Thursday, October 29, 2015

በአማራው ስም የሕወሓት ተላላኪ የሆኑ ሆዳም የብአዴን አመራሮች በአማሮች ላይ የሠሯቸው 14 እርጉም ግፎች

ተላላኪው ም/ል ጠቅላይ ሚ/ር እና የኢሕአዴግ ሊቀመንበር ም/ል ደመቀ መኮንን; ሕወሓት የሚሳደበው አንሶ የአማራውን ሕዝብ                ከተሳደቡት አቶ አለምነህ መኮንንና ከተላላኪ የአማራ የጦር መኮንኖች ጋር::

በትናንትናው እለት የብአዴን ምክትል ሊቀመንበርና የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ቃለምልልስ ሲያደርጉ ተከታተልሁ:: ርእሰ መስተዳድሩ ባንድ ወቅት “አማራ የራሱን የጦር ጀኔራል መርጦ ህዝቡን እያስታጠቀ ነው” በሚል በትግራዩ ገዥ አቶ አባይ ወልዱ ለቀረበባቸው ክስ “አዎ ለክልሌ ጀኔራል ነኝ” ብለው መልስ ሰጡ የሚል ጽሁፍ አንብቤ ስለነበር ልቤ በኩራት እብጥ ብሎ ክብር ሰጥቻቸው ነበር:: በአማራው ላይ የሚደርሰው ዘርፈ ብዙ ጥቃት ያበቃ ዘንድ በብአዴን ውስጥ ያሉት አማሮች በቁጭት “በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በቃ!”ብለው ተነስተዋል ማለት ነው ብየ ገምቸ ነበር:: ምንም ቢሆን ልጅ የወላጆቹን ባህሪ መውረሱ አይቀርም: ይኸው የብአዴን አማሮች ያባቶቻቸውን ወኔ ተላበሱ ብየ በደስታ የምሆነውን አጥቸ ነበር:: ይሁንና ሰውየው በሰሞኑ ያደረጉት ቃለመጠይቅ ላይ ብአዴን የአማራ ህዝብ የዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቹ ተከብረው ከሌሎቹ ወገኖቹ ጋር በእኩልነት እንዲኖር ከትምክህተኞችና ከጠባቦች ጋር ብዙ ትግል እንዳደረገና ውጤት እንዳስገኘ ሲገልጹ ሰማሁና ከልብ አዘንሁ:: አቶ ገዱ እናንተ የምታወሩትን ወይስ ምድር ላይ የሚታየውን እንመን? እንደእኔ እምነት የአማራ ህዝብ መቸም ቢሆን ያላገጠመውን ፈተና በናንተ ጊዜ እየተፈተነ ነው:: አማራ ተኮር የሆነ ጭፍጨፋ የተፈጸመውና ህዝባችን አጎንብሶ እንዲኖር የተደረገው በናንተ ጊዜ ነው:: ይህ ሁሉ መከራ በአማራው ላይ ሲፈጸም “ለምን እንዲህ ይሆናል” ብላችሁ ለመሟገት የሚያስችል እንጥፍጣፊ ወኔ የላችሁም:: እንዲያውም ድርጅታችሁ በተላላኪነት ተግባር ተሰማርቶ ግፍ አንገፈገፈን ብለው ተቃውሞ ያሰሙትን ወገኖች አሳዶ በመምታት የወያኔ አፋኝ ስኳድ ሆኖ እየሰራ ያለ ድርጅት እንደሆነ ህዝባችን አሳምሮ ያውቃል:: “የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ” ነውና እስቲ በኢህአዴግ ጊዜ በአማሮች ላይ የተፈጸመውን ግፍና የናንተን አቋም በጥቂቱ እናስታውሳችሁ:-

1. በደርግ የመጨረሻ ዘመን አሶሳ ላይ አማሮች ብቻ ተለይተው ሲታረዱና በእሳት ሲቃጠሉ ድርጅታችሁ አንድም ተቃውሞ አላሰማም::

2. የናንተን ድርጅት ያካተተው ኢህአዴግ መላ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ አማሮች እየተለቀሙ ከነነፍሳቸው በገደል ሲጣሉ:በገጀራ ሲታረዱ: በእሳት ሲቃጠሉ ድርጅታችሁ የወገንተኝነት ስሜት ተሰምቶት “ለምን ምንም ያላጠፉ ሰዎች አማራ በመሆናቸው ብቻ እንዲህ አይነት ግፍ ይፈጸምባቸዋል?” ብሎ በመቆርቆር እወክለዋለሁ የሚለውን ህዝብ መብት ለማስከበር ሲንቀሳቀስ አልታየም:: እንዲያውም ያሁኑ ፓስተር የያኔው የድርጅታችሁ ሊቀመንበር ታምራት ላይኔ በጅጅጋ ተገኝቶ በሶማሊያ ክልል በሚኖሩት አማሮች ላይ የሶማሌ መንግስትና ህዝብ እርምጃ እንዲወስዱባቸው በመቀስቀስ ድርጅታችሁ ጸረ አማራ መሆኑን እናንተም የጠላት ሀይል አንድ ክንፍ መሆናችሁን አስመስክሯል::

3. ከንጉስ ኃይለስላሴ ጊዜ ጀምሮ ለብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበር: ለሰው ልጅ እኩልነትና ነጻነት እልህ አስጨራሽ ትግል ሲያደርጉ ከነበሩትና መስዋእትነት ክከፈሉት ሰወች መሀል የአማሮች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም:: ይሁንና በነገስታቱና በደርግ ጊዜ በኤርትራ ላይ ተፈጽሟል ለተባለው ወንጀል አማሮችን ቀጥተኛ ተጠያቂ በማድረግ አስመራ ድረስ ሄደው “ማሩን” ብለው ከሻእቢያ እግር ላይ ወድቀው ይቅርታ እንዲለምኑ ሲደረግ “ለምን እንዲህ ይሆናል? ባለፉት ስርአቶች በገዥነት የተቀመጡ አማሮች ብቻ አልነበሩም: ታዲያ እንዴት አማራው ብቻ ይቅርታ ጠይቅ ይባላል?” ብላችሁ ለህዝባችሁ መብትና ክብር ያሰማችሁት ተቃውሞ አልነበረም::

4. አማራ ከየክልሉ ሀብት ንብረቱን ጥሎ የሞተው ሞቶ ማምለጥ የቻለው እግሩ ወዳመራው ሲሰደድ “አይደለም ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ ሀገር ውስጥ የሚኖር አማራ ካላግባብ ሀብት ንብረቱን ሊነጠቅ: ህይወቱን ሊያጣ አይገባም” ብላችሁ ስትከራከሩ አልተሰማችሁም:: ይባስ ብሎ የድርጅታችሁ የወቅቱ ሊቀመንበር አቶ አዲሱ ለገሰ ከኦሮሚያ የተባረሩትን አማሮች በተመለከተ ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱ የተባረሩት ሰዎች አጭበርባሪወችና ዘራፊወች ናቸው ነበር ያሉት:: የአማራ ሰዎች እንደዚያ በጅምላ ከየክልሎች አላግባብ እንዲፈናቀሉ ሲደረግ በአማራ ክልል ግን የሌሎች ክልሎች ተወላጆች በድርጅታችሁ ታቅፈውና ሹመኛ ሆነው በአማሮች ላይ እየፈረዱና ሀብቱን እየመዘበሩ በማናለብኝነት ቀጥለዋል:: ለዚህስ የምትሰጡት መልስ ምንድን ነው? የሚገርመው ደግሞ የአማራን ህዝብ ጥንብ እርኩሱን አውጥቶ ያዋረደው የክልሉ ተወላጅ አቶ አለምነው መኮንንን ህዝብን ያህል ነገር እንዴት እንዲህ ታረክሳለህ ተብሎ ሊጠየቅ ሲገባ እርስዎን ጨምሮ ሌሎች የድርጅቱ አባላት ባንድ ላይ ሰውየው የህዝብ ተቆርቋሪ እንደሆነና የተወራበት ሁሉ የጠላት ወሬ እንደሆነ ልታሳምኑን ስትደክሙ ሰምተን እጅግ አዝነናል:: በህዝብ ላይ ያን ያልተገረዘ የባለጌ መላሱን ያስረዘመውን ስድ አደግ ሰው ልትቀጡ ወይም ልትገስጹ ሲገባ ከህዝብ በላይ አድርጋችሁ በማየት የተገላቢጦሽ ለህዝብ የተቆረቆሩትን ሰዎች ወረፋችሁ::

