Sunday, May 31, 2015

አስቸኳይና ታላቅ የሀገር አድን ጥሪ ጉባዔ ከጁላይ 2 እስከ 3 በዋሽንግተን ዲሲ በጋራ ተዘጋጀ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ስላለው ሁለንተናዊ ቀውስ በመወያየት ሁሉን አቀፍ የአማራጭ ኃይል የሚቋቋምበትን ሂደት ለመምከር ከጁላይ 2-3 በዋሽንግተን ዲሲ የሀገር አድን ጉባዔ በጋራ ይዘጋጃል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄና
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ኅብረት ጋር በተደረጉ ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶችና
ስምምነቶች፡ ህዝባችን ላለፉት 24 ዓመታት ያለነፃነት በህወሓት የግፍ አገዛዝ ሥር ፍዳውን የሚያይበት ዋና ምክንያት፤
ሕዝብን መሠረት ያደረገና ብሄራዊ ጥቅምን ያስቀደመ፤ በአንድ ማዕከል የሚንቀሳቀስ ሁሉን አቀፍ የአማራጭ አካል
በማቋቋም ሥርዓቱን ለማስወገድ አስፈላጊውን ትግል የማድረግ ቁርጠኝነቱ በተቃዋሚው ጎራ ያለመኖሩ ዋና ጉዳይ
መሆኑን የጋራ ግንዛቤ ላይ ደርሰናል። ይህን አዙሪት በመስበርና ሁኔታዎችን በጋራ በማመቻቸት የአማራጭ ኃይሉ
በአስቸኳይ እንዲቋቋም ስምምነት ላይ መድረሳችንንም በተከታታይ ባወጣናቸው የሁለትዮሽ መግለጫዎች ይፋ
መሆናቸው የሚታወስ ነው።

ሥርዓቱ ባሳለፍነው ሳምንት ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል አስቀድሞ የታወቀውን የህወሓት/ኢህአዴግ የምርጫ
ድራማ በማካሄድ፤ ሕዝብን ተስፋ በማስቆረጥና ግፉን አሜን ብሎ በመቀበል፤ ቀደም ሲል ሲያደረግ የነበረውን ሀገር
የማፈራረስ ሂደትና የሕዝብን ስቃይ የሚያበዛ አገር በቀል የአፓርታይድ አገዛዝ ለቀጣይ አምስት አመታት ለማስቀጠል
የሚያስችለውን ህጋዊ ሽፋን በማመቻቸት ላይ በሚገኝበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፤ አገር አድን የምክክር ጉባዔ በማድረግ
በሕዝብ ተቀባይነትና ታማኝነት ያለው ሁሉን አቀፍ የአማራጭ ኃይል በማቋቋም ትግሉን በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠል
ወቅታዊና አስቸኳይ ነው።

ከላይ በመግቢያው ላይ የተዘረዘሩት ድርጅቶች፤ ከተለያዩ አክቲቪስቶችና ታወቂ ግለሰቦች ጋር በመሆን ከጁላይ 2-3
የምክከር ጉባዔ በጋራ ያዘጋጃሉ። የጉባዔውን ውጤት ለማሳወቅ ሕዝባዊ ስብሰባም ይዘጋጃል። የመሰብሰቢያ ቦታ፤
ዝርዝር ፕሮግራሞችና ተያያዥ እንቅስቃሴዎችን በተከታታይ እንደምናሳወቅ ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን።

ስለዚህ፤ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የፓለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ መኅበራት፣ የነገ ሀገር ተረካቢ የሆናችሁ ወጣቶች፤
በሀገራችን ነፃነት ሠላም እኩልነትና ፍትኅ ይሰፍን ዘንድ የምትተጉ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ አዘጋጆች፣ የፓልቶክ ክፍሎች፣
ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የእምነት አባቶች፤ እንዲሁም ለሀገር ደህንነት ተቆርቋሪ
የሆናችሁ ዜጐች በሙሉ፤ የሚገነባው የተባበረ አማራጭ ኃይል ባለቤት እንደመሆናችሁ መጠን የሂደቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ
በመሆን፤ በሀገራችን ነፃነት እውን እንዲሆን በሚደረገው ወሳኝ ሕዝባዊ ትግል ውስጥ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ ታበረክቱ
ዘንድ፤ እንዲሁም በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርጉ አደራ እያልን በአክብሮት ሀገራዊ ጥሪያችንን
እናቀርባለን።

ይህ አደገኛ የቁልቁለት ጉዞ እንዲገታ በጋራ እንቁም!
የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (SHENGO)
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት (ENTC)
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ህብረት (UEM-PMSG)
የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ (EYNM)
ግንቦት 22፤ 2007 (May 30, 2015)

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41838

Thursday, May 28, 2015

ፍ/ቤቱ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ የቀረቡ የሲ.ዲ መረጃዎችን ውድቅ አደረገ

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሶስቱ ጋዜጠኞች ዛሬ ግንቦት 19/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ መዝገቡ የተቀጠረው አቃቤ ህግ አሉኝ ባላቸው ሲ.ዲዎች እና ቀሪ ምስክሮቹን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ብይን ለመስጠት ነበር፡፡

በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ ቀሪ ምስክሮቹን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ ምስክሮቹን ለማቅረብ ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ የሰጠውን እድል ባለመጠቀሙ እና ምስክሮቹን ላለማቅረቡ የሰጠው ምክንያትም በቂ ባለመሆኑ አቃቤ ህግ ያቀረበውን የተጨማሪ ጊዜ ባለመፍቀድ ከዚህ በኋላ ምስክሮቹን እንደማይሰማ አመልክቷል፡፡


አቃቤ ህግ በኤግዚቢትነት ይዟቸው የቆያቸውን የ12ቱን ሲ.ዲዎች ጉዳይ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ሲ.ዲዎቹ በማስረጃ ዝርዝሩ ውስጥ ፕሪንት ተደርገው የተያያዙ ሰነዶችን እንደያዙ ስለተገለጸ ሲ.ዲዎቹ ከማስረጃነትም ሆነ ከኤግዚቢትነት ውድቅ መደረጋቸውን ገልጹዋል፡፡


አቃቤ ህግ በአንደኛ ተከሳሽ
 ላይ የሲ.ዲ ዶክሜንተሪ ማስረጃ ማቅረቡን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ እንዲመለከትለት የጠየቀ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ከሰዓት በኋላ አቃቤ ህግ ሲ.ዲውን በጽ/ቤት በኩል እንዲያስገባ በማዘዝ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበውን ዶክሜንተሪ በቢሮ ዳኞቹና ጠበቆቹ እንዲመለከቱት ከተደረገ በኋላ ሲ.ዲው ሌሎችን ተከሳሾች ይመለከታል ወይስ አይመለከትም የሚለውን አይቶ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 8/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በሌላ በኩል ተከሳሾች ጥያቄያቸውን ለፍርድ ቤቱ ለማስረዳት በሞከሩበት ጊዜ ፍርድ ቤቱ የመናገር እድል ሲነፈጉ የተስተዋለ ሲሆን፣ ተከሳሾቹ ፍርድ ቤቱ እንዲፈቅድላቸው ሲጠይቁ ‹‹ስነ-ስርዓት አድርጉ!›› ባለ ጊዜ ጦማሪ አቤል ዋበላ ‹‹እናንተ ራሳችሁ ስነ-ስርዓት አድርጉ….እንናገርበት! ይህ የመብት ጉዳይ ነው…በግልጽ ችሎት ላይ ህገ መንግስታዊ መብታችንን አክብሩ እንጂ…ጥያቄ አለን ተቀበሉን›› ሲል በመናገሩ ችሎት ደፍረሃል ተብሏል፡፡ በዚህም ፍርድ ቤቱ በአቤል ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለግንቦት 25/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41782

ምርጫ ቦርድ የአስቂኙን ምርጫ ውጤት ይፋ አደረገ * ኢሕአዴግ 100% አሸነፈ አለ * ምንም አይነት ተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ወንበር አላገኘም

ኢህአዴግ እና አጋር ድርጅቶቹ የዘንድሮውን አሳፋሪ ምርጫ 100% ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ገለጸ:: ምንም አይነት ተቃዋሚ ፓርቲ በፓርላማው ውስጥ መቀመጫ እንዳላገኘም ተገልጹዋል::
የገዢው ፓርቲ መሳሪያና ገለልተኛ ያልሆነው ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ኢህአዴግ አዲስ አበባ ላይ ከ23 መቀመጫዎች ኢህአዴግ 23ቱንም መቀመጫዎች አግኝቷል።

– ከትግራይ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ31 መቀመጫዎች ውጤት ህውሃት/ኢህአዴግ 31 መቀመጫዎችን
– ከአማራ ክልል ከደረሱት የ107 መቀመጫዎች ውጤት ብአዴን/ኢህአዴግ 107 መቀመጫዎች
ከኦሮሚያ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ150 መቀመጫዎች ውጤት ኦህዴድ/ኢህአዴግ 150 መቀመጫዎችን
– በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ16 መቀመጫዎች ውጤት ኢሶዴፓ 16 መቀመጫዎችን
– ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከደረሱት የሰባት መቀመጫዎች ውጤት ሰባቱንም ቤጉዴፓ;
– ከደቡብ ክልል ከደረሱት የ95 መቀመጫዎች ውጤት ዴኢህዴን/ኢህአዴግ 95 መቀመጫዎች፣
– በጋምቤላ ክልል ጋህዴፓ ከሶስት መቀመጫዎች ሶስቱንም፣ በሀረሪ ክልል ሀብሊ ከ2 መቀመጫዎች አንዱን ሲያገኝ አንዱን ኦህዴድ/ኢህአዴግ፣
– በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከሁለቱ መቀመጫዎች አንዱን ኦህዴድ/ኢህአዴግ ቀሪውን ሶህዴፓ አግኝተዋል
– ከአፋር ክልል ከደረሰው ከደረሰው የስድስት መቀመጫዎች ውጤት አብዴፓ ስድስቱንም መቀመጫ አግኝቷል።


በአሳፋሪነቱ የሚጠቀሰው የዘንድሮውን ምርጫ የአውሮፓ ሕብረት; የአሜሪካ መንግስትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ፍትሃዊ ያልሆነ ምርጫ ሲሉ አውግዘውታ:: ተቃዋሚዎችም የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41775

Wednesday, May 27, 2015

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙርና ከትግሉ ጐራ እንቀላቀል !


