ተከትሎ ከሃረር ከተማ 160 ኪሎሜትር ደቡብ ምስራቅ በምትገኝ በአኪርሚሽ ላስጋሎል በተባለ ቦታ መዋጋታቸውም ይታወሳል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39373

Thursday, February 26, 2015

ለአንድ ቀን የሚቆይ የቦይኮት ዘመቻ በድምፃችን ይሰማ ጥሪ ቀረበ

‹‹እስር ከትግላችን አያስቆመንም!›› – ለአንድ ቀን የሚቆይ የቦይኮት ዘመቻ
ነገ ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከምሽቱ 12 ሰዓት ስልካችንን እናጠፋለን!
መንግስት ሙስሊሞችን ከያሉበት በማሰር ህገ ወጥ ዘመቻ ላይ መሰማራቱን እና በህዝበ ሙስሊሙ ላይ ግፍ መፈጸሙን በመቃወም ነገ ጁሙዓ ታላቅ አገር አቀፍ ተቃውሞ እንደሚኖረን እና በዛሬው እለትም የተቃውሞው መርሃ ግብር ይፋ እንደሚሆን መገለጹ ይታወሳል፡፡በዚሁ መሰረት እነሆ የነገው አገር አቀፍ ተቃውሟችን በመጠነኛ የቦይኮት ዘመቻ (የራስን መብት በራስ ላይ የመንፈግ ተቃውሞ) የሚጀመር ይሆናል፡፡ኢትዮ ቴሌኮም ለመንግስት ከፍተኛ ትርፍ ከሚያስገኙ ካምፓኒዎች አንዱ ሲሆን
በቀን ከተጠቃሚዎች በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ገቢ ያገኛል፡፡ ሙስሊሙ
ማህበረሰብ ደግሞ የአገሪቱ ግማሽ እንደመሆኑ መጠን በአንድ ቀን ለቴሌ
የሚያስገኘው ገቢ እንዲሁ በሚሊዮን የሚቆጠር ነው፡፡ በመሆኑም የማይናቅ
ቁጥር ካለው ማህበረሰብ የሚያጣው የአንድ ቀን ገቢ ለኢትዮ ቴሌኮም
በሚሊዮን የሚቆጠር ብር አክሳሪ መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ የነገው
ቦይኮት በኢቲዮ ቴሌኮም ካምፓኒ ላይ የሚያተኩረውም ለዚህ ነው፡፡
ነገ ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ ሁላችንም ስልካችንን
በመዝጋት ተቃውሟችንን እናሰማለን፡፡ አስቸኳይ ጉዳይ ካላጋጠመን በስተቀርም
ስልካችንን አንከፍትም፤ አንጠቀምምም፡፡

አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥመን ለአፍታ ስልካችንን በመክፈት ቶሎ ጉዳያችንን ፈጽመን ወዲያው እንዘጋለን፡፡
ይህንን አገር አቀፍ እና መላ አገሪቱን ያካለለ ዘመቻ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማት ለስኬቱ የቻልነውን ሁሉ መጣር ታላቅ ተግባር ሲሆን ለዲናችን ስንል ለምንከፍለው
መስዋእትነትም ከጌታችን አላህ ዘንድ ምንዳችንን እንተሳሰባለን፡፡ አላህ ፈተናውን
እንዲያነሳልንም አጥብቀን ዱዓ እናደርጋለን፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ
አይደለምና!!!


አዎን! አንድነት ያለው ህዝብ ያሸንፋል!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!



ድምጻችን ይሰማ!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39339

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዓመታዊ ዘገባ Feb 25.2015

2014 ዓም ለሰብዓዊ መብት ይዞታ እጅግ አስከፊ ዓመት እንደነበር ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ባወጣው ዘገባው አስታወቀ። በዘገባው መሠረት፣ በብዙ አፍሪቃውያት ሀገራት፣ በኢትዮጵያም ጭምር የሰብዓዊ መብቱ ይዞታ ባለፉት ዓመታት ይበልጡን እየተበላሸ መሄዱ ነው የጎላው።