5. በአማራ ክልል የሚኖሩ ብሄረሰቦች በዞን ተደራጅተው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ ሲደረግ አማሮች በብዛት በሚገኙባቸው ሌሎች ክልሎች ግን ይህ እድል አልተሰጠም: ሌላው ቀርቶ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን እንኳ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ ዕድሉን አላገኙም:: ታዲያ እናንተ የታዘዛችሁትን ከመፈጸም አልፋችሁ እንዲህ የተዛነፈ አሰራር ሲታይ ምን ያደረጋችሁት ነገር አለ?

6. የአዊ ዞን ልጆቻቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአማረኛ እንዲማሩ ተስማምተው ያሳለፉትን ውሳኔ ከበላይ የመጣ ትእዛዝ ነው በሚል የብሄሩን መብት ገፍፋችሁ አዊወች በአዊኛ እንዲማሩ አደረጋችሁ: ይህን ውሳኔውን ያሳለፉትን ሰዎችም “የመንግስትን ፖሊሲ ተቃርነው የቆሙ” በማለት ፈርጃችሁ ከስራ እስከማባረር ድረስ የደረሰ ቅጣት ቀጣችኋቸው::


7. ለሱዳን ሊሰጥ በታሰበው መሬት ላይ የህዝብ ቁጣ ሲባባስ “የምንሰጠው መሬት የለም: ከሌላ የወሰድነውም የለም:: የራሳችን የሆነውን አንሰጥም የሌላውንም አንፈልግም” ብለው ነበር:: ይሁንና በተጨባጭ ከመተማና ካካባቢው በሱዳን ወታደሮች በሀይል እንደተፈናቀሉ ተፈናቃዮቹ አዲሳበባ ድረስ በአካል ተገኝተው ለፓርላማው አቤቱታ ማቅረባቸው በተጨማሪም ለአሜሪካው የአማረኛ ሬዲዮ ስርጭት (VOA) ቃለምልልስ መስጠታቸው አይዘነጋም:: አቶ መለስ ይህንን አስመልክቶ ከፓርላማው ለቀረባቸው ጥያቄ ሲመልሱ “አንድም ሰው አልተፈናቀለም” ብለው ሙልጭ አድርገው 
ዋሽተው ነበር:: እርስወም ድንበሩን በተመለከተ ለቀረበልወት ጥያቄ ከአቶ መለስ የተለየ መልስ አይደለም የሰጡት::

8. ከ10 አመት በፊት በተደረገው የህዝብ ቆጠራ ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ በአዲስአበባና በአማራ ክልል ብቻ ፕሮጀክት ከተደረገው ቁጥር በእጅጉ ማነሱ ይታወቃል:: በአዲስ አበባ ከሚኖረው ህዝብ መሀል እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው አማራው መሆኑን ያጡታል ብየ አላስብም:: ታዲያ ይህ የአማሮች በ2.5 ሚሊዮን ቁጥር መቀነስ መላው ፍትህ ወዳድ ኢትዮጵያዊያንን በንዴት ሲያርገፈገፋቸው ብአዴን ግን አንድም ሰው እንዳልጎደለበት ሆኖ ማስተባበያ በአቶ አዲሱ ለገሰ በኩል ሲሰጥ ነበር::
9. በአማራ ክልል ላይ ብቻ ያተኮረ በቤተሰብ ዕቅድ ስም እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል በወያኔ ተቀርጾ በናንተ የሚፈጸም አስነዋሪ ተግባር ነው:: የቤተሰብ ብዛትን መመጠን በሚል ምክንያት በአማራ ክልል ህዝብ ላይ ብቻ ያተኮረ የሴቶችን ማህጸን መቋጠር: የወንዶችን የዘር ፍሬ ማኮላሸት የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው:: አሁን ደግሞ ስልቱ ተቀይሮ የአማራ ሴቶችን የበሽታ መከላከያ ክትባት በማስመሰል መሀን የሚያደርግ መድሀኒት እንዲከተቡ ሲደረግ ብአዴን የወያኔን አላማ ለማስፈጸም ቀዳሚ ሆኖ የተሰለፈ ቡድን ነው::

10. አማሮችን ትጥቅ አስፈቱ የሚል መመሪያ በወረደላችሁ ጊዜ ምን ያህል ግፍ እንደፈጸማችሁ ትዝ ብሏችሁ ያውቃል? ወያኔ ይህን መመሪያ ሲያስተላልፍ ምክንያት እየፈጠረ አማሮችን ለመበቀል ካለው ፍላጎት በመነሳት ነበር:: ይህን ለማድረግ ደግሞ በራሱ ሰዎች ሳይሆን ህዝቡን እንወክለዋለን በምትሉት በናንተ ቢፈጸም ከተጠያቂነት ነጻ እንደሚሆን አሰበና “ህገወጥ መሳሪያ ታጣቂወችን መሳሪያቸውን እንዲያስገቡ አድርጉ” ሲል ትዕዛዝ ሰጣችሁ:: ይህን የበላይ ትእዛዝ ለማስፈጸም ነበር መሳሪያ ያልነበረውን ሳይቀር አስራችሁ የገረፋችሁት ብሎም የገደላችሁት:: የናንተ ህዝባዊነት መገለጫ የሰውን ክብር ገፋችሁ አባቶችን ሳይቀር ማሰቃየት ነው?

11. ለመሆኑ ቁልፍ በተባሉት የወታደራዊና የሲቭል ተቋማት ውስጥ የአማሮች ድርሻ ምን ያህል ነው? ይህስ አሳስቧችሁ ያውቃል? ወያኔ ገንዘብ የሚታፈስባቸውንና ስልጣንን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ተቋማትን ተቆጣጥሮ በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ያገር ሀብት ዘርፎ ከሀገር ሲያስወጣ ምን ያደረጋችሁት ነገር አለ? የሀገር ሀብት ለሁሉም ክልሎች እንጅ ለአንድ ቡድን ብቻ አገልግሎት እንዳይሰጥ ለማድረግ የሰራችሁት ስራስ ምን አለ?

12. የብድርና የቁጠባ ወይም የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አገልግሎት ለሁሉም አማራ ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ነው የምታከፋፍሉት? አገልግሎት ማግኘት የህዝብ መብት ነው:: እናንተ በአመራር ላይ የተቀመጣችሁ አገልግሎት ለማግኘት ሳይሆን ያለአድልዖ አገልግሎት ለመስጠት ነው:: ግን እናንተ በተግባር እያደረጋችሁ ያላችሁት ምንድን ነው? የአማራው ህዝብ በሙሉ እንደናንተ ፍጹም የወያኔ ሎሌ ሆኖ የታዘዘውን እንዲፈጽም: ሲገድሉት እንዲሞት ለማድረግ ስንት ግፍ ሰራችሁ? ጠላትና ወዳጅ በማለት ከፍላችሁ እንደናንተ ሊሆን ያልፈቀደውን ሰላማዊ ዜጋ በተለያየ መንገድ አላሰቃያችሁም?