ምርጫ 2007 ተጠናቆ ተወዳዳሪም አወዳዳሪም የሆነው ህወሓት ይፋ ውጤት እስኪገልጽ እየተጠበቀ ነው። ሁሉ በእጁ ነውና ባለሥልጣኖቹ ምን ዓይነት ውጤት እንደሚስማማቸው እስከሚነግሩን ጥቂት ቀናት ይወስዱ ይሆናል። ከፈለጉ ሁሉን የፓርላማ ወንበሮች ሊወስዷቸው ይችላሉ፤ ካሻቸው ደግሞ ጥቂቱን ለተቃዋሚዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። በዚህ የፓርላማ ወንበሮች እደላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ አንዳችንም ሚና የለውም።

ምርጫ የሕዝብ የሥልጣን ባላቤትነት ማረጋገጫ ከሆኑ አቢይ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት አንዱ መሆኑ የታወቀ ነው። ሆኖም ግን ነፃ ተቋማት በሌሉበት፤ በአምባገነኖች አስፈፃሚነት የሚደረግ ምርጫ የመራጮች ነፃ ፍላጎት መግለጫ በመሆን ፋንታ የገዢዎች ሥልጣን ማረጋገጫ መሣሪያ ይሆናል፤ ከአገራችን እየሆነ ያለውም ይህ ነው።

የዘንድሮው ምርጫ 2007 ከዚህ በፊት ከነበሩ በባሰ ለአፈና የተጋለጠ የነበረ መሆኑ ከጅምሩ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነበር። በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ አገዛዙ የወሰደው የግፍ እርምጃ የዚሁ የምርጫ ዘረፋ ስትራቴጂ አካል ነበር። ከዚያ በተጨማሪም መራጮች እውነተኛ ፍላጎታቸውን በነፃነት መግለጽ እንይችሉ ዘርፈ ብዙ ጫናዎች ሲደረግባቸው ቆይቷል። የተወዳዳሪ ፓርቲዎች አባላት እንደተፎካካሪ ሳይሆን እንደጠላት ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡና ሲገደሉ ሰንብቷል። በምርጫው ሰሞንና በዕለቱ በተለይ ከተሞች በባዕድ ጦር የተወረሩ መስለው ነበር። ይህ ሁሉ ስነልቦናዊና አካላዊ ተጽዕኖ ታልፎ የተሰጠው ድምጽ ቆጣሪው ራሱ “ተወዳዳሪ ነኝ” ባዩ ህወሓት ነው።

በእንዲህ ዓይነት ምርጫ መሳተፍ ትርፉ “በሕዝብ ድምጽ ተመረጥኩ የማለትን እድል ለአምባገኑ ህወሓት መስጠት ነው”፤ “ለዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብም የተምታታ መልዕክት ማስተላለፍ ነው”፤ ”ለህወሓት ተጨማሪ ገንዘብ ማግኛና የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራ ማራዘሚያ ነው“ በሚል በዚህ ምርጫ ላይ ማዕቀብ እንዲደረግ አርበኞች ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በርካታ ወገኖቻችን የምርጫ ካርድ ቢያወጡም የደረሰባቸውን ጫና ተቋቁመው በምርጫው ባለመሳተፍ ላሳዩት ጽናት አርበኞች ግንቦት 7 አድናቆቱን ይገልፃል።

ህወሓት በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ የምርጫ ጉዳይ እና የምርጫ ፓለቲካ ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳን ተጨማሪ ማስረጃ ለሚፈልጉ ግንቦት 16 ቀን 2007 መጥቶላቸዋል። አሁን ከፊታችን የተደቀነው ጥያቄ የሚከተለው ነው – አገራችን ከህወሓት አፈና ነፃ ለማውጣት ያለን አማራጭ መንገድ ምንድነው

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህወሓት ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ የሚወርደው ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽን ባቀናጀ ሁሉገብ ትግል ነው ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ለሁለቱም የትግል ዘርፎች ተስማሚ የሆኑ አደረጃጀቶችን አዘጋጅቷል።

ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ታጋዩ ከመኖርያ ወይም ከሥራ ቦታው ሳይለቅ በህቡዕ የሚከናወን ትግል ነው። ሕዝባዊ አመጽ ደግሞ ከመኖሪያና ሥራ ቦታ ለቆ መንቀሳቀስን ይጠይቃል። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች የህወሓትን ህጎች በመቃወም የሚደረጉ ናቸው። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች ድርጅት፣ ዲሲሊንና ጽናትን ይጠይቃሉ። ለድላችን ሁለቱም የትግል ዘርፎች እኩል ዋጋ አላቸው። እናም ከዛሬ ጀምሮ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደዝንባለውና አቅሙ በሚመቸው የትግል ዘርፍ ይሳተፍ። ሕዝባዊ ኃይልን መቀላቀል የቻለ ይቀላቀል፤ ያልቻለው በያለበት ተደራጅቶ በሕዝባዊ እምቢተኝነት ይታገል።

በየመኖሪያ ሠፈሩና በሥራ ቦታዎች የሚቋቋሙ የአርበኞች ግንቦት 7 ማኅበራት በርካታ ሥራዎች አሏቸው። ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅትን ማጠናከር የሁላችንም ድርሻ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም፤ እናም ትኩረታችን እዚያ ላይ እናድርግ። እያንዳንዳችን ከሚመስሉንና ከምናምናቸው ጋር ተነጋግረን እንደራጅ፤ ወያኔ የሸረሸረብንን በራስ መተማመን እና የእርስ በርስ መተማመንን መልሰን እንገንባ። ውስጥ ውስጡን ጠንካራ አገራዊ ኅብረት እንፍጠር፤ የዕለት ተዕለት ተግባሮቻችን ደግሞ አካባቢያዊ ይሁኑ። 

ድርጅታችንን እያጠናከርን ወያኔን ከሁሉም አቅጣጫ እንሸርሽረው እንገዝግዘው። በዚህ መንገድ በሚደረግ ሕዝባዊ ትግል የሚገኝ ድል ፈጣን ከመሆኑን በላይ የድሉ ሕዝባዊነት ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ይሆናል።

ስለሆነም እያንዳንዱ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ታጥቆ እንዲነሳ፤ ወደ ተግባራዊ ትግል ፊቱን እንዲያዞር አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያቀርባል።


ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41754


Tuesday, May 26, 2015

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን የተሰጠ መግለጫ – “በምርጫ ተሸንፎ በስልጣን መቆየት አያዋጣም”


በ 2007 ብሄራዊ ሀገር አቀፍ ምርጫ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከምርጫው ቅስቀሳ ጊዜ ጀምሮ ያለው ሁኔታ ነፃና ፍትሃዊ አለመሆኑን ባወጡት ሪፖርት አረጋግጠዋል::ወያኔ በምርጫው ቅስቀሳ ሂደት ድብደባ፣ አፈና ፣እስራት ፣ግድያ እና እንግልት በግልጽ ፈጽሟል:: (በምዕራብ ሸዋ ዞን ሚዳቀኝ እና በአርሲ ኮፈሌ የተፈጸመው ግድያ ፤ በእነ በቀለ ገርባ ላይ በበደሌ፣ ጅማ እና በነቀምቴ የተፈጸመውን ድብደባ ልብ ይሏል)::

ተቃዋሚዎች ወያኔ ኢሕአዴግን በምርጫ ክርክር አዋረዷት:: ህዝቡ ለመድረክ የሰጠው ድጋፍ ስላስደነገጠው ሃይልን በመጠቀም ጫና ቢያደርግም አልተሳካላትም:: ተስፋ ስቆርጡ ለምርጫው ሁለት ቀናት ሲቀሩት ጠ/ሚኒስትሩ ፓርላማው በማይጠራበት ወቅት ስብሰባ በመጥራት ማስፈራሪያ እና ዛቻ በተቃዋሚዎች ላይ ሰንዝረዋል:: ይህም አስቀድሞ የምርጫውን ውጤት ለመቀልበስ በሃይል ምርጫውን ለማጭበርበር ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ እንደነበር የሚያስይ ነበር :: የኢሕዴግ ካድሬዎች የምርጫው ዋዜማ ሌሊት ከአለቆቻቸው የተላለፈውን ትእዛዝ ለመፈጸም አስቀድመው ኮሮጆ በመሙላት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የፌዴራል ፖሊስ: ሚሊሺያዎች: ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እና አድማ በታኝ ፖሊሶችን በማዝመት የምርጫ ቦርድ ተወካዮችን እና የተቃዋሚ (የመድረክ) የምርጫ ታዛቢዎችን መታወቂያቸውን በመቀማት እያስፈራሩ እየደበደቡ በርካቶችን (90%) ሙሉበሙሉ ማለት ይቻላል ከምርጫ ጣቢያ በሀይል አባረዋል።በርካታ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የምርጫ ካርድ ተከልክለዋል። የመምረጥ መብታቸዉን ተነፍገዋል።

ስለሆነም: ፀረ ሠላም እና ፀረ ዴሞክራሲ የዘረፋ ቡድን የፈጸመው ምርጫን ማጭበርበር ፣ የህዝብ ድምፅ መዝረፍ፣ ንጹሃን ዜጎችን መግደል እና የማሰር ድርጊት አጥብቀን እያወገዝን የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ይህን መግለጫ አውጥቷል።

1. ኦፌኮ/ መድረክ በኦሮሚያ ክልል ምርጫዉን ሙሉ ለሙሉ አሸንፏል።

2. የተፈፀመው ድርጊት በማንኛውም አለም አቀፍ የምርጫ መስፈርት ተቀባይነት የሌለው እና ህገ ወጥ መሆኑን እንገልጻለን:: በጽኑ እናወግዛለን::


3. ይህንን የህዝብ ድምፅ ዝርፊያ እና የምርጫ ማጭበርበር ተከትሎ ለሚነሳው የህዝብ ተቃውሞም ሆነ መንግሥት ለወሰደው እና ለሚወስደው እርምጃ ተጠያቂው እራሱ ኢሓዴግ ነው።


4. የህዝቦች ህገመንግስታዊ መብቶች በተጣሰበት፣ በማፈንና በማስፈራራት ምርጫ አስፈፃሚዎች እና የምርጫ ታዛቢዎች ተባረው ምርጫ ተካሂዷል ለማለት አንችልም።


5. ህዝባችን የመረጠው ድርጅት ኦ.ፌ.ኮ /መድረክ/ የሚያደርገውን ቀጣይ የትግል ጥሪ ዝግጁ በመሆን እንዲጠብቁ እናሳስባለን ።


6. የወያኔን አፋኝ ስርአት እድሜ ለማሳጠር በትግል ላይ የምትገኙ ሃይሎች: ወያኔ ይህን ያህል ረጅም ዓመታት በስልጣን ላይ ሊቆይ የቻለው በራሱ ድርጅታዊ ጥንካሬ ሳይሆን የተቃዋሚ ሃይሎች ትግሉን በተቀናጀ ሁኔታ ያለመምራት በመሆኑ በቀጣይ ለሚደረገው ትግል የፖለቲካውን ክፍተት በመዝጋት ትግሉን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ለማሸጋገር በመተባበር እና ልዩነቶችን በማጥበብ እንድንታገል ጥሪ እናቀርባለን።


ትግሉ ይቀጥላል !!!!!!!!


የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41724

Sunday, May 24, 2015

ኢትዮጵያ – የምርጫ ቀጣና ሳይሆን የጦርነት ቀጠና እየመሰለች ነው


የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዉጥ ይፈልጋል። የዘንድሮው ምርጫ እንደ መሳሪያ በመጠቀም፣ ለዚህ ግፈኛ መንግስት ተቃዉሞዉን ይገልጻል ተብሎ ይጠበቃል። ህወሃት/ኢህአዴግ ህዝብ እንደተፋው ያውቃል። ከዚህም የተነሳ በብዙ ቦታዎች ፣ የምርጫ ጣቢያዎች ሁሉ ተዘግተዋል። እንደ አዲስ አበባ፣ ባህር ዳር ያሉ ከተሞች የጦርነት ቀጠናዎች ይምስሉ። ቁጥሩ እጅግ በጣም ብዙ የሆነው የታጠቃ ኃይል ተሰማርቷል። ቁጥራቸው እጅግ በጣም ብዙ የሆነ ኢትዮጵያዉይን እየታፈሱ ነው።


በአገር ቤት ያለው ሁኔታ እንዲህ እንዳለ ህወሃት/ኢሕአዴግ ከፍተኛ የአለም አቀፍ ተቃዉሞ ገጥሞታል። በርካታ የዉጭ ጋዜጦች ምርጫው የዉሸት እንደሆነ እየዘገቡ ነው። የአቶ ኃይለማሪያም የአልጃዚራም ቃል ምልልስ በአገዛዙ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ዉርደትን አከናንቧል። አቶ ኃይይለማሪያ የአንድ አገር መሪ ሳይሆኑ ሃሺሻ ሳያገኝ ሲቀር የሻሺሽ ሱሰኛ እንደሚሆው ፣ የሚቀጠቀጡ ዱርዬ ነበር የሚመስሉት

ሕወሃት/ኢሕአዴግ በራዲዮና ቲቪ በመዛት፣ የወታደር ብዛት በማከማቸት፣ ታንኮች በማሰማራት በ1997 እንዳደርገው የሕዝቡን ጥያቄ አፈቤ እገዛለሁ የሚል እምነት ይኖረዋል። ሆኖም 2007 እንደ 1997 አይደለም።

ይሄ በአገዛዙ ላይ የደረሰው ዉጥረትና ውርደት ፣ የሕዝብ ትግል ያመጣው ነው። ይሄ የሕዝብ የትግል መነሳሳት ደግሞ በአገራችን የነጻነት ጮራ የሚፈነጥቅበት ጊዜ ቅርብ መሆኑ የሚያሳይ ነው። በርግጥም የሕዝብ ጉልበት ያሸንፋለ። እነርሱ ጥቂቶች ናቸው። እነርሱ እስከ አሁንም የኖሩት እየከፋፈሉ ነው። እኛ ግን ሚሊዮኖች ነን። እኛ ግን ዘር፣ ኃይይማኖት ሳንለይ አንድ ሆነናል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41633

Saturday, May 23, 2015

ዞን9 ጦማርያን በብሎገርነት ሽፋን ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር አንደሚሰሩ እርግጠኞች ነን ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም በአልጀዚራ ቴሌቭዥን


ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ምርጫውን አስመልክቶ ከአልጀዚራ ቴሌቭዥን ጋር ቆይታ ባደረጉበት ወቅት በተደጋጋሚ ስለዞን9 ጦማርያን አና ሶስቱ ጋዜጠኞች ተጠይቀው በጥቅሉ የሚከተሉትን ምላሾች ሰጥተዋል፡፡

1. ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር አንደሚሰሩ እርግጠኞች ነን ብሎገርነት ስም ሽፋን ነው
 ፡፡

2. ፓርላማ በሽብር ከመደባቸው ድርጅቶች ጋር እንደሚሰሩ ማስረጃ አለኝ የድርጅቱን ስም ግን አሁን አልናገርም ምክንያቱም የፍትህ ሂደቱ ላይ ተጽእኖ ላመጣ እችላለሁ
 ፡፡

3. ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር ላለመስራታቸው (ለፍርድ ቤቱ) ማስረዳት አለባቸው
 ፡፡

4. አንድ ዓመት እስር ለሽብር ህግ ምንም ማለት አይደለም
 ፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር አስመልክቶ ከዚህ በፊት በእስር ላይ ከሚገኙት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ግልጽ ደብዳቤ የጻፍን ቢሆንም ጠቅላይ ሚንስትሩ በዛሬውን ንግግራቸው የተለመደውን የአመክንዮ፣ የሃቅ እና የህግ ስህተቶች ፈጽመዋል ፡፡

1. የዞን9 ጦማርያን የሽብርተኛ ድርጅት አባል ለመሆናቸው የቀረበባቸው ምንም የአባልነት ማስረጃ የለም ፡፡ ፍርድ ቤት ላይ የቀረቡ ማስረጃዎችም ይህንን አያስረዱም ፡፡

2. በፍርድ ቤት የተከሰስነው የግንቦት ሰባት እና የኦነግ አባልነት መሆኑ በግልጽ ተቀምጦ ሳለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሚስጥር ማስመሰላቸው ጉዳዩ ላይ እውቀት አንደሌላቸው ያስረዳል፡፡


3. በመሰረታዊ የህግ መርሆ መሰረት ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር አለመስራታችንን ማስረዳት ሳይሆን መንግስት በአቃቤህግ በኩል ወንጀል መስራታችንን ነው ማስረዳት ያለበት ፡፡ የማስረዳት ሸክሙን እኛ ላይ በመጣል መሰረታዊ የህግ ጥሰት ከመፈጸማቸውም ውጪ መንግሰታቸው የሚሰራበትን “ሁሉም ሰው ወንጀለኛ ነው ወንጀለኛ አለመሆኑን ማስረዳት አለበት” የሚል ትችት የሚሰነዝሩ ዜጎችን አንደወንጀለኛ የማየት አቅጣጫ ፍንትው አድርጎ ያሳያል ፡፡ በዚህም ወጣት የህግ ባለሞያዎች እንዳሉበት ስብስብ አፍረናል፡፡


4. መሰረታዊ የሆነው አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብት በተራዘመ ምርመራ እና የፍርድ ቤት ቀጠሮ መጉላላት መጣሱ መንግስትን አንደማያሳስበው ማየታችን አሁንም አሳፍሮናል፡፡ አገራችን በፈረመቻቸው አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎች መሰረት አፋጣኝ ፍትህ ማግኘት የዜጎች መብት ሲሆን የመንግሰት ከፍተና አመራረር ያለምንም ማፈር የመብት ጥሰቱን መከላከላቸው አስገራሚ ነው ፡፡


በመሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ ሌሎች ከፍተኛ የመንግሰት ባለስልጣናት ያልተፈረደባቸውን ተከሳሾች ሽብርተኛ በማለት መፈረጃቸው አንዲያቆሙ ፣ መሰረታዊ የወንጀል ህጎቸን አንዲያከብሩና አንዲያስከብሩ ልናሳስብ አንወዳለን፡፡
የዞን9 ጦማርያንም ሆነ ወዳጅ ጋዜጠኞች በምንም አይነት ወንጀል ተሳትፈው የማያውቁ ሲሆን ክሳቸውም ፓለቲካዊ ነው ፡፡ ተከሳሾቹን በነጻ ማሰናበት ለመንግሰት በጣም ቀላሉ ችግሩን የመፍቻ መንገድ ነው ፡፡


ስለሚያገባን እንጦምራለን!

ዞን 9


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41602

Friday, May 22, 2015

ማይጨውም ተወጥራለች..! – አምዶም ገብረስላሴ

የህወሓት ጭንቀት በገጠርም በከተማም በከፍተኛ ደረጃ ደርሰዋል። ማይጨው ከተማም እንደሌሎች የትግራይ ኣከባቢዎች በክፍተኛ ውጥረት ትገኛለች።

በማይጨው ከተማ ያለው ውጥረት በማይጨው ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተማሪዎችና በኮሌጁ ኣስተዳደር፣ በተማሪዎችና የከተማው ካድሬዎች፣ በካድሬዎችና በኑዋሪ ህዝብ መካከል ነው።

የውጥረቱ መነሻ “..ዓረና-መድረክ በከተማው ያለው ተቀባይነት ህወሓት ሊያሽንፋት ይችላል..” የሚል ድምዳሜ በዞኑና በከተማዋ ኣስተዳዳሪዎች ድምዳሜ ስላስደረሳቸው ነው። በማይጨው ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተፈጠረው ውጥረት የህወሓት ካድሬዎች ከኮሌጁ ኣስተዳዳሪዎች በመሆን ተማሪዎቹ ኣንድ በኣብድ ወደ ኦፊስ በመጥራት ከዓረና-መድረክ ኣባልነት ውጣ…!፣ ከዓረናዎች ጋር ግንኙነት ኣለህ…!፣ ኣቋምህ ግልፅ ኣይደለም..!” የሚሉ ጥያቄዎ በማቅረብ “..ግለ ሂስ ኣድርገህ፣ ይቅርታ ጠይቀህ በሰላም መኖር ትችላለህ። ኣለበለዚያ ግን እኛ በስንት መስዋእትነት ያመጣነው ስልጣን በወረቀት የሚቀየር እንዳይመስልህ፣ ከምርጫ በሗላ በዚች ኣገር በሰላም የምትኖር እንዳይመስልህ..” እየተባለ ሲያስፈራሩት ውለዋል።

