Tuesday, March 27, 2018

“ባህር ዳር ላይ በግፍ የታሰሩ የአማራ ልጆች በአስቸኳይ ይፈቱ!”

ከመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት የተሰጠ መግለጫ
አማራን ማህበራዊ ደስታ እና ሰላም እንዳይኖረው አደርጋለሁ በማለት ምሎ ተገዝቶ የመጣው እብሪተኛው የወያኔ ትግሬ ፋሽሰት መንግስት በዘወትር አሽከሩ ብዓዴን አማካኝነት በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ከተማ ሰላማዊ ወጣት የአማራ ምሁራንን ወደ ማጎሪያ ስፍራ ወስዶ በማሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡ እነዚህ ምሁራን የታፈሱት በሰላማዊ መንገድ ተንቀሳቅሰው ለአማራ ህዝብ ነጻነት የሚታገል የፖለቲካ ድርጅት ለመመስረት ህጉ የሚጠይቀውን ሁሉ ሲያሟሉ ቆይተው፤ የቅድመ ምስረታ ጉባዔ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ዕቅድ ለመንደፍ ለእራት በተሰባሰቡበት ሰዓት ነው፡፡ በእንዲህ ያለ ሁኔታ የሚንቀሳቀሱ ዜጎች እንክብካቤ እንጅ እስራት እና እንግልት አይገባቸውም ነበር፡፡ ይሁን እንጅ ማንኛውንም ዓይነት የአማራን ህዝብ እንቅሰቃሴ በተመለከቱ ቁጥር አይናቸው ደም የሚለብሰው የስርዓቱ ቁንጮወች ይህ እንዲሆን ፈፅሞ አይፈልጉም፡፡ የአማራ ህዝብ ያለበት ነገር ሁሉ ያንገበግባቸዋል፡፡ ቅናት እና ፍርሃት በእጅጉ ያውኳቸዋል፡፡ ሞት ሞት ይሸታቸዋል፡፡
በተመሳሳይም ከወያኔው ማሰቃያ እስር ቤት በህይወት ተርፈው ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸውን አስመልክቶ የደስታ ጊዜ ለማሳለፍ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በእንድ ጓደኛቸው ቤት የተሰባሰቡ የነጻነት ታጋዮች በግፈኛው ስርዓት ማናለብኝነት እንደገና ለእስራት ተዳርገዋል፡፡ እነዚህም ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ የአማራ ልጆች ናቸው፡፡
አማራ ከሌሎች ጋር ተባብሮ ለመታገል ሲንቀሳቀስም ሆነ ለብቻው በአማራነቱ ለመደራጀት ሲፈልግ ዘረኛው ስርዓት ያለ የሌለ የአፈና ጉልበቱን በመጠቀም ዕንቁ የአማራ ልጆችን ሲገድል እና ሲያስር ብሎም በህጋዊ መንገድ የመሰረቱትን የፖለቲካ ድርጅት ሲነጥቅ እና ሲያፈርስ 27 ዓመት ሆኖታል፡፡ ይህ አይነት አካሄድ ከአሁን በኋላ በአማራ ላይ እንደማይሰራ ሊረዳ ያልቻለው ወያኔ መግቢያ ጉድጓዱን አርቆ በመቆፈር ላይ ይገኛል፡፡
ከላይ በተጠቀሰው ሁኔታ ባህር ዳር እና አዲስ አበባ ላይ የታሰሩ ሁሉም እስረኞች ያለምንም ቅደመ ሁኔታ በአስቸኳይ ይፈቱ፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን አድማ መምታትን ጨምሮ መጠነ ሰፊ እርምጃ እንዲወስድ መዐሕድ ለመላው የአማራ ህዝብ ጥሪ የሚያስተላልፍ መሆኑን አበክሮ ያስጠነቅቃል፡፡
ድል ለአማራ ህዝብ!
የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት (መዐሕድ)
http://www.satenaw.com/amharic/archives/53584

Wednesday, March 21, 2018

የኦሮሚያ ፍትህ ቢሮ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ “ሕዝብን የገደሉ ይጠየቁ” በማለታቸው ታሰሩ