13. ህዝቡ የፖለቲካ አማራጭ የማግኘት መብቱ በህገመንግስቱ የተጠበቀ ነው:: ይህንን የህዝብ መብት አክብራችሁ ህዝቡ በመረጠው እንዲተዳደር ምን አድርጋችኋል? በግድ ውጣ ተብሎ እንዲመርጥ የተደረገን ህዝብ ምርጫውን ነፍጋችሁ እጅ እጅ በሚል ውሸት እኛ ተመረጥን ስትሉ የብዙሀኑን መብት የነፈጋችሁና በህዝብ ላይ በጉልበት የነገሳችሁ አምባገነኖች እንደሆናችሁ አስተውላችሁት ታውቃላችሁ? መቸ ነው ወደህሊናችሁ የምትመለሱት?

14. ክልሎች ታሪክ እየጠቀሱ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ ሲያነሱ የአማራ ክልል ግን በግላጭ በታሪክ የሚታወቀውን መሬቱን ማስከበር አልቻለም:: አንዳንድ የዋህ ሰዎች በአንድነት እስከኖርን ድረስ አንድ አካባቢ በዚህ ወይም በዚያ ክልል ቢካተት ችግር የለውም ሲሉ ይደመጣሉ:: እንደእኔ ከሆነ ይህ አባባል ፍጹም ስህተት ነው:: የመገንጠል መብት በተከበረበት ሀገር ትክክለኛ የራስን መሬት ሳይዙ ህገመንግስቱን ማጽደቅ አደጋው ቀላል አይደለም:: ዛሬ እየኖርን ያለነው አንድነቷ በተጠበቀ ሀገር ውስጥ አይደለም:: ህገመንግስቱም ቢሆን በአንድነት ለመቀጠላችን ዋስትና የሚሰጥ አይደለም:: የፈለገውን ማድረግ እየቻለ ያለው ወያኔ የተፈራረምንበትን ህገመንግስት መሰረት በማድረግ ነገ ብድግ ብሎ ለመገንጠል ወስኛለሁ ቢል በምን ነው ልንከላከል የምንችለው? የክልል መንግስታት ተፈራርመው ያጸደቁት ህገመንግስት በአለም አቀፍ መድረክ ተቀባይነት የማይኖረው ይመስላችኋል? በርግጥ በአሁኑ ጊዜ ከትግራይ ውጪ ያሉት ክልሎች መገንጠል እንፈልጋለን የማለት ድፍረቱ አይኖራቸውም: ድፍረቱ ቢኖራቸው እንኳ ወያኔ ጥያቄውን ለማዳፈንና ጥያቄ አቅራቢወችን ለመበቀል የሚሄድበት መንገድ አያጣም:: ነገር ግን የወያኔ ፈቃድ ሆኖ ክልሎች እንዲገነጣጠሉ ቢያደርግ ታሪካዊ መሬታችን ነው የምንለውን አካባቢ እንዴት ነው ማስመለስ የምንችለው? የአማራ ክልል ለመሆኑ ታሪካዊ መኖሪያ አካባቢው የቱ ነው? ይህ ጥያቄ ከተመለሰ በኋላ ነበር ህገመንግስቱ ቢፈረምም መፈረም የነበረበት:: ድርጅታችሁ አላግባብ የተወሰደበትን መሬት ለማስመለስ ያደረገው ምን ነገር አለ? “አማራ ነን:: ያላግባብ ወደትግራይ ክልል እንድንካተት ተደርገናል” እያሉ ለሚጮሁት የወልቃይት ወገኖቻችንስ ምን አደረጋችሁ? ታዲያ ለአማራው ህዝብ መብትና እኩልነት ያደረጋችሁት የሚያስፎክር ትግል የት አለ!

በርግጥ ማንም አሌ የማይለው ነገር ቢኖር አማራው ሀገሩ ኢትዮጵያ መሆኗን ነው: የኖረውም የሀገሪቱን ዳር ድንበር ለማስከበር: ሰላምና ጸጥታ ለማስፈን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢወች ነው:: ይህችን ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አስከብሮ ለእኛ ያስረከበ ህዝብ እንደጠላት እየታደነ ሲገደል አባሪ ከመሆን ውጭ ለክልሉና ለህዝቡ ያበረከታችሁት አንድም አኩሪ ስራ የለም:: እናንተ የአማራውን ህዝብ የምታኮሩ ሳትሆኑ የምታሳፍሩ: የምታስከብሩ ሳትሆኑ የምታዋርዱ ሙሉ ትኩረታችሁን በሰፈር እየተደራጃችሁ ስልጣን ለመያዝ በርስ በርስ ሽኩቻ ጊዜአችሁን የምታባክኑ እንጥፍጣፊ ህዝባዊ ስሜት የሌላችሁ የምትገርሙ ሰዎች ናችሁ:: አይናችሁን ጨፍናችሁ በምትዋሹት ውሸት የአማራው ህዝብ አምኖ ይቀበለናል ብላችሁ አስባችሁ ከሆነ ተሳስታችኋል:: ብታምኑም ባታምኑም ህዝቡ እናንተን ህሊና የሚባል ነገር የሌላችሁ የወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚ ሮቦቶች እንደሆናችሁ አድርጎ ነው የሚያያችሁ:: ወያኔም ቢሆን በፈለገው መንገድ ሊያሰልፋችሁ የሚችል ጅሎች አድርጎ እንደሚያያችሁና እንደሚታዘባችሁ አንጠራጠርም::

ሰሞኑን አቶ ኃይለማርያም ከፓርላማ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ የዶ/ር ደብረጽዮንን ስሜት ሳትገነዘቡ የቀራችሁ አይመስለኝም:: መቸም ኃይለማርያም ከራሳቸው የፈለቀች አንዲትም ቃል ሊናገሩ ድፍረት ይኖራቸዋል ተብሎ አይታሰብም:: ታዲያ ለሚቀርብላቸው ጥያቄ በወያኔ ተዘጋጅቶ የተሰጣቸውን መልስ ሸምድደው ገብተው “መንግሥታችን ርምጃ ይወስዳል…” ምናምን ሲሉ ዶክተሩ ስሜታቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው የፌዝ ፈገግታ ሲያሳዩ ነበር:: ዶ/ር ደብረጽዮን “ነገ ቃላችንን አጥፈን ተቃራኒውን ለማድረግ ብንወስንና ይህንን ባደባባይ ተናገር ብንለው ያው እንደለመደው መንግስታችን እንዲህ ያደርጋል እያለ መናገሩ አይቀርም:: የነዚህ ሰዎች ሰውነት ከምኑ ላይ ነው?” የሚል አይነት የግርምት ፈገግታ ነበር ሲያሳዩ የነበሩት:: ወያኔ እንዲህ የሚያሾፈው በሁላችሁም ላይ ነው::