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ ካለፉት በርካታ ዓመታት ወዲህ ተስፋፍቶ ቢታይም፣ በተለይ የፊታችን ግንቦት የሚደረገው ብሔራዊ ምርጫ እየተቃረበ በመጣ ቁጥር የመናገር፣ እና የመሰብሰብ የመሳሰሉ መሠረታዊ ነፃነቶችን መገደብን በተመለከተ ጥሰቱ መባባሱን በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚገኙት ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአፍሪቃ ቀንድ ተባባሪ ባልደረባ ሬይቸል ኒክልሰን ለዶይቸ ቬለ ገልጸዋል።


« ያለፈው አውሮጳዊ ዓመት 2014 በጋዜጠኞች በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እና ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ በወጡ ሰዎች ላይ የእስራቱ ድርጊት በጣም የተስፋፋበት ዓመት ነበር። ስድስት ጦማርያን እና ሶስት ጋዜጠኞች ባለፈው ሚያዝያ መታሰራቸው፣ በኋላም በፀረ ሽብር ወንጀል መከሰሳቸው እና ለፍርድ መቅረባቸው ወይም፣ መንግሥት አካሄድኩት ካለው አንድ ጥናት በኋላ በበርካታ አሳታሚ ድርጅቶች እና ሕትመቶች ላይ የሽብር ተግባር አሲራችኃል በሚል ክስ መመሥረቱ እንደ ምሳሌ ይጠቀሳል፣ ይህን ተከትሎ የአሳታሚዎቹ ድርጅቶች እንዲዘጉ በመደረጉም ለብዙ ጋዜጠኞች ሸሽተው ሀገር ለቀው እንዲወጡ ተገደዋል።

ተቃውሞ እንዳይወጡ የማከላከሉ ርምጃም ዓመቱን ሙሉ ቀጥሎዋል። እና ሀሳብን በነፃ የመግለጹ እና በፖለቲካውም ውስጥ በሙሉ በሙሉ የመሳተፉ ነፃነት ከምርጫው ቀደም ብሎ ባለው ጊዜ ውስጥ በጣም እየጠበብ መምጣቱን ታዝበናል። »

በሀገሪቱ የዘፈቀደ እስራት፣ መጠን ያለፈ የኃይል ተግባር እና ሰዎች ካለ ፍርድ የተገደሉባቸው ጥሰቶች መታየታቸው የተዘረዘረ ሲሆን፣ ለነዚሁ ጥሰቶች የፌዴራል እና ያካባቢ ፀጥታ ኃይላት ተጠያቂ መሆናቸውን ነው ከብዙ ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት ይዞታ የሚከታተሉት የአፍሪቃ ቀንድ ተባባሪ ባልደረባ ሬይቸል ኒክልሰን የኦሮሚያን አካባቢ በምሳሌነት በመጥቀስ ያመለከቱት።

« በኦሮሚያ አካባቢ ያለውን ሰፊ ጭቆናን እና አንዳንድ የመብት ጥሰትን በተመለከተ አምና ለብቻው አንድ ዘገባ አውጥተናል።ባለፈው ሚያዝያ እና ግንቦት ከአዲስ አበባና አካባቢዋ ጋር የተጣመረውን የልማት መሪ አቅድ በመቃወም በኦሮሚያ ፌደራል መስተዳድር ሰልፍ በብዛት በተካሄደበት ወቅት፣ ከፍተኛ ጥሰት ተፈጽሞዋል፣ ብሎም፣ ተቃውሞውን ለመበተን ሰዎች በብዛት ሲታሰሩ እና መጠነ ያለፈ የኃይል ተግባር ሲካሄድ ተመልክተናል። በነዚህ ጥሰቶች ላይ የፀጥታ ኃይላት ተሳታፊዎች ነበሩ። የጦር ኃይሉ እና ልዩ ኃያላትም መጠን ባለፈ የኃይል ርምጃ ተጠቅመዋል። ተቃውሞው ከቀዘቀዘም በኋላ እስካለፈው ሀምሌ ድረስ 350 እስከ 500 አባሎቹ እንደታሰሩበት ከኦሮሞ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አንዱ የሆነው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ገልጾልናል። ስለዚህ እስራቱ ዓመቱን ሙሉ ቀጥሎዋል። »