ይህ ተግባር የሚፈፅሙ ሰዎች የማይጨው ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን መምህር ግርማይ ሓጎስ፣ ምክትል ዲን መምህር ዓፈራ ሲሆኑ ከካድሬዎች ደግሞ ሃፍቱ ጫሪ፣ መምህር ሚኪኤለ ኣበበና የማይጨው ከተማ ፕሮፖጋንዳ ሃላፊ ኣቶ ተሻለ ባይሩ ናቸው። የዚህ ውጤት ደግሞ “..እኛ የፈለግነው ፓርቲ ኣባል የመሆን፣ የመደገፍና የመምረጥ መብት ኣለን። የፈለጋቹ እርምጃ ልትወስዱ ትችላላቹ፣ እኛ ደግሞ በእምነታችን መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁዎች ነን..” በማለት ኣንጀታቸው ኣሳርረው መልሶኣቸዋል።

በማይጨው ህዝብና ካድሬዎችም ተመሳሳይ ውጥረት ነግሶ ይገኛል። ካድሬዎች የህወሓት ድጋፍ ሰልፍ እንዲወጣ ህዝቡ ቀጭን ትእዛዝ በማስተላለፍ ሳይወድ በግድ እንዲወጣ ቢያደርጉትም ህዝቡ እየቀለደባቸውና እየተሳለቀባቸው ኣርፍደዋል። በሌላ ኣጋጣሚ ደግሞ የምርጫ ወረቀት ይዘው የተገኙ የቀበሌ ሴቶች የዓረና-መድረክ ኣባላት በማጋለጣቸው ምርጫ ቦርድም ወረቀቱ ኬት እንዳመጡት ቢጠይቋቸውም የከተማዋ ከንቲባ ኣቶ ተስፋይ ኪዳኑ በኣካል ተገኝቶ ነገሩ እንዲደፋፈን ኣድርጎታል።

ህወሓትየማይጨው ወጣቶች፣ የፖሊ ቴክኒክ ተማሪዎችና ኑዋሪ ህዝብ የህወሓት ራስ ምታት ሁኖበታል። ኣዎ..! ህዝብ የፈለገው ለውጥ ከማድረግ ማንኛውም ሃይል ኣይገታውም።

ነፃነታችን በእጃችን ነው..!

http://satenaw.com/amharic/archives/7124

Wednesday, May 20, 2015

በእነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ላይ የተመሰረተው ክስ ተሰማ * ‘ኤርትራን ተሻግራችሁ ግንቦት 7ን ልትቀላቀሉ ነበር’ ተብለው ተከሰዋል

‹‹በይልቃል ጌትነት እና በዮናታን ተስፋዬ ላይ መስክር እያሉ ያሰቃዩኛል›› ብርሃኑ ተ/ያሬድ
የፌደራል አቃቤ ህግ በቀን ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም በእነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ላይ የመሰረተው ክስ ከሦስት ሳምንታት በኋላ ዛሬ ግንቦት 12/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በንባብ ተሰምቷል፡፡


በብርሃኑ ተ/ያሬድ ስም በተከፈተው የክስ መዝገብ ላይ አራት ሰዎች የተካተቱ ሲሆን፣ እነዚህም 1ኛ ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ 2ኛ እየሩሳሌም ተስፋው፣ 3ኛ ፍቅረማርያም አስማማው እና 4ኛ ደሴ ካህሳይ ናቸው፡፡ የሽብር ክስ የቀረበባቸው እነዚህ ተከሳሾች በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ (አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና የጸረ ሽብር አዋጁ አንቀጽ 7(1)ን በመተላለፍ ወንጀል እንደተከሰሱ የክስ ቻርጁ ያመለክታል፡፡


በክሱ ላይ እንደተመለከተው ተከሳሾች ኤርትራ ውስጥ መቀመጫውን ባደረገውና በሽብርተኝነት በተፈረጀው ግንቦት ሰባት ስር አባል ሆነው የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ወስነው ከድርጅቱ ጋር ለመቀላቀል የኢትዮጵያንና የኤርትራን ድንበር አቋርጠው ሊሻገሩ ሲሉ በቁጥጥር ስር የዋሉ በመሆናቸው በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በአባልነት መሳተፍ ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

ተከሳሾቹ ክሱን ካዳመጡ በኋላ ጠበቃ ማቆምን በተመለከተ ከፍርድ ቤቱ ለተነሳላቸው ጥያቄ ሁሉም ተከሳሾች፣ ‹‹ከተያዝን ጊዜ ጀምሮ በደል እየደረሰብን ነው፤ ይህ የብቀላ ስራ ነው ብለን ስለምናምን እና በዚህ ሁኔታ ተከራክረን ፍትህ እናገኛለን ብለን ስለማናምን የግልም ሆነ የመንግስት ጠበቃ አንፈልግም›› ብለዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ጠበቃ አለማቆም መብታቸው እንደሆነ በማውሳት ሀሳባቸውን የሚቀይሩ ከሆነ ጥያቄያቸውን ለመቀበል ዝግጁ ነው ሲል ገልጾዋል፡፡

በሌላ በኩል አንደኛ ተከሳሽ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ለፍርድ ቤቱ ባሰማው አቤቱታ እንደገለጸው አሁን በሚገኝበት ቂሊንጦ ማቆያ ውስጥ በደል እየደረሰበት ይገኛል፡፡ ‹‹የተከሰስኩበት ወንጀል በክሱ ላይ የተመለከተው ሆኖ እያለ በግድ ቀድሞ እሰራበት በነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ጓደኞቼ ላይ በተለይም በፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እና በህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ የግንቦት ሰባት አባል እንደሆኑ ተደርጎ መስክር እየተባልኩ ስቃይ እየደረሰብኝ ነው›› በማለት አቤቱታውን ያሰማው አቶ ብርሃኑ፣ በተጨማሪም ማንነትን መሰረት ያደረገ ስድብ እንደሚሰደብ፣ ጨለማ ቤት እንደሚታሰር እንዲሁም የተጠየቀውን ካልፈጸመ ወደማዕከላዊ ሊመልሱት እንደሚችሉ እንደሚዝቱበት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡


ፍርድ ቤቱ በበኩሉ አቶ ብርሃኑ አለኝ ያለውን አቤቱታ በጽሑፍ እንዲያቀርብ በማሳሰብ፣ አቤቱታውን አይቶ የሚመለከተው አካል መልስ እንዲሰጥ እንደሚያደርግ ገልጾዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች በክሱ ላይ መቃወሚያ ካላቸው ለመቀበል ለግንቦት 28/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41499

Tuesday, May 19, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢዎች ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ተገለፀ


የሰማያዊ ፓርቲ አባላት አሁንም እየታደኑ እየታሰሩ ነው፡፡ በትናንትናው ዕለት የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ ተስፋዬ በፖሊስ ታድኖ ተይዟል፡፡ በአሁኑ ወቅት አራዳ ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢዎች በሚሊሻዎች ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ በቃሉ አዳነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ታዛቢዎቹ ‹‹ከአሸባሪ ፓርቲ ጋር አብራችሁ እየሰራችሁ ነው›› እየተባሉ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የገለጹት አቶ በቃሉ ቀሪዎቹን ‹‹ከአሸባሪ ፓርቲ ጋር ሲሰሩ አገኘናቸው ብለን እንከሳችኋለን›› እያሉ እያስፈራሯቸው ነው ብለዋል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር የምትገናኙበት ነው በሚልም ስልካቸውን እንደሚነጠቁ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን በየወረዳው ከብርሸለቆ የሰለጠኑ 150 ሚሊሻዎች ተመድበው የተቃዋሚ በተለይም የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን፣ ታዛቢዎችንና ህዝቡን በማስፈራራት ላይ እንደሚገኙ አቶ በቃሉ ገልጸዋል፡፡ አቶ በቃሉ አክለውም ‹‹በየ ወረዳው የተመደቡት ሚሊሻዎች ስራቸው ህዝቡን ማስፈራራትና ማሸበር ነው፡፡ ይህንም የሚያደርጉት ምንም ነገር ሳይከሰት ጥይት ወደ ላይ በመተኮስ ነው፡፡ በዚህ ሂደት በተባባሪ ጥይት የሞተ ሰውም አለ›› ብለዋል፡፡


በተመሳሳይ በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ሳንቃ ከተማ ላይ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ ያረጋል ፈንታው፣ ሁሴን እንድሪስና ዝናቡ ጋሊስ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ዕጩዎች በፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባቸው የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በሰሜን ወሎ ዞን ሚሊሻዎች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ድብደባ እንዲፈፅሙ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸውም አስተባባሪዎቹ ተገልጾአል፡፡ በዞኑ ካድሬዎች መራጩን ‹‹ኢህአዴግን እመርጣለሁ›› ብላችሁ ፈርሙ እያሉ እያስገደዱ እንደሆነ የገለጹት የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ‹‹ድምጼን የምርጫው ቀን ነው የምሰጠው›› የሚሉ መራጮችን ካድሬዎች ‹‹እኛን አትመርጡም ማለት ነው!›› እያሉ እየዛቱባቸው ነው ብለዋል፡፡

http://satenaw.com/amharic/archives/7053

Sunday, May 17, 2015

በዓረና መድረክ የተደናገጠው ሕወሓት በትግራይ የተቃዋሚዎችን የምርጫ ፖስተሮች መቅደድ ጀምሯል

አምዶም ገብረስላሴ ከትግራይ እንደገለጸው

የዓረና መድረክ የእጩ ተወዳዳሪዎች ምስል የያዙ ፖስተሮች በህወሓት የወረዳ ካቢኔ ኣባላት፣ ካድሬዎች፣ ፖሊሶችና የኮብልስቶን በመስራት ላይ ያሉ ወጣቶችና በህፃናት ኣማካኝነት እየተቀደደ ነው። የምርጫ ህጉ የተወዳዳሪዎች ፖስተር መቅደድ በህግ የሚያስጠይቅና የሚያስቀጣ ቢሆንም ህወሓት ግን በህጉ ተገዢ ለመሆን ፍቃደኛ ልጦን ኣልቻለችም።

ህወሓት በተግባርዋ የህዝብ መሳቅያ ሁና ፍርሃትዋ ምን ያክል እንደሆነበ ትዝብት ላይ ወድቃለች። ይህ የህወሓት የፖስተር ቀደዳ ተግባር ለኮረጆ ቀደዳ እንደ የኣቋም መፈተኛ ልምምድ ሊታስብ ይችላል። እነሱ የፈለጉት ህገወጥ ተግባር ሲሰሩ እኛ ደግሞ የህዝባችን ልብ ፣ ድጋፍና ማገር እያገኘን እንጎመራለን።