ልበ ሙሉ፡ ደፋር፡ ጀግና፡ አንደበተ ርትዑ፡ የወገን ጥቃት የሚያመው፡ ትንታግ፡ ልበ ደንዳና ኦቦ ታዬ ደንደአ። የኦሮሚያ ክልል ፍትህ ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ሃላፊ ናቸው። በዚህ የጭንቅና የምጥ ወቅት የተገኙ ኮከብ በመሆናቸው ልናመሰግናቸው፡ ከጎናቸውም ልንቆም የሚገባን እንደሆነ ይሰማኛል። አቶ ታዬ በሁለት ቃለመጠይቆች ላይ ባሳዩት ፍጹም ድፍረትና የወገን ተቆርቋሪነት ነጥረው የወጡ የኢትዮጵያ ልጅ ናቸው። ዛሬ ጭራቆቹ እጅ ላይ ወድቀዋል።
የትግራዩ ገዢ ቡድን የለማን ኦህዴድ ለማዳከምና ለመሰባበር እንቅልፍ አጥቶ እያደረ ነው። የኦሮሚያን የወረዳ፡ የከተማና የዞን ባለስልጣናትን በማሰር የጀመረው እንቅስቃሴ ወደላይ ከፍ ብሎ የካቢኒ አባላት ጋ ደርሷል። አቶ ታዬ የትግራዩን ገዢ ቡድን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ለህዝባቸው ያላቸውን ፍጹም ተቆርቋሪነት በማሳየታቸው በኮማንድ ፖስቱ መታሰራቸው ታውቋል። በተለይ ሰሞኑን በሞያሌ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ ”በስህተት” በሚል መገለጹን ተከትሎ አደባባይ በመውጣት ”ስህተት አይደለም፡ ግልጽ የጦር ወንጀል ነው። የመከላከያም ሆነ የኮማንድ ፖስቱ አዛዦች በህግ ሊጠየቁ ይገባል” ማለታቸው በትግራዩ ገዢ ቡድን ሰፈር ጸጉር እስኪነቀል ያበሳጨ መሆኑ ተሰምቷል።
ከዚህ ቀደምም የትግራዩ ገዢ ቡድን ቄሮዎች ላይ ምርመራ ጀምሬአለሁ ያለ ሰሞን ሚዲያ ላይ ወጥተው ”ምን አገባህ” በማለት ምላሽ መስጠታቸው ከህዝብ ከፍተኛ ከበሬታን እንዲያገኙ አድርጓቸዋል። ከትግራዩ ገዢ ቡድን ደግሞ ጥርስ አስነክሶባቸዋል። እሳቸው ብቻ አይደሉም። የአምቦ ከተማ ፖሊስ አዛዥ፡ የሞያሌ ከተማ ከንቲባ፡ ሌሎችም የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት እያሳዩ ያሉት የህዝብ ወገንተኝነት በደማቁ የሚነሳ ነው። ከትግራዩ ገዢ ቡድን ዱላ ይልቅ የህዝባቸው ቁጣ የሚያስፈራቸው ናቸው። መንገዳቸውን መርጠዋል። ዘላቂ ጉዞ ከህዝብ ጋር እንጂ ከሚያልፍ ስርዓት ጋር እንዳልሆነ አውቀውታል። ካወቁ አይፈረድባቸውም። ለምንስ ይቀጣሉ? እየሰጠመ ካለ መርከብ ዘንድ ምን አላቸው? ቄሮን የመስለ መከታና ጋሻ እያላቸው ? ?
የትግራዩ ገዢ ቡድን ዙሩን ማክረር ፈልጓል። ለህዝብ የሚበጀው፡ ለሀገር የሚጠቅመው እንዲህ ዓይነቱ በትዕቢትና ድንቁርና የሚነዳ አመራር አልነበረም። ድምሩ ዜሮ የሆነ፡ አጥፍቶ መጥፋት መስመር ላይ የቆመ አካሄድ አወዳድቅን አጉልና ዘግናኝ ከማድረግ ውጪ የህዝብን የነጻነት ተጋድሎ አይቀለብሰውም። የአቶ ታዬ ደንደአ እስር ህዝብን ለቁጣ የሚፈነቅል ተጨማሪ ምክንያት እንጂ ወደ ቤቱ የሚያስገባ፡ በፍርሃት ተሸብቦ አንገቱን ደፍቶ እጅ የሚያሰጠው አይሆንም።
ሺ ታዬዎች ተፈጥረዋል። ሚሊየን ለማዎች በቅለዋል። ለትግራዩ ገዢ ቡድን የደንቆሮ ለቅሶ መልሶ መላልሶ ሆኖበት እንጂ ለነጻነት የቆመን የህዝብ ልብ ወደ ኋላ የሚመልሰው ምንም ዓይነት ምድራዊ ሃይል የለም። ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ ይባላል። የትግራዩ ገዢ ቡድን ከዚህ በኋላ የራሱን መጨረሻ የማሳመር ሃላፊነቱ የራሱ ብቻ ነው። አወዳደቁ አጉል እንዳይሆን ነገሮችን የማለስለስ ስራ እንጂ እንዲህ ማጦዝ ከማንም በላይ የሚጎዳው ራሱኑ ነው።
ትላንት ዛሬ አይደለም!!!!
https://ecadforum.com/Amharic/archives/18716/