አማራን የሚያህል ትልቅና ታሪካዊ ህዝብ እንወክላለን ብላችሁ ግን ለውርደትና ለእልቂት ስትዳርጉት: ለዚህ ውለታችሁ የሚሰጣችሁ ክፍያ በአናሳው ቡድን እንዲህ መሳቂያ መሳለቂያ መሆን ከሆነ ምን አይነት ህሊና ቢኖራችሁ ነው አሜን ብላችሁ ተሸክማችኋቸው የምትኖሩት:: “አማራ ሆዳም ነው” እንደሚሉን እናውቃለን:: የህዝብ ክብርና ነጻነት ከምንም በላይ አይደለም እንዴ! ባትበሉት ባትጠጡት ባፍንጫችሁ ቢወጣ ምን ነበረበት::

እስከቀበሌ ድረስ በዘለቀው አደረጃጀታችሁ ተጠቅማችሁ “መላው የአማራ ህዝብ ሆይ ደምና አጥንት ከፍለህ ባስከበርሀት ሀገር ላይ መኖር ተከልክለህ ዘርፈ ብዙ ግፍ እየተፈጸምብህ ስለሆነ ይህንን ባንተ ላይ ያነጣጠረ ሰቆቃ ለማስወገድ ከጎናችን ተሰልፈህ መብትህን እንድታስከብር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን::” የሚል አዋጅ ብታስነግሩ አማራው “ሆ” ብሎ ተነስቶ የተበላሸውን ለማስተካከል ጊዜ ይፈጅበት ነበር!

ለነገሩ ወያኔ ከራሱ ክልል ውጪ ላሉት ክልሎች ባለስልጣናትን ሲያስቀምጥ በተጠና መንገድ ሆድ እንጅ ህሊና የሌላቸውን ስለህዝብና ስለሀገር ደንታ ቢሶችን መርጦ ነው:: ለዚያም ነው አማራው ከያለበት እየተያዘ ግፍ ሲፈጸምበት አንድም ተቃውሞ ያላሰማችሁት! እናንተም ብትሆኑ አፋችሁ ያውራ እንጅ ለህዝብ ቀርቶ ለራሳችሁ እንደማትሆኑ ልባችሁ አሳምሮ ያውቃል:: ሙሉአለም ሲገደል ምን አደረጋችሁ? ታምራት ላይኔ በአደባባይ “በትግል ያልተሸነፈ ሰው በስኳር ተሸንፎ እጁን ሰጠ” ተብሎ ሲቀለድበት: ራሱን አዋርዶ “ቢመክሩኝ አልሰማ ብየ” ብሎ ቀበጣጥሮ ይቅርታ እንኳ ተነፍጎት ወህኒ ሲወርድ ከማጨብጨብ ውጪ ምን ሰራችሁ? ለነገሩ እንደፖለቲከኛ ሳይሆን እንደሆደ ቡቡ ህጻን በፍርሀት የቀባጠረ ሰው ሲመራው ከነበረ ድርጅት ምን ይጠበቃል?


የጊዜ ጉዳይ ነው እንጅ እናንተም ሆናችሁ ጌቶቻችሁ ከፍርድ አታመልጡም: የውሻን ደም ከንቱ የማያስቀር ግፍን የሚቆጥር አምላክ አለ:: እስከዚያው ድረስ እናንተ ስልጣን ላይ ተቀምጣችሁ ለምታገኙት ፍርፋሪ አማራውን ረግጣችሁ እንድትይዙ የእድል በር የከፈተላችሁን የልደት ቀናችሁን በፌስታ ስታከብሩ እኛ ደግሞ ያችን የተረገመች ቀን በሀዘን እናስታውሳታለን:: መቸም ከአንጎል ክፍላችሁ የሆነ የጎደለ ነገር አለ መሰለኝ ጸጸትና ቁጭት ይሰማችኋል ብየ አላምንም:: የህዝብን አስተያየት በግብአትነት ተጠቅማችሁ ራሳችሁን ወደውስጥ አይታችሁ ስህተታችሁን ለማረም ከመሞከር ይልቅ የሚተቿችሁን ለማጥፋት የምትተጉ እንደሆናችሁ ግን እናውቃለን:: እስካሁን በሰራችሁት ስራ ክብር ያገኛችሁ መስሏችሁ ከሆነ ተሳስታችኋል:: እና ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር ነውና በስራችሁ ከማፈርና ከማዘን አልፈን ምነው ሳትወለዱ በናታችሁ ማህጸን ውስጥ ውሀ ሆናችሁ በቀራችሁ ነበር ብለን ድርጅታችሁ የተወለደበትን ቀን ብቻ ሳይሆን እናንተ የብአዴን ሰዎች እራሳችሁ የየተወለዳችሁበትን ቀን ሳይቀር እረግመናል::

 http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47815

Wednesday, October 28, 2015

በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት አለ” የሚለው ተረት ተረት ነው ሲሉ ዶ/ር መረራ ጉዲና ገለጹ


ጥቅምት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሞ ፌደራሊስት ሊቀመንበር እና የመድረክ የአመራር አባል የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና ይህን ምላሽ የሰጡት ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀረበውን የውይይት ግብዣ ተቃዋሚዎች ውድቅ ማድረጋቸውን ለፓርላማ አባላት መናገራቸውን ተከትሎ ነው።

መንግስት በጠራው የአምስት ኣመታት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውይይት ላይ ያልተሳተፉ እንደመድረክ፣ ሰማያዊ እና መኢአድ ያሉ ፓርቲዎች ያቀረቡት ምክንያት ውሃ ያማያነሳ ነው ያሉት አቶ ሃይለማርያም ፣ ፓርቲዎቹ ያልተሳተፉት በሕጋዊ መንገድ የተመረጠ መንግስት አይደለም በማለት መሆኑን ጠቅሰው ወደፊት ከየትኛው መንግስት ጋር እንደሚወያዩ እናያለን ሲሉ ዝተዋል፡፡

ዶ/ር መረራ ሲናገሩ፣ “በቅድሚያ አንነጋገርም አላልንም፣ ቅድሚያ መሰረታዊ በሆኑት የአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ለምሳሌ ነጻ ምርጫን ፣ ነጻ ሚዲያን፣ በነጻነት መንቀሳቀስንንና በመሳሰሉት መሰረታዊ መብቶች ጉዳይ እንነጋገር ” ነው ያለው ካሉ በሁዋላ፣ እነሱ በሚሉት ጉዳይ ላይ ለመነጋገርም ፣ በር ዘግቶ ሳይሆን፣ በነጻ ሜዳ፣ ለህዝብ በቀጥታ በሚተላለፍ መልኩ መሆን አለበት በማለት በጽሁፍ መግለጻቸውን ተናግረዋል።

መድረኩን ተጠቅማችሁ ለምን ሃሳባችሁን ለማስተላለፍ አልቻላችሁም በሚል ለተጠየቁት ዶ/ር መረራ፣ የኢህአዴግ ፖሊሲ ስልጣን ወይም ሞት በመሆኑ፣ የልጅ ስራ መጫወቱ ትርጉም የለውም ብለዋል።

አገሪቱ አደጋ ውስጥ ናት ያሉት ዶ/ር መረራ ዲሞክራሲው የፖለቲካ ቅርቃር ውስጥ መግባቱን፣ አገሪቱ ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እያመራች መሆኑዋንና የሚባለው ዲሞክራሲ፣ ሰላምና መረጋጋት አለመኖሩን እንዲሁም ረሃብና ድህነት ታሪክ ሆኗል የሚባለውም ተረት ነው በማለት ገልጸዋል።

http://www.satenaw.com/amharic/archives/10863

Monday, October 26, 2015

በጎንደር ከተማ 6 የፖሊስ አባላት ላይ ጥቃት ተፈፀመ፡፡

ባለፈው አርብ ዕለት ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው የጎንደር ከተማ ፖሊስ አባላት የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋይ የሆነውን አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክሩ አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመ በታጠቀው ኮልት ሽጉጥ ተኩስ ከፍቶ 6 ፖሊሶችን መትቶ መሬት ላይ አጋድሟቸዋል፡፡