ዓረና መድረክ እምዲህ ያስደነገጣቸው ምክንያት በመላ ትግራይ የምርጫ ታዛቢዎች መልምሎ ኣዘጋጅቶ በማቅረቡ ነው። ለታዛቢዎቻችን የእስራት፣ የማስፈራራትና ዛቻ በኣስተዳዳሪዎች እየደረሰባቸው ነው።


የፖሊስ ስራውና ሃላፊነቱ በኣግባቡ ኣለመወጣት ምርጫው ወዳልሆነ ኣቅጣጫ እየወሰደው ይገኛል።
ነፃነታችን በእጃችን ነው


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41439

ህወሃትን መምረጥ ማለት ገዳይን መምረጥ ማለት ነው።

. ህወሃት ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ያደረገ ድርጅት ስለሆነ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት ለትግራይ ሕዝብ እንኳን የማይራራ የትግራይ ወጣቶችን ያስፈጀ በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበሯን በማስደፈሩ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት ወጣት ኢትዮጵያውያንን ለባርነት የዳረገ ስለሆነ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት ኢትዮጵያውያንን አገር ጥለው እንዲሰደዱ ያደረገ በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት የሀገርና የሕዝብ ሀብት ዘርፎ ወደ ውጭ በማውጣት አገር ያደኸየ በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት በመግደልና በማሰር የሚያምን ፋሽስት ድርጅት በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት ጠባብና ዘረኛ ድርጅት በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት የአማራውን ነገድ ሕዝብ ዘር በማጥፋት የተሰማራ በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት በክርስቲያኑም ሆነ በእስልምናው እምነት ጣልቃ በመግባት ሁከት የፈጠረ በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት የኢትዮጵያን አንድነት የናደና ኢትዮጵያውያንን እንዳይተማመኑ በማድረጉ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት ሕገ-መንግሥቱን የጣሰ በመሆኑ መመረጥ የለበትም፤

. ህወሃት ሕግ አውጭ፤ሕግ ተርጓሚና ሕግ አስከባሪ ባለመሆኑ መምረጥ የለብንም፤

. ህወሃት በሕዝብ ተመርጦ ስልጣን ላይ ስለአልወጣና የኢትዮጵያን ሕዝብ ስለማይወክል መምረጥ የለብንም፤

. ህወሃት ታሪክን ያዋረደና የካደ ድርጅት በመሆኑ ሊመረጥ አይገባውም፤

. ህወሃት የመደራጀት፤የመጻፍ፤የመሰብሰብ፤የመናገር፤በሀገር የመኖርን፤ሀብት የማፍራትን መብት በመግፈፉ ሊመረጥ አይገባውም፤

. ህወሃት በግድ አባል የማድረግና ከአባላቱ ውጭ ያለውን ሕዝብ የማይፈልግ በመሆኑ በምርጫ ካርድ ሊባረር ይገባዋል፤

. ህወሃት ምሊዮኖቹን  ያሠረ በመቶ ሽህ የሚቆጠሩትን የገደለ ወንጀለኛ ድርጅት ስለሆነ መመረጥ የለበትም።


እንደ አንድ ኢትዮጵያዊነቴ ህወሃት ከዚህ በላይ በጠቀስኳቸውና በሌሎችም ተጠቅሰው የማያልቁ ህልቆ መሳፍርት የሆኑ ፋሽስታዊ ድርጊቶቹ ሊመረጥ አይገባውም ብየ እየሞገትኩ ስለሆነ መራጩ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቅርቡ በሚጀመረው የ2007 ምርጫ ህወሃትን ከጨዋታው ውጭ ማድረግ አለበት።ህዝቡ ማድረግ ያለበትን አድርጎ ህወሃት በተለመደው መንገድ ሄዶ የምርጫ ኮሮጆ እዘርፋለሁ ካለ ከዚያ በኋላ የሚሆነውን እናያለን።ሕዝቡ እነዚህን ሁሉ እያወቀ በማይረባ ጥቅማ ጥቅምና በህወሃት የውሸት ጋጋታ ተጭበርብሮ ህውሃትን ቢመርጥ አንድምታው የሚሆነው፦ በግልጽ ዝረፍ፤ግደል፤እሠር፤ደብድብ፤ከሀገር አሳደህ አስወጣን፤መሬታችን ሽጥ ለገፀ-በረከት አድል፤ድንበራችንና ሉዓላዊነታችን አስደፍር፤ልጆቻችንን ለባርነት አሳልፈ ስጥልን፤ዜግነታችን ግፈው ወዘተ ብሎ እንደወሰነ ህዝብ ስለሚታይ አስቀድመን ልናውቀው ይገባል። 

Friday, May 15, 2015

ኢህአዴግ በዜጎች ላይ ፍርሃት በመልቀቅ እንዲመረጥ እያግባባ ነው ሲሉ የባህርዳር ነዋሪዎች ተናገሩ


ዘጋቢያችን በላከችው ሪፖርት የገዢው መንግስት ካድሬዎች በየመንደሩ በመዞር የሚደርጉት የምርጫ እንቅስቃሴ የነዋሪዎችን ነጻነት ከማሳጣቱ በተጨማሪ፣ ኢህአዴግ በሚጠራው የመንደር ስብሰባዎች የሚቀር ሰው የተቃዋሚ ድርጅት ደጋፊ ተብሎ ይመዘገባል።

የገዢው ፓርቲ አባላትና የቀበሌ አመራሮች በየሰፈሩ በሚያደርጉት ስብሰባ በአካባቢው የሚኖሩ ባለሃብቶችን ያለ ፈቃዳቸው ለዕለቱ የሚስፈልገውን ለቡና፤ዳቦ እና ቆሎ ዝግጅት የሚውል ገንዘብ በመቀበል በሰፈሩ በመዘዋወር እንዲሰባሰቡ የሚያደርጉ
ሲሆን፣ የሚዘገዩ ሰዎችን ስልክ በመደወል ‹‹ ለምን አልመጣችሁም?›› ፣ ‹‹ ጸረ ህዝብ ስራችሁን አቁሙ!›› በሚሉ ማስፈራሪያዎች ገዢውን መንግስት እንዲመርጡ ለማድረግ እየጣሩ ነው።


በየመንደሩ የሚካሄዱት ስብሰባዎች በየሶስት ቀኑ የሚቀጥሉ መሆኑን ያስታወቁት የገዢው መንግስት ካድሬዎች በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ ጫና በመፍጠር ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሌላ ዜና ደግሞ አምስቱ የኢህአዴግ አጋር ተብለው የሚታወቁ ክልሎች ማለትም ሶማሌ፣ አፋር፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ እና ሃረሪ ቅዳሜ በአዲስአበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የስብሰባ ማዕከል በመገኘት ለኢህአዴግ ያላቸውን አጋርነት ከማረጋገጥ አልፈው በመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደሰማያዊ ፓርቲ ያሉትን ፓርቲዎች ያወግዛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም ኢህአዴግ በወጣት ሊጉ አማካይነት በአዲስአበባ በየክፍለከተማው ወጣቱ ኢህአዴግን እንዲመርጥ የተለያዩ ቅስቀሳዎችን ሲያደርግ የሰነበተ ሲሆን፣ በብዙ አካባቢዎች ወጣቶች ኢህአዴግን እንደማይመርጡ ፊት ለፊት ከመናገር ጀምሮ ተቃውሞአቸውን በተለያየ መንገድ እየገለጹ መሆናቸው ታውቆአል፡፡


ሰሞኑን በየካ ክፍለከተማ በተደረገ አንድ ስብሰባ ላይ ወጣቶች “ኢህአዴግ ምን ስላደረገልን እንመርጠዋለን» በማለት ጥያቄ ከማቅረብ ጀምረው ሥራአጥነትና የኑሮ ውድነት፣ ሙስናና ብልሹ አሰራር የመሳሰሉ ችግሮችን በማንሳት እንደማይመርጡት በግልጽ ተናግረዋል።

http://satenaw.com/amharic/archives/7011

Thursday, May 14, 2015

የሁለት አመት አስተማሪ ደሞዝ ለአንድ ቀን ፌሽታ በዲሲ (የሳሞራ የኑስ የሆቴል ወጪ በአንድ ቀን)

ጀነራል ሳሞራ የኑስ፣ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኤታ ማጆር ሹም ናቸው። አንዳንዶች እንደዉም አገሪቷን የሚመሩት አቶ ኃይለማሪያም ሳይሆኑ እኝሁ ጀነራል ናቸው የሚሉም አሉ። ጀነራሉ በዋሽንግተን ዲሲ Mandarine Oriental Hotel እንዳረፉ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። ጀነራሉ ለምን ወደ አሜሪካ እንደመጡ የታወቀ ነገር የለም። በዋሺንገትን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ድህረ ገጽ ስለ ጀነራሉ ጉብኘት በድህረ ገጹ ላይ ምንም ነገር አላሰፈረም። ምናልባትም የጀነራሉን ጉብኘት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላያውቀዉም ይችላል። ጀነራል በግላቸው ለግል ጉዳይ መጥተዉም ይሆናል። በምርጫው ወቅት አዲስ አበባ አለመገኘታቸው ፣ ምናልባት የሕክምና ችግርም አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል የሚል ግምትም በአንዳንዶች ዘንድ አለ።

ሆኖም አንድ ትኩረታችንን ሊሰብ የሚገባ ትልቅ ነጥብ አለ። ጀነራሉ ያረፉበት ሆቴል እጅግ ዘመናዊና በጣም ዉድ ሆቴል ነው። ለምሳሌ ማንዳሪን ሱት የሚባለው በቀን 1295 ዶላር ( 28 ሺህ ብር ) ነው የሚከፈለው። አምባሳደር ሱት 1495 ዶላር ( 31 ሺህ ብር ) ሲሆን ኦሪየንታል ሱት ደግሞ 2500 ዶላር ( 53 ሺህ ብር) ነው።

እንደዉ አንድ ኢትዮጵያ ያለ አስተማሪ በደንብ ተከፍሎት የወር ደሞዙ 2000 ብር ቢሆን፣ ጀነራል ሳሞራ ለአንድ ቀን ዲስ ፌሽታ የሚያወጡት ቢያንስ ለሁለት አመታት የአንድ አስተማሪን ደሞዝ የሚከፍል ነው ማለት ነው።

የጀነራሉን ወጭ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍሎ ከሆነ፣ ኤምባሲው አወቆት፣ እንግዲህ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ምን ደረጃ ላይ እንዳለች በገሃድ በድጋሚ የሚያሳየን ነው የሚሆነው።