እስረኞች የቁም ስቅል እንደሚደርስባቸው የገለጸው የአምነስቲ ዘገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ወኪሎች በሌሎች ሀገራት በስደት የሚገኙ መንግሥት የሚፈልጋቸውን ስደተኞችን ካንዳንዶቹ ሀገራት በመተባበር በግዳጅ ወደ ትውልድ ሀገራቸው መመለሰቻውን በጥብቅ ነቅፎዋል። ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል 2011 ዓም ወዲህ በሀገሪቱ እንደልብ ተንቀሳቅሶ መረጃዎችን መሰብሰብ መከልከሉን በመግለጽ ድርጅቱ በውጭ ሀገር ካሉ ኢትዮጵያውያን ወይም በሀገር ውስጥ ካሉት ተባባሪዎቹ ላይ ጥገኛ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዓለም በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ከመንግሥታት እና ከታጣቂ ቡድኖች ከሚገጥማቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለመከላከል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን አላደረገም ሲል 160 ሀገራት የሰብዓዊ መብት ይዞታን የዳሰሰው ድርጅት በዘገባው ወቀሳ ሰንዝሮዋል።

አርያም ተክሌ
http://www.dw.de/%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%8A%90%E1%88%B5%E1%89%B2-%E1%8A%A2%E1%8A%95%E1%89%B0%E1%88%AD%E1%8A%93%E1%88%BD%E1%8A%93%E1%88%8D-%E1%8B%93%E1%88%98%E1%89%B3%E1%8B%8A-%E1%8B%98%E1%8C%88%E1%89%A3/a-18278968

Wednesday, February 25, 2015

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በምርጫ ቦርድ ምክንያት ሰልፉን እንዳስተላለፈ ገለጸ

Feb.25.2015

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ምርጫ ቦርድ የአባል ፓርቲዎችን ዕጩዎች ያለ አግባብ በመሰረዙና እስከዛሬ ድረስ ዕጩዎቻቸው በዝርዝር ባለማሳወቁ ምክንያት ለየካቲት 22/2007 ዓ.ም በ15 ከተሞች ሊያደርገው የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ላልተወሰነ ጊዜ ማስተላለፉን የትብብሩ ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
አቶ ግርማ በቀለ ‹‹ምርጫ ቦርድ ዕጩዎችን እመዘግብበታለሁ ባለበት የጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ዕጩዎቻችን በዝርዝር ሊያሳውቀን አልቻለም፡፡ በተለይ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ለመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ከምንም በላይ ግን በዕጩዎች ስረዛና ወከባ በርካታ ጊዜ አጥፍቶብናል፡፡›› ሲሉም ሰልፉ የተራዘመበትን ምክንያት ገልጸዋል፡፡
ምርጫ ቦርድ የትብብሩን አባል ፓርቲዎች ዕጩዎች በዝርዝር ባለማሳወቁ፣ አባል ፓርቲዎቹ ለምርጫ ቦርድ ቅሬታ እያቀረቡ በመሆኑና አሁንም ድረስ ከምርጫ ቦርድ ጋር ያሉት ችግሮች ያልተፈቱ በመሆናቸው ትብብሩ ሰልፉ የሚደረግበትን ቀን ወደፊት ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጸዋል፡፡
http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/17434#more-17434

Monday, February 23, 2015

የወያኔ ሚኒስቴር ከ30 እስከ 40% የግንባታ ወጭ እንደሚዘረፍ አሳወቁ !!

የኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና፣ ከቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑን አምነዋል።
የፀረ ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው ጥናት በባቡር መስመር ግንባታ 2.3 ኪሜ የባቡር ሃዲድ መስመር በሙስና ምክንያት ከደረጃ ውጭ እንዲሆን በመደረጉ የ124 ሚልዮን በር ኪሳራ ደርሷል። የአደጋ መከላከያ ብረቶች የተሰሩት ከወጣላቸው የጥራት ደረጃ በሶስት እጅ ያነሱ ሆነው በመገኘታቸው ጉዳዩ ለቦርድ ሰብሳቢው ዶ/ር አርከበ እቁባይ ቢቀርብም ምላሺ ሰይሰጠው በመቅረቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የት እንደገባ ማወቅ አለመቻሉን ገልጿል።
የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ምላሺ የሰጡት ሚኒስትር መኩሪያ ሃይሌ ፣ ችግሩ የተፈጠረው ለምርጫው ሲባል የባቡሩ ግንባታ እንደ ትልቅ የምርጫ ማሰመኛ በመያዙ ነው ።
የግንባታ ኢንዱስትሪው ከሚያወጣው ወጪ ከ30 እስከ 60 በመቶ የሚሆነው በሙስና ይባክናል ሲሉም ሚኒስትሩ አክለዋል። እንደዚያም ሆኖ በቅርቡ የተመረቀ የአዲስ አበባ መለስተኛ የባቡር ግንባታ፣ አገልግሎት ከመጀመሩ ከወዲሁ በርካታ የመፈራረስ ችግሮች እያጋጠሙት ነው። ለፖለቲካ ፍጆታና ለፕሮፖጋንዳ ሲባል ቶሎ ቶሎ እንዲሰራ ከማድረግ ዉጭ እነ አቶ አርከበ እቁባይ የሕዝቡን ፍላጎት ከግምት ያላስገቡ ሲሆን፣ አስፈላጊ የጥንቃቄ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በዋናነት የባቡ ሃኢዱ ከተማዋን ለሁለት የከፈለ ሲሆን ከሃዲዱ በስተቀኝ እና በስተግራ ያሉ ነዋሪዎች ለመገናኘት እጅግ  በጣም ብዙ ርቀት ለመጓዝ ተገደዋል።