ጀግናው አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመ ከጎንደር ከተማ እምብርት ፒያሳ ጀምሮ እጁን ሊይዙ የተከታተሉትን ፖሊሶች ቀበሌ 6 ቂርቆስ አካባቢ እስኪደርስ “አትቅረቡኝ! ብትመለሱ ይሻላችኋል…” እያለ የለመናቸው ሲሆን ነገር ግን ፖሊሶቹ ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ባለመቻላቸው ቆራጥ እና የማያዳግም እርምጃ ወስዷል፡፡

ጀግናው አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመ በያዘው ኮልት ሽጉጥ አንዲት ጥይት ብቻ እስክትቀረው እጁን ሊይዙ ከተከታተሉት ፖሊሶች ስድስቱን እያለመ ከረፈረፋቸው በኋላ በመጨረሻዋ ጥይት ራሱን ገድሏል፡፡

እጁን ለጠላት አሳልፎ ላለመስጠት እሳት ጨልጦ የአርበኛ ሞት በሞተው ጀግናው አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመ የኮልት ጥይት ሰለባ ከሆኑት 6 የፖሊስ አባላት ሦስቱ ወዲያውኑ ሲሞቱ ቀሪዎቹ ሦስቱ ደግሞ በጠና ቆስለው በሞትና በህይወት መካከል ሆነው ሆስፒታል ውስጥ በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡ ቆስለው በህክምና ላይ የሚገኙት ፖሊሶች የደረሰባቸው ጉዳት እጅግ በጣም ከፍተኛ በመሆኑ ከሞት ሊተርፉ እደማይችሉ እየተገለፀ ነው፡፡

ጀግናው አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመን በህይወት ለመያዝ ሳይሳካላቸው የቀሩት የጎንደር ከተማ ጥቂት የህወሓት ተላላኪ ፖሊሶችና ደህንነቶች እንዲሁም የመስተዳደሩ አገልጋይ ባለስልጣናት አስከሬኑን በቁጥጥር ስር በማዋል “አንሰጥም” ብለው የነበረ ሲሆን በመጨረሻም በአካባቢው ህዝብ ግፊት የጀግናው አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመ አስከሬን ለቤተሰቡ ተሰጥቶ ስርዓተ ቀብሩ ተፈፅሟል፡፡


በተመሳሳይም ሳጅን ወለላው ዋናይሁን የተባለው የመተማ ወረዳ ፖሊስ የአመራር አባል እንደዚሁ አንድ በወወንጀል የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክር ከነተከታዮቹ ተገድሏል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47730

Wednesday, October 21, 2015

ከሕወሐት መከላከያ ማዕከላዊ ዕዝ እና ምዕራብ ዕዝ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት እየከዳ መሆኑ ታወቀ

የህወሓት አባላት በሆኑ የይስሙላህ የጦር መኮንኖች ከታች እስከላይ ተጠርንፎ በጉልበት ተይዞ በአገር መከላከያ ስም እየተጠራ ነገር ግን በፀረ-ህዝብነት ሳይወድ በግድ እንዲሰለፍ እየተደረገ የሚገኘው ሰራዊት ስርዓቱን መክዳቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ መጥቶ በአሁኑ ወቅት ፈፅሞ ከአገዛዙ ቁጥጥር ውጭ ሆኗል፡፡በተለይም ደግሞ ማዕከላዊ ዕዝ እና ምዕራብ ዕዝ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት የከዳባቸው መሆናቸው ታውቋል፡፡

በማዕከላዊ ዕዝ እና በምዕራብ ዕዝ ውስጥ የሰራዊቱ አባላት ስርዓቱን ጥሎ መክዳት ተባብሶ የቀጠለ በመሆኑ የሰራዊቱ አባላት የትምህርት ማስረጃቸውንና ሌሎችን ሰነዶች ለመያዣነት እየተነጠቁ ይገኛሉ፡፡

በማዕከላዊ ዕዝ እና በምዕራብ ዕዝ በሰፊው እየተተገበረ የሚገኘው ይህ የትምህርት ማስረጃ እና ሌሎችም የግል ሰነዶች ንጥቂያ በተለይም የሙያተኛ መኮንኖችን መክዳት ለመግታት ታስቦ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን ድርጊቱ በሰራዊቱ ውስጥ እልህና ቁጣን ቀስቅሶ ይገኛል፡፡ ከጫፍ የደረሰ ኩርፊያም ጭምር አስከትሏል፡፡

በማዕከላዊ ዕዝ ዕና በምዕራብ ዕዝ ውስጥ ሲከዱ ተይዘው በቁጥጥር ስር የዋሉ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት እንዳሉ የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ ዜና ምንጮች ገልፀዋል፡፡



በሌላ በኩል ደግሞ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ባልተጠበቀ ሰዓት ጥቃት ሊከፍቱ ይችላሉ ተብሎ በመስጋቱ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ላይ ሰፍሮ የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን ታዞ በአካባቢው ከፍተኛ ጥበቃ አየተደረገ ይገኛል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47580

Tuesday, October 20, 2015

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የፔን ካናዳ ተሸላሚ ሆነ

በሽብርተኝነት ተከስሶ 18 አመት የተፈረደበትና በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የፔን ካናዳ ደረጃ አንድ ሰብዓዊነት (PEN Canada’s One Humanity Award) ሽልማት ተሸላሚ መሆኑን ፔን ካናዳ ይፋ አድርጓል፡፡

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በፈረንጆቹ ግንቦት 2012 የባርባር ጎልድ ስሚዝ ሽልማት እንዲሁም በሰኔ 2014 የጎልደን ፔን ሽልማትን ተሸላሚ እንደሆነ ይታወሳል፡፡ በካናዳ ቶሮንቶ እየተደረገ በሚገኘው 36ኛው ዓለም አቀፍ የፀሃፊዎች ፌስቲባል የፔን ካናዳ ደረጃ አንድ ሰብዓዊነት ሽልማትን ተሸልሟል፡፡

እ.ኤ.አ በ2011 የአረብ አብዮትን ተከትሎ መንግስት ለውጥ የማያደርግ ከሆነ ተመሳሳይ ህዝባዊ ንቅናቄ በኢትዮጵያም ሊከሰት ይችላል የሚል አስተያየቱን ማንጸባረቁን ተከትሎ ለእስር የተዳረገውና በፀረ ሽብር ህጉ ተከስሶ 18 አመት የተፈረደበት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በበርካታ የሰብአዊ መብት ተቋማት ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ዓለማቀፍ መብቱን መጠቀሙን በማስታወስ እስክንድር የህሊና እስረኛ እንደሆነ በመግለፅ ከእስር እንዲለቀቅ መጠየቃቸውን ቀጥለዋል፡፡ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ከእስር እንዲለቅ ሲያሳስብ ቆይቷል፡፡


በአሁኑ ወቅት በቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በእስር ቤቱ ከሚደረግበት ከፍተኛ ቁጥጥርና ጫና ባሻገር ከቤተሰብ ውጭ እንዳይጠየቅ ተከልክሎ ይገኛል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47557