በግላቸው ከሆነ ደግሞ ጄነራል ሳሞራ የመጡት፣ ከሁለት አመታት በላይ የአንድ አስተማሪ ደሞዝን ሊሸፍን የሚችል ገንዘብ፣ ለአንድ ቀን ሆቴል የመክፈል አቅም እንዴት ሊኖራቸው ቻለ የሚል ጥያቄ ይነሳል። ይሄም አሁን የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ለጥቂቶች ሲኦል እንደ ጀነራል ሳሞራ ላሉ በሙስና ለተጨማለቁ ዘራፊ ባለስልጣናትና መኮንኖች ግን ገነት መሆኗንም የሚያሳይ ነው።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41359

Wednesday, May 13, 2015

ሳሞራ የኑስ በዋሽንግተን ዲሲ እጅግ ተዋረዱ ተቃውሞው ቀጥሏል

በዋሽንግተን ዲሲ ማንደሪን ኦሪየንታል ሆቴል ድንገት የተገኙት የወያኔው መንግስት መከላከያ ሚኒስተር ጄነራል ሳሞራ የኑስ በኢትዮጵያዊያኑ ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶባቸው ውርደትን መከናነባቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ::

በአንድ ለሊት አዳር 12 ሺህ 700 ብር በሚከፈልበት በማንደሪን ኦሪየንታል ሆቴል ያረፉት ጀነራል ሳሞራ የኑስ ከዋሽንግተን ዲሲ ግብረሃይል ወጣቶች ጋር ፍጥጫ ገጥመው ከፍተኛ የሆነ ግብግብ ተፈጥሯል:: አካባቢው በዲሲ ፖሊሶች የታጠረ ሲሆን ሳሞራም ካረፈበት ከዚህ ሆቴል ሊወጣ እንዳልቻለ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጠቁመዋል::

ኢትዮጵያውያኑ “ኢትዮጵያውያንን የሚያሰቃይ ወንጀለኛ ለፍርድ ይቅረብ” በሚል ሳሞራ ላይ ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ናቸው::

በሽንግተን ዲሲ መጥተው በኢትዮጵያውያኑ ውርደትን ከተናነቡ የወያኔ ተላላኪ ባለስልጣናት ውስጥ ስብሃት ነጋ; ሬድዋን ሁሴን; ሶፊያን አህመድና ሌሎችም ይገኙበታል::

ግብግቡ አሁንም የቀጠለ ሲሆን የደረስንበትን መረጃ እናሳውቃችኋለን::

 http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41324

Tuesday, May 12, 2015

እነ ወይንሸት ዋስትና ተከልክለው ለግንቦት 24 ተቀጠሩ

መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም ራሱ በጠራው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳትና በማስተባበር›› ካሰራቸው ሰዎች መካከል እነ ወይንሸት ሞላ ላይ ክስ መሰረተ፡፡ በፌደራል አቃቤ ህግ ከሳሽነት ክሱ የተመሰረተባቸው አራት የሰማያዊ አባላትና አንዲት ሌላ ግለሰብ ሲሆኑ፣ ተከሳሾች ዛሬ ግንቦት 4/2007 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቄራ ምድብ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡

በእነ ወይንሸት ሞላ የክስ መዝገብ የተካተቱት ተከሳሾች ወይንሸት ሞላ፣ ዳንኤል ተስፋዬ፣ ኤርሚያስ ጸጋዬ፣ ማስተዋል ፈቃዱ እና ቤተልሄም አካለወርቅ ሲሆኑ፣ የክሱ ይዘትም በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና 490(3) የተመለከተውን በመተላለፍ መሆኑ በክሱ ላይ ተገልጹዋል፡፡

1ኛ ተከሳሽ መንግስት በጠራው ሰልፍ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ሲናገሩ፣ ስድብና ማንቋሸሽ እንደፈጸመችና ሌሎች ተከሳሾችን በማስተባበር ‹‹ናና ናና መንግስቱ ኃ/ማርያም ናና››፣ ‹‹ወያኔ አሳረደን፣ ወያኔ ሌባ›› እያሉ ህዝቡን ያነሳሱ እንደነበር ክሱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

ሁሉም ተከሳሾች ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን እንዲያስጠብቅላቸው የጠየቁ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ጥያቄያቸውን ባለመቀበል 20 ቀናት ቀጠሮ ሰጥቶባቸዋል፡፡ በዚህም ተከሳሾቹ ለግንቦት 24/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፣ ወደ ‹ማረፊያ ቤት› እንዲወርዱም ታዝዟል፡፡

አቃቤ ህግ አሉኝ ያላቸውን የሰው ምስክሮች ያሰማ ሲሆን፣ በምስክሮቹ ቃል ላይ ወጥነት የሌለውና ተደጋጋሚ መደነባበር ተስተውሎባቸዋል፡፡


(የክሱን ሙሉ ይዘትና የቀረቡ ምስክሮችን ዝርዝር ይመልከቱ!)



 http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41299


Monday, May 11, 2015

የጋምቤላ ነዋሪዎች መንግስት በታጠቁ አካላት እያስጨፈጨፈን ነው አሉ !!



በጋምቤላ ክልል፣ መጃንግ ዞን፣ ጎደሬ ወረዳ የሚኖሩ ዜጎች በመንግስት በተቀነባበረ ሴራ ጭፍጨፋ እየደረሰባቸው እንደሆነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በተለይ ከግንቦት 2006 ዓ.ም ጀምሮ 400 ያህል ነዋሪዎች እንደተገደሉ የገለጹት ነዋሪዎች መንግስት የእርስ በእርስ ግጭት ለማስመሰል ቢሞክርም ችግሩ በመንግስት የተቀነባበረ እንደሆነ እንደሚያምኑ ገልጸዋል፡፡
¨
‹‹የአብዛኛዎቹ ነዋሪዎች እርሻ ለገዥው ፓርቲው ካድሬዎች በመስጠት እኛ ከቦታችን እንድንፈናቀል ጥረዋል፡፡

አንወጣም ስንል ግን በግድ እንድንወጣ የተላከብን ጨፍጫፉ ነው›› ሲሉ የአካባቢው ነዋዎች በስልክ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በዛሬው ዕለት በግልጽ ባልታወቁ ነገር ግን እነሱ ሚሊሻዎች እንደሆኑ በሚገምቷቸው 10 ያህል ሰዎች እንደተደገደሉ ነገር ግን ከስድስቱ በስተቀር የሌሎቹን ሰዎች አስከሬን ማንሳት እንዳልቻሉ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ 


ነዋሪዎቹ አክለውም ‹‹መንግስት በጭፍጨፋው ላይ እጄ የለበትም ቢልም ህዝቡ ሲማረር ይወጣል በሚል እያስጨፈጨፈን ይገኛል፡፡

 በርካታ ወታደርና ፖሊስ ቢኖርም ጭፍጨፋውን ለማስቆም ጥረት አለማድረጉ መንግስት ከበስተጀርባው እንዳለ እንድናምን አድርጎናል፡፡›› ብለዋል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41294

Friday, May 8, 2015

የለውጥ ሃይሎችን አፍሶ በማሰር እና በማሳደድ ስር ነቀሉን የለውጥ አብዮት ማስቆም አይቻልም

በሃገራችን ውስጥ ለይስሙላ በወያኔ የተጠራውን ምርጫ በመንተራስ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያጣው የወያኔ ስርአት የለውጥ ሃይሎችን እያፈሰ በማሰር እና በማሳደድ ላይ መሆኑ ባለፉት ሳምንታት እየተመለከትን ነው::የወያኔ አምባገነን ጁንታ በጠራው የጸረ አይሲስ ሰልፍ አሳቦ የተቃዋሚ ሃይሎች አባላትን በተለይ የሰማያዊ ፓርቲ የለውጥ ሃይሎችን እንዲሁም የተለያዩ የለውጥ ፈላጊ ሃይሎችን ከየመንገዱ እየለቀመ እያፈሰ በማሰር ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ የማጎሪያ ካምፖች እያከማቸ ይገኛል:እንዲሁም መንግስታዊ ሽብርተኝነትን በመሸሽ የሚሰደዱ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ በገሃድ እየታየ ነው::

በአዲስ አበባ እና በክፍለ ሃገር ከተሞች ምርጫውን ተከትሎ ግርግር ያነሳሉ ሕዝባዊ አመጽ ይመራሉ ያስተባብራሉ የተባሉ ወጣቶች ታፍሰው የታሰሩ በአውቶብስ እና በጭነት መኪና ተጭነው ከየእስር ቤቱ ከከተሞች ክልል ውጪ ባሉ የማጎሪያ ካምፖች በመውስድ ላይ መሆኑን ሲታወቅ ገና ያልተጫኑ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች በየእስር ቤቱ እንደሚገኙ ጉዳዩን እየተከታተሉ የሚገኙ የገለጹ ሲሆን የለውጥ ሃይል የሆኑ ወጣቶችን አፍሶ አስሮ እና አሳዶ ስር ነቀል የሆነውን የለውጥ አብዮት ማስቆም እንደማይቻል ወያኔዎች በፍጹም አልተረዱትም::እንዲሁም ከምርጫው ጋር በተያያዘ አፈሳውን እና መታሰሩን በመፍራት የተለያዩ ክፍለሃገር ነዋሪዎች ወደ ጎረቤት ሃገሮች እየተሰደዱ መሆኑ ከየአከባቢው የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ::


ምርጫውን ተከትሎ የስል ነቀል አብዮት አመጽ ያሰጋው ወያነ ህዝቡ አንድነቱን በማሳየት በአደባባይ ተቃውሞውን መግለጹ ከፍተኛ ስጋት ላይ እንደጣለው ራሱ እየመሰከረ ባለበት ባሁኑ ወቅት የምርጫ ካርዶችን አምጡ በማለት በማስገደድ ላይ ይገኛል::ወያኔ ማንም እንደማይመርጠው በማወቁ ያለው እድል የመሳሪያ ሃይል ተጠቅሞ በአንድነት የተነሳበትን ሕዝብ ማዳከም ሌላው አላማ ቢሆንም አንድ ለአምስት ብሎ ከዚህ ቀደም ያደራጀው እንዳልሰራለት እና አሁንም በሌላ መንገድ ያንኑ አንድ ለአምስት የሚለውን አደረጃጀቱን ለምርጫው ለመጠቀም እየሰራ መገኘቱ የለውጥ ሃይሎች የትግል ውጤት ምን ያህል እንዳፍረከረከው በተግባይ እየታየ ነው::ይህንንም የለውጥ ሃይሎች እንቅስቃሴ በመስጋት በከፍተኛ ደረጃ ወጣቶችን በማፈስ በማሰር እና በማሳደድ ለማሸማቀቅ ቢሞክርም ቀሪው የህብረተሰብ ክፍል ከንፈሩን በመንከስ ወያኔን ሊበቀለው በዝግጅት ላይ መሆኑን በተግባር አንድነቱን አጠናክሮ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል::ወጣቱን ሃይል በማሰር እና በማሳደድ ስር ነቀሉን የለውጥ አብዮት ማስቆም አይቻልም::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41181