http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/17401#more-17401

ሐዋሳ በእሣት ተመታች – እሣት አደጋ ነበር? ቪዲዬ ይዘናል

ህይወት ጠፍቷል፤ ንብረት ወድሟል!

February 23, 2015 09:23 am 

በሐዋሳ ለጊዜው የጉዳቱ መጠን ያልታወቀ የእሣት ቃጠሎ መድረሱን በአደጋው ያዘኑ ገለጹ፡፡ ከስፍራው እንደተሰማው ለሰኞ አጥቢያ የተነሳው ቃጠሎ ምናልባትም በከተማዋ ታሪክ ከፍተኛው ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡ አደጋው ሲደርስ የእሣት አደጋአገልግሎትበነዋሪዎች ላይ ቅሬታ አስነስቷል፡፡

ለሰኞ አጥቢያ ሌሊት ላይ ነፍሳት ባረፉበት ወቅት የደረሰው የእሣት አደጋ መነሻው በትክክል ባይታወቅም ማምለጥ የሚቻልበት ባለመሆኑ አሟሟቱ የከፋ እንዳደረገው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የተለያዩ ወገኖች በምስል ይፋ ያደረጉት ቃጠሎ እንደሚመለክተው የእሣቱ መጠን በቀላሉ የሚቆጣጠሩትና አደጋውን የሚቀንሱበት እንዳልነበረ ያስረዳል፡፡

በሐዋሳ ታሪክ ከፍተኛ ነው የተባለው ይህ ቃጠሎ በህይወት ላይ ያደረሰው አደጋ በትክክለኛው ቁጥሩ ባይገለጽም ከሥፍራው የደረሰን አጭር መልዕክት እንደሚያስረዳው ከሰባት የማያንሱ መሞታቸውን 23 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቃጠሎ ደርሶባቸው የተጎዱ እንዳሉ ሌሊት የተነሳ ቃጠሎ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብ ቢያስቸግርም ደረሰ የተባለው ሰብዓዊና ቁሳዊ ቀውስ ከዚህ የበለጠና ምናልባትም ኅሊናን የሚጎዳ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡

በዚሁ በደረሰን አጭር መልዕክት እሣቱን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የከተማዋ የእሣት አደጋ ብርጌድእውን ሐዋሳ የእሣት አደጋ ብርጌድ አላት?” የሚያሰኝ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ለመባሉ ምክንያቱ በዝርዝር አልተገለጸም፡፡ ምናልባትም አደጋው ሌሊት ላይ መከሰቱ በሰው ህይወት ላይ የተመዘገበውን አኻዝ ከሚገመተው በላይ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡


የዝግጅት ክፍላችን በደረሰው የህይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት የተሰማውን ልባዊ ሐዘን በዚህ አጋጣሚ ይገልጻል፡፡

http://www.goolgule.com/fire-broke-out-in-hawassa-city/

https://www.youtube.com/watch?v=cYWxat4rnwM


Sunday, February 22, 2015

የሕወሓት አስተዳደር በአዲስ አበባ ዙሪያ በአዳማ እና ደብረዘይት ማስተር ፕላኑን በሚቃወም ቅስቀሳ ተረብሿል

መላው ኢትዮጵያውያን ለሚደረገው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከጎናችን እንዲቆሙ ሲሉ አስተባባሪዎች ጠይቀዋል::
(ምንሊክ ሳልሳዊ) ከመሃል ሃገር ከሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች የደረሱን መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በወጣቶች ማህበር አስተባባሪነት በአዲስ አበባ ዙሪያ በናዝሬት/አዳማ እና ደብረዘይት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም እንዲሁም የወያኔው ጀሌ አባይ ጸሃዬ የሚባለው የተናገረውን ጸረ ሕዝብ አፍራሽ አነጋገር በመቃወም ከፍተኛ የሆነ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ ቅስቀሳ እየተካሄደ መሆኑ ተጠቁሟል::ይህ ቅስቀሳ ወያኔን አስጨንቆ የያዘው ሲሆን ሊያስቆመው የማይችል ከፍተኛ የሆነ ህዝባዊ አመጽ ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት አስከትሏል::

ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልሎች ላይ በተደረገ ተቃውሞ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን የተቹ የተቃወሙ እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ስለገበሬዎች መብት አቤት ያሉ ወጣቶች ተገለዋል ታስረዋል ተደብድበዋል በአፋኝ ሃይሎች ተሰውረዋል::ይህ ቁስል ሳይጠገን የሕወሓት ጀሌዎች በሃዋሳ በተደረገ ስብሰባ ላይ ባደረጉት እብሪት የተሞላ ንግግር ልክ እናስገባለን ብለው መዛታቸው በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል::ይህንን ቁጣ ተከትሎ በአዲስ አበባ ዙሪያ ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለማድረግ ህዝብን የማስተባበር ስራ እና የቅስቀሳ ስራ እየተሰራ በመሆኑ መላው ኢትዮጵያውያን ከአስተባባሪዎች ጎን እንዲቆም ጥሪዎች አስተባባሪዎቹ ጠይቀዋል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39198

Friday, February 20, 2015

በምእራብ ኢትዮጵያ ቶንጎ አካባቢ ሌሊቱን ውጊያ ሲደረግ ማደሩ ተሰማ

(ምኒልክ ሳልሳዊ) በምእራብ ኢትዮጵያ በቤንሻንጉል ክልል ደቡባዊ አቅጣጫ ቶንጎ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በታጣቂ ሃይሎች እና በወያኔ ወታደሮች መካከል ለሊቱን ከባድ ውጊያ መደረጉን ለታጣቂ ሃይሎቹ ቅርብ ነን ያሉ ምንጮች ከማላካል አስታውቀዋል::

ከደቡብ ሱዳን ማላካል ተብሎ ከሚጠራው አከባቢ ተነስተው በምእራብ የኢትዮጵያ ድንበር ከሚገኙት የወያኔ ሰራዊት ጋር ውጊያ የገጠሙት ታጣቂ ሃይሎች በስርአቱ በደል ደርሶባቸው የሸፈቱ እንደሆነ ምንጮቹ ሲገልጹ ለሊቱን ከባድ ውጊያ ያካሄዱ ሲሆን ከታጣቂ ሃይሎቹ 26 ሰውች መሰዋቱን ምንጮቹ ተናግረዋል::

በጋምቤላ እና ቤንሻንጉል ጉምዝ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በስርአቱ ከባድ በደል እየደረሰባቸው ሲሆን ምንም አይነት የልማት መዋቅር ካለመዘርጋቱም በላይ ከየአከባቢያቸው እየተፈናቀሉ መሬታቸው ለውጪ ባለሃብት እንዲሁም ከትግራይ መጥተው ለሰፈሩ አልሚዎች ለተባሉ የትግራይ ተወላጆች እየተሰጣብቸው ለስደት ለስራ አጥነት እና ለድህነት ተዳርገዋል::እነዚህ የስርአቱ በደል አንገሽግሿቸው ደቡብ ሱዳን ጫካ በመግባት ራሳቸውን ያደራጁ ታጣቂ ሃይሎች የወያኔን ወታደሮች መዋጋታቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል::


የኢትዮጵያ ሕዝቦች ለነጻነቱ እና ለመብቱ በሚያደርገው ትግል በአንድነት መነሳት አለበት አለበት ያሉት ምንጮቹ ራሳችንን ከበደል እና ከብዝበዛ ለማዳን ጠንክረን ልንታገል ይገባል ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39156