Friday, October 16, 2015

ከአዲስ አበባ አስተዳደር የተባረሩት ከ800 በላይ ሠራኞች ከባድ ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ ወድቀው ይገኛሉ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተመድበው ሲሰሩ ከቆዩት ከ800 በላይ ሰራተኞች በመቀነሳቸው ምክንያት ለከባድ ማህበራዊ ችግር እንደተጋለጡ ተዘገበ::

የደህሚት ራድዮ እንደዘገበው የኢህአዴግ ካድሬዎች ስልጣናቸውን ለማደላደል ሲሉ ላይና ታች በሚሉበት በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ መስተዳድር ስር ባሉት የመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ሲሰሩ የቆዩትን ሲቪል ሰራተኞች 800 የሚሆኑትን በተለያዩ ምክንያቶችን በመፈጠር በዚህ ሳምንት ውስጥ ተቀንሰው እንዲወጡ በመደረጉ ምክንያት ያለ ስራ ተጥለው በመቅረታቸው የተነሳ ቤተሰቦቻቸው ለከባድ ማህበራዊ ችግር ተጋልጠው እንደሚገኙ ተገለፀ።

መረጃው በመጨመር ከሲቪል ሰራተኞች ጋር የትምህርት ደረጃቸው ዝቅተኛ ነው ተብለው ከሃላፊነታቸው የተቀነሱት የገዢው ቡዱን ካድሬዎች ግን በመንግስት ልዩ ትኩረትና ድጋፍ ተደርጎላቸው በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅተው እንዲሰሩና ከሌላው ዜጋ የበለጠ ሃብት አፍረተው እንዲኖሩ ሁኔታዎችን እንደተመቻቸላቸው ምንጮቻችን በላኩት መረጃ ለማወቅ ተችሏል።


አስተዳደሩ በሙስና የተጨማለቁ ከፍተኛ አመራሮችና ሲቪል ሰራተኞችን ህግ ፊት በማቅረብ እንዲ ጠየቁ እንደሚያደርግ በተደጋጋሚ ቢገልፅም በተግባር ግን የበታች ሲቪል ሰራተኞች ለመክሰስ መረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ ሲሆን ይህ ግን ወደ በላይ አመራሮች እንዳይሸጋገር ታስቦ እየተከተለው ያለው የስርአቱ አስመሳይ አካሄድ እንደሆነና ከዚህም አልፎ እርምጃ እንዲወስድ የፖለቲካ ቁርጠኝነቱን እንደሚያንሰው የህግ ባለሞያዎች ዋቢ በማድረግ መረጃው ጨምሮ አስረድቷል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47464

Thursday, October 15, 2015

የኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ሰቆቃ ዛሬም ከወደ ደ/አፍሪካ ይጣራል “ይህ አስር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሴኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ” ይለናል የ 15 አመቱ ልጅ ኢትዮጵያዊ እስረኛ

በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን ለመለወጥ/ለማሻሻል በማለት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት ሲሉ በጎረቤት ማላዊ በኩል ለማቋረጥ የሞከሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች በፖሊስ ተይዘው የተፈረደባቸወን የገንዘብ እና የእስራት ቅጣት ቢጨርሱም በአሳቃቂው የማላዊ እሰር ቤት ወስጥ ፈዳቸውን እያዩ እንደሚገኙ የፈረንሳዩ የዜና ወኪል (አጃንስ ፈራንስ ፕሬስ ) እሮብ ጥቅምት 14 2015 አኤአ አ ዘግቧል።

“ለተሻለ ኑሮ ወደ ደ/አፍሪካ ለመሻገር የቋመጡት ኢትዮጵዊያን ሰደተኞች ምኞታቸው ቅዠት ሆነ። “ ያለው ዜና ዘገባው ከመዲናይቱ ሎላንግዊ 85 ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኘው እና ለ 800 እስረኞች ተብሎ በተገነባው የዲደዛ እስር ቤት ውስጥ ወደ 2,650 የሚጠጉ እስረኞች ከእነዚህ መካከል 317 በላይ ኢትዮጵያዊያኖች ያለ በቂ ምግብ እና ውሃ አቅርቦት እየተሰቃዩ ይገኛሉ ብሏል።የ15 አመቱ ኢያሱ ታዲዮስ ባለፈው ሃምሌ ወር ከ 29 ጓደኞቹ ጋር ማላዊ ውስጥ ታሰረው በፍርድ ቤት የተጣለባቸውን የገንዘብ አና የእሰራት ቅጣት ቢፈጽሙም “ወደ አገራቸው የሚያጓጉዛቸ ተቋም በመታጣቱ ለተጨማሪ ሰቆቃ ተጋልጠዋል ተብሏል።እያሱ ሰለደረሰበት ሰቆቃ ሲናገር “ይህ እሰር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሲኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ። ቀድሞ የነበረኝ ሕልም እና ተሰፋ ሁሉ እዚህ ላይ ተገቷል ። ከ 5 ጓደኞቼ ጋር የተጣለብን 62 ዶላር ቅጣትን ብንከፍልም እና እስራቱን ብንጨርስም እስከ አሁን ድረስ አልተፈታንም ። አሁን የምፈልገው ነገር ቢኖር ወደ አገሬ መመለስ ብቻ ነው ።” በማለት ሰውነቱ በደካም እና በረሃብ የጠወለገው ታዳጊው ወጣት ኢያሱ በማላዊው እስርቤት ውስጥ የደረሰበትን ሰቆቃ እና መጥፎ ገጠመኝ በመግለጽ “የድረሱልን” ጥሪውን አቅርቧል።


ባለፈው መሰከረም ወር በአሜሪካው የስደት ተመላሾች ደረጅት አማካኝነት 70 ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች ነፍሳችውን ብቻ አትርፈው ወደ አገራቸው በበጎ ፍቃደተኝነት የተመለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በእሰራት ላይ ያሉተን 317 ወገኖቻችንን ወደ ኢትዮጵያ ለማጓጓዝ በትንሹ የ አሜሪካ 200,000 ዶላር እንደሚያሰፈልግ ተገምቷል።የአለም አቀፉ ከሰደት ተመላሾች ድርጀት ተሰፋ የጠፋባቸው ኢትዮጵያዊያኑ ሰደተኞችን ወደ አገራቸው ለማጓጓዝ የበኩሉን ጥረት ቢያደረግም የአለማቀፉ ማህበረሰብ ወቅታዊ ትኩረቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ (የሶሪያ ሰደተኞች) ላይ በመሆኑ አትዮጵያዊያኑ ሰደተኞች አሰተዋሽ አጥተዋል ተብሏል ። የደርጅቱ ዋና ሹም የሆኑት ሚስስ ካትሪን ሳኒ በበኩላቸው “እነዚህ ማስኪን ነፍሳት ከአገራቸው /ከኢትዮጵያ / እርቀው እንደዚህ አይነቱ አሰከፊ ሁኔታ ውስጥ መውደቃቸው በእጅጉ ያሳዝናል” በማለት በኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ችግርን በሃዘኔታ ለማስረዳት ሞክረዋል።

በዚህ አጋጣሚ አገሪቱ በኢኮኖሚዋ “አድጋለች፣ ተመንደጋለች፣ ሰላም እና መረጋጋት ዙሪያ ገባዋን ሰፈኖባታል” ከተባለ ለምን ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ፖለቲከኞች ያልሆኑ ነገር ግን የወደፊቱ አገር ተረካቢ የሆኑ ሕጻናት እና ወጣቶች አስከፊውን የባህር እና የየብስ ጉዞ በማድረግ ለእንደዚህ አይነቱ እጅግ ዘግናኝ እና አሳቃቂ ችግር ይጋለጣሉ? ብለው የሚጠይቁ ወገኖች ተበራክተዋል።


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47441

Monday, October 12, 2015

ለማይቀረው እና ለመጨረሻው ትግል ከዚህ ፍሽስት ከወያኔ አገዛዝ ጋር ለሚደረገው ትንቅንቅ እራሳችንን በተገቢው መንገድ እናዘጋጅ !!!