Thursday, May 7, 2015

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተያዙበት ሁኔታ ለህይወታቸው አስጊ ነው ተባለ

የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በከፍተኛ ህመም በመሰቃየት ላይ ሲሆኑ እስካሁን በዶክተሮች ለመጎብኘት አልቻሉም።

አያያያዛቸው የከፋ መሆኑን በማስመልከት የእንግሊዝ መንግስት አስቸኳይ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መጻፉንም ምንጮቻችን ገልጸዋል።

አቶ አንዳርጋቸው ያለፉትን ተከታታይ ወራት ጸሃይ የሚባል ነገር ሳያዩ ጨለማ ቤት ተዘግቶባቸው አሳልፈዋል; ከህመማቸው ጋር በተያያዘም ምግብ መመገብ በእጅጉ ቀንሰዋል።

በከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው፣ አያያዛቸው አስከፊ እንደሆነ በቅርቡ ለጎበኙዋቸው የእንግሊዝ አምባሳደር መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ይህንን ተከትሎም የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጠንከር ያለ ደብዳቤ መጻፉን የአዲስ አበባ ምንጮች ገልጸዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ በአፋጣኝ የማይለወጥ ከሆነ፣ በህይወታቸው ላይ ያልተጠበቀ አደጋ ሊፈጠር እንደሚችል ያስጠነቀቁት የእንግሊዝ ባለስልጣናት፣ አቶ አንዳርጋቸው የኮንሱላር ድጋፍ እንዲያገኙ፣

በመደበኛ እስር ቤት ውስጥ እንዲታሰሩና በጠያቂዎች እንዲጎበኙ ፣ ሃኪሞች እንዲያዩዋቸውና ሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር ደብዳቤ መጻፋቸውን ምንጮች ገልጸዋል።


ገዢው ፓርቲ ከአቶ አንዳርጋቸው የረባ መረጃ ለማግኘት ባለመቻሉ_የስነ ልቦና ጫና በማሳረፍና ህክምና በመከልከል ለመጉዳት ማሳቡን ምንጮች ገልጸዋል።

የእንግሊዝ ባለስልጣናት በሂደት ስለሚወስዱት እርምጃ ግልጽ ባያደርጉም፣ ጉዳዩን በቀላሉ እንደማያዩት ለኢህአዴግ ሹሞች እንደገለጹላቸው ታውቋል።

አቶ አንዳርጋቸው በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ለኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች ተላልፈው ከተሰጡ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ሁለት ጊዜ በቴሌቪዥን አቅርቧቸዋል። ተቆራርጦ የተላለፈውን ቪዲዮ ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ትችት ሲቀርብብት ቆይቷል።


ኢህአዴግ አቶ አንዳርጋቸውን ህዝብ ሊጎበኛቸው በሚችል እስር ቤት አለማሰሩና ሰብአዊ መብታቸውን ሁሉ መግፈፉ የገዢውን ፓርቲ የፍርሃትና የበቀል ደረጃ፣ እንዲሁም ራሱ ላወጣው ህግ እንኳን የማይገዛ መሆኑን የሚያሳይ ነው ተብሏል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41158

Wednesday, May 6, 2015

የሰሜን ጎንደር ሕዝብ አመጽ በርትቷል * በድንበር ከተሞች አሁንም ችግሩ እየሰፋ ነው

የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እና ካድሬዎቻቸው በሕወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ተወካዮች መሪነት በባህር ዳር ስብሰባ መቀመጣቸው በታወቀበት በዚህ ሳምንት በአማራ ክልል ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ሕዝባዊ እምቢተኝነት መከሰቱን እና የፌዴራል ፖሊሶች ከሕዝቡ ጋር እየተጋጩ መሆኑ ሲጠቆም በጎጃም ገበሬው በብጡ ደጃፍ እና በቤቱ ውስጥ የእያኔን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት እንዲለጥፍ እየትገደደ እና እምቢ ያለ በመታሰር ላይ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል::

ሕወሓቶች በሚመሩት እና በባህር ዳር እየተካሄደ ያለው የብአዴን ስብሰባ ላይ ከምርጫው ጋር ተያይዞ የሚመጥውን ችግር እና ሕዝቡ ሊመርጠን ስለማይችል በድምጽ መስጫ ካርዶች ዙሪያ መወሰድ ስላለባቸው እርምጃዎች እንዲሁም ትጥቅ ያልፈቱ መሳሪያ የቀበሩ ሰዎች ካሉ አስቸኳይ ክትትል ተደርጎ እርምጃ እንዲወሰድ የሚሸፍቱ ሰዎች የሚተረጠሩ ካሉ እንዲታሰሩ የሚሉ ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከትግራይ ክልል አማራ አዋሳኝ በሆኑ ቦታዎች ያሉ የሕወሓት ሚሊሻዎች እና ካድሬዎች ወደ አማራ ክልል በማምጣት ድምጽ ሰጥተው እደ አከባቢያቸው እንዲመለሱ እንዲሁም በተለያየ ወረዳ የተለያያ የመራጭ ካርድ ዬሰዱ ሰዎች አስቸኳይ የትራንስፖርት አቅርቦት እየተደረገላቸው በየወረዳው እየሄዱ እንዲመርጡ ሲባል ከምርጫው በኋላ ሊነሱ የሚችሉ የአመጽ ስጋቶችን ለመቆጣጠር የመከላከያ ሰራዊት አባላይ የፌዴራል ፖሊስ ልብሶችን በመልበስ ተክተው እንደሚሰሩ እና ካድሬዎች እና የጸጥታ ሰራተኞች አስፈላጊዉን ትብብር በማድረግ የሚፈጠረው ችግር በቁጥጥር ስር እንዲውል እንዲያደርጉ ከሕወሓት ሹሞች መመሪያ ተሰቷቸዋል::


በሰሜን ጎንደር የላይ እና የታች አርማጮ ጨምሮ በአብድራፊ በሁመራ በመተማ በሸዲ በጭልጋ አክባቢዎች በከፍተኛ ደረጃ ሕዝቡ እና የወያኔ ፖሊሶች ውጊያ የገጠሙ ሲሆን በርካቶች ሲቆስሉ በአከባቢው የተነሳው የህዝብ እምቢተኝነት እየሰፋ መምጣቱን እና ጥያቄዎች ምላሽ አለማግኘታቸው ሲከፋ የመኖሪያ ቤታችውን በማፍረስ ሕዝቡን ለጎዳና ተዳዳሪነት መዳረጉ በመተማ እና አከባቢው የሚኖሩ ሕዝቦችን ቁጣ ቀስቅሶ እስከ ዛሬ ድረስ ሊበርድ ያልቻለ ከፍተኛ ግጭት በአከባቢው እየተደረገ እንደሆነ የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::በአጠገባችን መጥቶ የሚያግዘን ማጣታችን ነው እንጂ ወያኔን ከጎንደር ክፍለሃገር ጠራርገን እናወጣው ነበር ያሉ ወጣቶች ባለው ስርአት መማረራቸውን በቁጣ ይናገራሉ::ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎጃም ክፍለሃገር የሚኖሩ ገበሬዎች የወያኔን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት በቤታቸው እስጥ እና በቤታቸው ደጃፍ ላይ በግዳጅ እንዲለጥፉ የተደረገ ሲሆን ለመለጠፍ ፍቃደኛ ያልሆኑ ገበሬዎች በመታሰር ላይ እንደሚገኙ አንድ የደብረማርቆስ ወጣት በላከው መረጃ ገልጿል:: ሕዝቡ አስተባባሪ እና አደራጅ ነው ያጣው ቢባልም በራሱ መሪነት ብሶቱን እየገነፈለ እየወታ የሚገኘው ሕዝብ ለነጻነቱ በጋራ ሆኖ መታገሉን እንደቀጠለ ነው::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41142

Tuesday, May 5, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው:: ‪

ሰማያዊ ፓርቲ የአፍሪካ ህብረት ምርጫውን እንዳይታዘብ እንደሚፈልግ ገለጸ

•የህብረቱ ታዛቢ ቡድን ፓርቲዎችን አነጋግሯል
• በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ አባላት ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ቀጥሏል
• ‹‹የተጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው››


የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ሰበብ እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ሀሙስ ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም ብሌን መስፍንና ተዋቸው ዳምጤ ከመስሪያ ቤት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን ሚያዝያ 24/2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተደረገውን አመጽ መርታችኋል፡፡›› በሚል ፖሊስ ክስ እንዳቀረበባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ዛሬ ሚያዝያ 26/2007 ዓ.ም ማቲያስ መኩሪያ ቤቱ ውስጥ እያለ በፖሊስ ተይዞ ታስሯል፡፡ ማቲያስ፣ ብሌንና ተዋቸው ወረዳ 10 (ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ) ታስረው ይገኛሉ፡፡ ይህንን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው እስርም ‹‹መንግስት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው፡፡ ፖሊስ ምርመራ ሳይጨርስ በሀሰት 20 አባላትንና 6 አመራሮችን አስረናል ብለው ነበር፡፡ እነሱ የፈለጉት ይህን ሚዲያ ላይ ወጥተው በሀሰት የፈፀሙትን ውንጀላ ማሰመሰል ነው፡፡›› ሲል አቶ ዮናታን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡


በሌላ ዜና በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ደህንነትና ፖሊስ የሚፈፅመው ድብደባ አሁንም መቀጠሉ ተገልጾአል፡፡ በዛሬው ቀን የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነችው የሀሳብ ጌታቸው ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ ወረቀት በትነሻል›› በሚል ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀሙባት ተገልጾአል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ የአፍሪካ ህብረት 5ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንዳይታዘብ እንደሚፈልግ ለህብረቱ ታዛቢ ቡድን ገለጸ፡፡ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ዛሬ ሚያዝያ 26/2007 ዓ.ም በምርጫ የሚወዳደሩ ፓርቲዎችን በተናጠል በምርጫው ዙሪያ ያነጋገረ ሲሆን፣ ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ቡድኑን ያነጋገሩት አቶ ወረታው ዋሴ እና አቶ እምዕላሉ ፍስሃ ህብረቱ ምርጫውን እንዳይታዘብ እንደሚፈልጉ አስረድተዋል፡፡