Sunday, March 18, 2018

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሰላማዊ ዜጎችን መግደል እንዲቆም ጠየቁ

ከእስር በቅርቡ የተፈቱት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ወልዲያ ናቸው።  የጉዟቸው ምክንያት ደግሞ ልጆቻቸው በመንግሥት ታጣቂዎች የተገደሉባቸውን ቤተሰቦች ለማፅናናት እንደሆነና በዚህም “መንግሥት ሰላማዊ ዜጎችን ተኩሶ ሊገል አይገባም” የሚል መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ እንደሆነ ለባልደረባችን ለመለስካቸው አምሃ ነግረውታል።መለስካቸው ከአዲስ አበባ ደውሎ ሦስቱንም እንዲሁም አብረዋቸው ያሉትን የ13 ዓመት ዕድሜ ልጃቸው ዮሴፍ እሸቱ የተገደለባቸውን አባት አቶ እሸቱ ጀመረን አነጋግሯል።
 VOA Amharic
http://www.satenaw.com/amharic/archives/53041

Saturday, March 17, 2018

ወደ ኬንያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ሊጨምር ይችላል ተባለ

ባለፈው ሣምንት ቅዳሜ በቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ የመከላከያ ሠራዊት በነዋሪዎች ላይ የፈጸመው ግድያ በየአቅጣጫው ቁጣን ቀስቅሷል። የኮማንድ ፖስቱ ድርጊቱ በተሳሳተ መረጃ ምክንያት የተከሰተ መሆኑን ቢገልፅም የመከላከያ ኃይሉ ጥቃት ሆን ተብሎ የተፈጸመ የወንጀል ድርጊት እንደኾነ የገለጡ አሉ


ከኢትዮጵያ ተጨማሪ ዜጎች ወደ ኬንያ ሊሰደዱ እንደሚችሉ የዓለም የምግብ መርኃ-ግብር (WFP) ሥጋቱን ገለጸ። የድርጅቱ የኬንያ ጽ/ቤት ቃል አቀባይ ፒተር ስሜርዶን ተፈናቃዮችን በተመለከተ ሲናገሩ፦ «በኢትዮጵያ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት ምናልባት ቁጥራቸው ሊጨምር ይችላል ብለን እንጠብቃለን» ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። ወደ ኬንያ የተሰደዱት ኢትዮጵያውያን «አሁን ቁጥራቸው ከ9, 600 በላይ ናቸው ተብሎ ይገመታል» ያሉት ስሜርዶን አብዛኞቹ ሴቶች እና ሕፃናት መሆናቸውን ገልጸዋል። ከትናንት ጀምሮም የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት እና የዓለም የምግብ መርኃ-ግብርን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ወደ ኬንያ የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ለመርዳት ሁኔታውን እያጠኑ መሆኑን ለዶይቼ ቬለ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ የተሰደዱ ዜጎችን ለመመለስ «ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ»መሆኑን ገልጿል። የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አሰፋ አብዩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ «ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚመለከታቸው ከክልልና ከፌድራል መንግሥት ከአካባቢ አስተዳደር ቡድን ተዋቅሮ ወደ ቦታው ሔዷል። ሕብረተሰቡን የማረጋጋት ሥራ እየተሰራ ነው። የተጎዱ ቤተሰቦችን የመደገፍ ሥራ እየተሰራ ነው። የተፈናቀሉ እና ወደ ኬንያ ድንበር የሔዱ ዜጎቻችንን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው» ሲሉ ተናግረዋል።
http://www.dw.com/am/%E1%8B%88%E1%8B%B0-%E1%8A%AC%E1%8A%95%E1%8B%AB-%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%88%B0%E1%8B%B0%E1%8B%B1-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%E1%8B%8D%E1%8B%AB%E1%8A%95-%E1%89%81%E1%8C%A5%E1%88%AD-%E1%88%8A%E1%8C%A8%E1%88%9D%E1%88%AD-%E1%8B%AD%E1%89%BD%E1%88%8B%E1%88%8D-%E1%89%B0%E1%89%A3%E1%88%88/a-43025309

‘Ethiopian police killed hundreds of protesters’