ለሚደረገው ትንቅንቅ እራሳችንን በተገቢው መንገድ እናዘጋጅ የምልበት ምክንያት በርካታ እድሎችን ወይንም አጋጣሚዎችን በእኛ የዝግጅት ማነስ እንዲሁም ሁኔታዎችን አስቀድሞ ፖለቲካዊ ትንበያ ወይንም ትንተና ተሰጥቶ በዛላይ ተንተርሶ ለዛ የሚሆን ተመጣጣኝ ዝግጅት ባለመደረጉ የተገኙት ወርቃማ አጋጣሚዎች በሙሉ እንዲሁ እንደዋዛ አሳልፈናቸዋል:: ስለዚህም ታሪካዊ ጠላታችን ይሄንን እድል በአግባቡ ተጠቅሞ እንደ እባብ አፈር ልሰው ያሉባቸውን ችግሮች ቁጭብለው ለማስተካከል የማገገምያ ግዜ በእኛ ደካማነት ስላገኙ በመልሶ ማጥቃት የፈሪ ዱላቸውን አሳረፉብን::

እንደዛም ሆኖ በተፈጠረውም ችግር (ከባድ ምት) በቶሎ ማገገም ስላልተቻለ ገሚሱን ለስደት እኩሌታ ውን በአገር ውስጥ ሆነው በመሰባሰብ እንደገና በጥቂቱ ለማንሰራራት ሞክረው አዳዲስ እና ነባር የፖለቲካ ስሞችን በመጠቀምም እንደ አዲስ አባሎቻቸውን በመመዝገብ በተገኘችው ትናንሽ ቀዳዳዎችን ተጠቅመው የፓርቲያቸውን አላማ ለሕዝብ በማስተዋወቅ ሰላማዊ ሰልፎችን በማድረግ(የተሳካም ያልተሳካም)ፓርቲዎቻቸውን ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሮላቸው ነበር። ሕብረተሰብ በሚገባ የተቀበላቸውን ለአብነት ያህል ለመጥቀስ አንድነት፣መኢአድ እና ሰማያዊ በመባል ይታወቁ ነበር:: ነበር ያልኩበት ምክንያት ከእነዚህ ከላይ ከጠቀስኩዋቸው ሰዎስቱ ድርጅቶች(የፖለቲካ ፓርቲዎች) መካከል በጠራራ ጸሀይ ታሪክ እራሱን ይደግማል እንዲሉ ቅንጅት ላይ የደረሰው በተመሳሳይ ሁኔታ በአንድነት እና መኢአድ ደርሶ አየነው ማነህ ባለሳምንት አትሉም? ከላይ በጥቅሉ ለማስቀመጥ እንደሞከርኩት በቢጫ ካርድ ሆናቹ ለተቀመጣችሁቱ አሁን ገዢው ፓርቲ ከሚያሳድርባቹ ጫና በመነሳት የተወሰኑትን አባል ወይንም አመራር በማሰር በማስፈራራት በናንተው መካከል ልዩነት በመፍጠር እናንተንም እንደ ሌሎቹ ችግር ውስጥ ሊከቱዋቹ ይችላሉ ወይንም ጠንካራ አመራሮችን በመለየት የተለያየ ታፔላ በመለጠፍ አገዛዙ የተለመደ ጨዋታውን ሊጫወት ይችል ይሆናል::

ስለዚም ችግሩ ደርሶ ጋቢ ተከናንባቹ ሶፋላይ ከመተኛታቹ በፊት አንድ በአንድ ሊመጡ ይችላሉ ብላቹ ያሰባችሁትን ችግሮች ሳትንቁ ከነመፍትሄው በማስቀመጥ ፣ ተተኪ አመራሮችን በማዘጋጀት ፣ ትግሉ እንዲቀጥል የበኩላችሁን ማድረግ ይጠበቅባቹኋል። በሀገር ውስጥ የሚደረገው ትግል በወያኔ የፈሪ በትር ለስደት የተዳረገውን ጨምሮ የለም ይሄንን የፋሽስት ስርአት ለማስወገድ ትክክለኛው አማራጭ በተጠናከረ በሁለገብ ትግል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ግዜ ማስወገድ ነው በሚል በጠነከረ መንፈስ የትግል አቅጣጫ በማስቀመጥ በተቁዋቋመ በአጭር ግዜ በቀላሉ ከሀገር ውጭ የሚኖሩ ኢትዬጵያኖችን እና ትውልደ ኢትዬጵያኖችን በማስተባበር እና እንደ አለት የጠነከረ ሕዝባዊ መሰረት የያዘ ድርጅታዊ ተክለ ቁመና በመያዝ ወያኔ ከዚህ ቀደም እንደልብ ይፈነጭበት የነበረውን ይውጩን ማህበረሰብ ከጫፍ እስከጫፍ በማነቃነቅ በተጠናከረ ተቃውሞ እዛው ባለበት በሀገር ቤት ብቻ እንዲወሰኑ(እንዲያፈገፍጉ) አድርጎዋቸዋል::

በዚህም ሳያበቃ የትግል አድማሱን በማስፋት ጠንካራ ሕዝባዊ መሰረት ያለውን የውጭ እምቢተኝነት በማቋቋም በሂደትም በአላማ ተቀራራቢ ከሆነው በትጥቅ ትግሉም የካበተ ልምድ ካለው እና ከወያኔ ሰራዊት ጋር ለበርካታ ግዜ በመግጠም አንጸባራቂ ገድሎችን ከተጎናጸፈው ድርጅት ከአርበኞች ግንባር ጋር በመዋሀድ ትግሉን ወደላቀ ደረጃ በማሳደግ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ፣ ሁለቱም ድርጅቶች የተናጠል ህልውናቸውን በማክሰም የአርበኞች ግንቦት7 ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄን መስርተው ከሌሎች መሰል ድርጅቶች ጋርም በግንባር ወይንም በጥምረት እና ትብብር በማድረግ አብረው እንደሚሰሩ ከኢትዬጵያ ሳተላይት ቴሌቨዥን ጋዜጠኛ ከሲሳይ አጌና ጋር በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል:: የአርበኞች ግንቦት7 ዋና ሊቀመንበር ዶክተር ብርሀኑ ነጋም የሰጡትን ቃለ ምልልስ ላዳመጠ ሰው፣ ግንቦት7 ዋና ሊቀመንበር ዶክተር ብርሀኑ ነጋም የሰጡትን ቃለ ምልልስ ላዳመጠ ሰው፣ የድርጅቱን መግለጫዎች ላነበበ እና በተጨማሪም የኤርትራው ፕሬዘዳንት አቶ ኢሳያስ አፈወርቄን በግልጽ በኤርትራ በትጥቅ ትግል የሚቀሳቀሱትን ድርጅቶችን እንደሚረዱ ማሳወቃቸውን ለተመለከተ እና በተለይም በራስ መተማመናቸውን ላስተዋለ ሰው ታጋዬቻችን በከፍተኛ ሁናቴ ላይ እንደደረሱ ለማወቅ ጠንቁዋይ መሆን አይጠይቅም:: የወያኔም ግብአተ መሬት መፈጸሚያው እንደተቃረበ ለማንም ግልጽ እየሆነ የመጣ ይመስላል በውጩ የትግል እንቅስቃሴ በዚሁ ላይ ልግታና ወደ ቀደመ ነገሬ ልመለስ ።