የህብረቱ ታዛቢ ቡድን ከአሁን ቀደም በተካሄዱት ሀገራዊ ምርጫዎች መታዘቡን ያወሱት የሰማያዊ ተወካዮች፣ ህብረቱ በሪፖርቱ ለአምባገነኖች እውቅና ከመስጠት ያለፈ አንዳች እውነታውን የሚያሳይ ትዝብቱን አላስቀመጠም ሲሉ ለታዛቢ ቡድኑ መግለጻቸውን ተናግረዋል፡፡

‹‹ህብረቱ የአምባገነኖች ስብስብ ነው›› ያሉት የፓርቲው ተወካዮች፣ የአውሮፓ ህብረትና አሜሪካ በኢትዮጵያ ምርጫ ላይ ተስፋ በማጣት በታዛቢነት እንደማይሳተፉ ማሳወቃቸውን በመግለጽ፣ የአፍሪካ ህብረት ግን ለአምባገነኖች እውቅና ለመስጠት መምጣቱ በሰማያዊ ፓርቲ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል፡፡

‹‹ቀደምት ፓን አፍሪካኒስቶች አፍሪካን ከቅኝ ግዛት ነጻ ለማውጣት ታግለዋል፤ የአሁኖቹ እውነተኛ ፓን አፍሪካኒስቶች ደግሞ አፍሪካን ከአምባገነኖች ነጻ በማውጣት ወደ ዴሞክራሲ ማሸጋገር ይጠበቅባቸዋል›› በማለት ለህብረቱ ታዛቢዎች የገለጹት የፓርቲው ተወካዮች፣ በዚህ ረገድ ህብረቱ ተገቢውን ስራ እያከናወነ ነው ለማለት እንደማይቻል አስረድተዋል፡፡


የአፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት ጋባዥነት 5ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለመታዘብ በቅርቡ አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል፡፡ ህብረቱ በዛሬው ዕለት ያነጋገራቸው ፓርቲዎች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ በውል አልታወቀም፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41121

Sunday, May 3, 2015

“እንከን የለሹ” የምርጫ ዝግጅት በትግራይ እንዲህ ባለ “እንከን የለሽ” ሁናቴ እየተከናወነ ነው፡

እንግዲህ የትግራይ ክልል ምርጫ ቦርድ ሐላፊዎች፣ አስፈፃሚዎች በየገጠሩ ህዝቡን እየሰበሰቡ “ንቧ እቺ ናት፣ እርሷ ላይ “X” የምታደርጉት፡፡ ሌሎች ምልክቶች ትናንት ሲያርዷችሁ፣ ሐውዜን ላይ ቦምቦች ሲያዘንቡባችሁ የነበሩት የጠላቶቻችሁና መቐለን ባግዳድ ማድረግ የሚሹ አሸባሪ ሐይሎች ምልክት ነው፡፡ ሁላችሁም አንዳንድ ስዕል ወደቤታችሁ ውሰዱና በደምብ አጥኑት፡፡ እላዩ ላይ X ማድረግ ተለማመዱ፡፡ ቀኑ እየደረሰ ነው፡፡ “
“ሌሎች ያልመጡትን በተለይም ወጣቶች ይህንን በደምብ አስረዷቸው፣ ተሳስተው ከጠላቶች ጋር እንዳያብሩ ምከሯቸው፡፡ ቄሶችም የነፍስ ልጆቻችሁን ይህንን እንዲመርጡ ማሐላ አስገቧቸው፤ እምቢ ካሉም ገዝቷቸው፣ አውግዛችሁም የነፍስ አባትነታቹ አቁሙ፡፡ “
“ሌላ ፓርቲን የመምረጥ ዝንባሌ ያሳየ ማንኛውም ገበሬ የመስኖ ውሐ ካለ ከውሐው እንዳይጠቀም፣ ቢታመም እንዳትደርሱት፣ ቢሞትም እንዳትቀብሩት፣ ከማንኛውም ማሕበራዊ ኑሮ እንዲገለል፡፡”
“ደግሞ ‘እቺ ንብ ለናንተ ማር ሰጠች እንጂ እኛንስ ከመንደፍ ያለፈ ምንም አልፈየደችልንም’ የምትሉ እንዳላችሁ ሰምተናል፣ ራዕዩ ሲገለፅላችሁ እናንተም ማሩ መቁረጥ ትጀምራላችሁ፡፡
ግንቦት 16 ላይ እንገናኝ፡፡ እነዚህን ስዕሎች ላይ X ማድረግ በተለማመዳችሁት መሰረት ያው “X” ማድረግ ነው፡፡”
እንከን የለሹ “የምርጫ ስልጠና” በትግራይ እንዲህ ባለ ሁኔታ እየተካሄደ ነው፡፡ ምርጫ አስፈፃሚውም “እንከን የለሽ ገለልተኛነቱ”ን እንዲህ ባለ “እንከን የለሽ ሁኔታ” አስመስክሯል፡፡
http://satenaw.com/amharic/archives/6688

Saturday, May 2, 2015

"ለመሆኑ የሃይማኖት መሪዎችና ሽማግሌዎች በአገሩ የለንም?"

ሴቶችን በወንዶች ፊት፣ ወንዶችን በሴቶች ፊት ልብስ እያስወለቁ የአካላቸውን ክፍሎች ሁሉ ለማየት የሚያስችል እንቅስቃሴ አንዲሠሩ ማስገደድ በሽተኞችን ያስደስታል፤ የምርመራ ዘዴ ግን አይደለም፤ ውርደት እንዲሰማቸው ከሆነ በወራዶች ሰዎች ፊት የምን መዋረድ አለ? ወራዶች እነሱ ደረጃ ላይ ከእነሱ ጋር ያስተካክላሉ አንጂ አያዋርዱም፤ በሌላ አነጋገር ወራዶች አያዋርዱም፤ ወራዶቹ ደንቆሮዎችም ሆነው ነው እንጂ ልብስ የሚያስወልቁ እነሱ ብቻ አይደሉም፤ ሀኪሞችም ልብስ አስወልቀው፣ አጋድመው በጣታቸውም ሆነ በመሣሪያ የፈለጉትን የአካል ክፍል አንደፈለጉ ያደርጉታል፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ከሚያደርጉት የሀኪሞቹ የሚለየው ሀኪሞቹ ሰዎችን ለማዳን ሲሉ ነው፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ግን የራሳቸውን ሱስ ለማርካት፣ የራሳቸውን ህመም ለማስታገስ ነው፤ ወራዶቹንና ደንቆሮዎቹን ከመለዮአቸው አራቁቻቸዋለሁ!

ከነውር በቃላት ወደነውር በተግባር፣ ያውም በመሥሪያ ቤት!

ዱሮ ዱሮ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቲያትር ፊት ለፊት የአንድ ኢጣልያዊ ቡና ቤት ነበር፤ እዚያ ውጭ ተቀምጠን ቡና ስንጠጣ አንዲት ውብ ሴት ወደጸጉር መሥሪያው ቤት ስትመጣ የሁላችንም ዓይኖች እየዘለሉ እስዋ ላይ ዐረፉ፤ ከሦስታችን አንዱ ስለሴትዮዋ የወሲብ ችሎታ በዝርዝር መናገር ሲጀምር ሁለታችን ተያየንና አፈርን፤ ጨዋታው የጣመለት መስሎት ሲቀጥል የሕግ ባለሙያ የሆነ ጓደኛዬ አቋረጠውና ‹‹ስማ! ይህን ጊዜ እናትህ በአንድ ቦታ ስታልፍ አንዱ እንዳንተ ያለ ስለእርስዋ ችሎታ ያወራ ይሆናል!›› አለው፤ ሊጠጣ ወደአፉ ያስጠጋውን ስኒ ቁጭ አደረገና ተነሥቶ ሄደ፡፡

ሥልጣን ተሰጥቷቸው ሴቶችን ልብስ እያስወለቁ ምርመራ ነው የሚሉ በእናቶቻቸውና በእኅቶቻቸው ላይ ሊደርስ እንደሚችል አይገነዘቡም ይሆናል፤ ደንቆሮ የሚያደርጋቸውም ይኸው ነው፤ የአንዱ እናት አንድ ቦታ ላይ ራቁትዋን ቆማ በሽተኞች ተሰብስበው ሲስቁባት፣ በሌላ ቦታ ደግሞ ጓደኛው የእሱን እናት ወይም እኅት ያንኑ እያደረገ ያስቅባት ይሆናል፤ አንተ በእኔ እናትና በእኔ እኅት አስቅባቸው፤ እኔ ደግሞ በአንተ እናትና በአንተ እኅት አስቅባቸዋለሁ፤ ይህንን እየሠራን ኑሮአችንን እናቃናለን፤ እቤታቸው ሲገቡና ከእናቶቻቸውና ከእኅቶቻቸው ጋር ሲቀመጡና ሲበሉ (?!) ሰው ይመስላሉ፤ እነዚያም ግፉ የተፈጸመባቸው እናቶችና እኅቶችነውራቸውንምሥጢር አድርገው ለሰው ስለማይናገሩ ግፈኞችና የግፍ ሰለባዎች አብረው ይበላሉ!

አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ አንዳንድ ሴቶች የደረሰባቸውን ተናገሩ፤ አሁን ያፍራሉ የተባሉት እውነቱን ራቁቱን አወጡትና ከእፍረት ነጻ ወጡ! እውነቱ ሲወጣ የሚያፍረው ማን ነው? ደካማዎቹና የግፍ ሰለባ የነበሩት በጭራሽ አያፍሩም፤ የሚያፍሩት ግፈኞቹ ናቸው፤ የሚያፍሩት የሕዝብን አደራ በማቆሸሻቸው፣ በሥልጣን በመባለጋቸው፣ የሕዝብንና የአገርን ክብር በማዋረዳቸው ያፍራሉ፤ ኅሊናቸው በየቀኑ ነፍሳቸውን አርባ ሲገርፋት እየሳሳች እንቅልፍ ትነሳቸዋለች፡፡


/ መስፍን ወልደ ማርያም

http://www.goolgule.com/let-the-truth-be-spoken/