ለማይቀረው እና ለመጨረሻው ትግል ከዚህ ፍሽስት ከወያኔ አገዛዝ ጋር ለሚደረገው ትንቅንቅ እራሳችንን በተገቢው መንገድ እናዘጋጅ የሚለው መልእክቴ በቀጥታ ወይም በዋነኛነት የሚጠልዋትን ሐገር በሚገዙት ጭራቆች ለተማረራቹ፣ በስቃይ እና በመከራ ውስጥ ላላችሁቱ ወገኖቼ እንባችሁን ሊያብሱ የቆረጡ የግፍ አገዛዙን ወደ መቀመቅ ሊከቱ ተዘጋጅተው ይጠብቁሀል እና ስለዚህም የሀገሬ ሰዎች አቅም ያላቹ ትግሉን በቀጥታ ያሉበት ድረስ በመሄድ መቀላቀል ይገባል እያልኩኝ ከላይ የጠቀስኩትን አማራጮች ለመጠቀም እድሉ ላልገጠማቹ የጽሁፌ ማጠቃለያ ላይ ላስቀምጠው ። በመጨረሻም መሳርያ አንስተው የትግል ጥሪ አቅርበውላቹ ነገር ግን በአንዳንድ ምክንያት ትግሉን መቀላቀል ላቃታቹ ሰዎች በአካባቢያቹ ሆናቹ ከምትተማመኑት ሰዎች ጋር በመሆን ተቡዋድናቹ ህዝባዊ እንቢተኝነት ሲነሳ ተገቢውን ተሳትፎ ማድረግ በተጠናከረ እና አንድ ወጥ በሆነ በተባበረ ትግል አሁን የተገኘውን አጋጣሚ ተጠቅሞ ወያኔን የስንግ ይዞ እራሱ አርቆ በቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ግብአተ መሬቱን ለመፈጸም በቆራጥነት መዘጋጀት ያስፈልጋል ስል ጽሁፌን በዚሁ እቋጫለሁኝ ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ድል ለሠፊው ሕዝብ

ሰለሞን ነኝ ከኖርዌ,በርገን ቸር ይግጠመን

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47349

Sunday, October 11, 2015

ለብይን ተቀጥረው የነበሩት ዞን 9 ጦማሪያን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ

በተጠረጠሩበት የሽብርተኝነት ድርጊት ወንጀል ለብይን ለመስከረም 27 ቀን 2008 ዓ.ም. ተቀጥረው የነበሩት ጦማሪያን ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ አቤል ዋበላና በፈቃዱ ኃይሉ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ፡፡

ጦማሪያኑ ፍርድ ቤት ያልቀረቡበት ምክንያት ደግሞ በዕለቱ በሌላ ሥራ ምክንያት ይሁን ወይም በሌላ ጉዳይ ባይታወቅም፣ ለብይን የቀጠሯቸው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ዳኞች እንደሌሉ ተነግሯቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ብይኑ በዕለቱ እንደሚሰጥ የገመቱ የጦማሪያኑ ቤተሰቦች፣ ጓደኞቻቸውና ጋዜጠኞች በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ የተገኙ ቢሆንም፣ የፍርድ ቤቱ ሠራተኞች ‹‹ዳኞች ስለሌሉ እንዳይመጡ መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ለማረሚያ ቤቱ ተደውሎ ተነግሮታል›› በማለታቸው ለመከታተል የሄዱ ታዳሚዎች ተመልሰዋል፡፡

የጦማሪያኑ ጠበቆች ግን በሁኔታው ማዘናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ፍርድ ቤቱ በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ማስታወቂያ መለጠፍና ጉዳዩን የሚከታተሉ እንዲረዱ ማድረግ ሲገባው፣ ምንም ሳይል መሄዱ አግባብ አለመሆኑንና ታይቶም እንደማይታወቅ ገልጸዋል፡፡


ጦማሪያኑ እንዲከላከሉ ወይም መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ የሚሰናበቱበት ብይን ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በሙሉ ከመስከረም 26 ቀን እስከ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. አዳማ ሥልጠና ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47329

Friday, October 9, 2015

የሕወሓት ሰዎች ዶላርን በሰሜን አሜሪካ በ23 ብር እየመነዘሩ ሃብታቸውን በማሸሽ ላይ መሆናቸው ታወቀ

የሕወሓት ባለስልጣናት ከሃገር ቤት ሃብታቸውን ለማሸሽ እየጠቀሙበት ያለው ዘዴ የኢትዮጵያን ባንኮች ከመጉዳቱም በላይ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አስፈሪ ዳመና እንደጣለበት ተሰማ:: በአሁኑ ወቅት የሕወሓትና የተላላኪዎቹ ድርጅቶች ባለስልጣናት በሙስና ያከበቱትን ሃብት እያሸሹ ያሉት እዚህ ሰሜን አሜሪካ ወደ ሃገራቸው ዶላር መላክ የሚፈልጉትን በ23 ብር ሃገር ቤት ላይ እንመነዝርላችኋለን በሚል እንደሚቀበሉና በዚህም ጥቁር ገበያ የሕዝብ ሃብት እየሸሸ መሆኑ ተጋልጧል::

በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ; በሲያትል; በዴንቨር; በሚኒያፖሊስ; በአትላንታ; በዳላስ; በቺካጎ; በሂውስተን; በኦሃዮ; በፖርትላንድ; በላስቬጋስ; በካሊፎርኒያ የተለያዩ ከተሞች; በአሪዞና በተዘረጉ ኔትወርኮች ዶላር በጥቁር ገበያ 23 ብር እየተመነዘረ መሆኑ ታውቋል::

የገንዘቡ ዝውውር የሚደረገው ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች ባሉ ኔትዎርኮች መካከል ዶላሩን እዚሁ ይሰጡና ሃገር ቤት በግለሰቦች አማካኝነት በ23 ብር ምንዛሬ ይሰጣል::

ዘ-ሐበሻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድረገጽ ባገኘችው መረጃ መሰረት በዛሬው ዕለት የዶላር ምንዛሬ ዋጋ 20.85 ሲሆን በ23 ብር በጥቁር ገበያ እየሸጠ ይገኛል::


ዶላር በሕገወጥ መንገድ እንዲህ መተላለፉ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንግስት ዘንድ ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት የሚያባብሰው መሆኑ እየታወቀ የሕወሓት ሰዎች እንዴት እንዲህ ባለው ሕገወጥ ተግባር ላይ እንደተሰማሩ የሚያስገርም ነው የሚል አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች ከጥቂት ጊዜያት በፊት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “የኢትዮጵያን መንግስት በኢኮኖሚ ማዳከም ካስፈለገ ከውጭ የሚላኩ ዶላሮች በኢትዮጵያ ባንኮች በኩል መተላለፍ የለባቸውም:: ሕዝቡ ዶላሩ መንግስት እጅ በማይገባበት መልኩ ገንዘቡን ይላክ” ማለታቸውን ይጠቅሳሉ::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47282

Thursday, October 8, 2015

ረሃቡ ከገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው !! ‹‹ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነውን ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል አለብን›› ሰማያዊ ፓርቲ

ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ መስከረም 27/2008 ዓ.ም በፅ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ረሃቡ ከገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት የመነጨ ነው ብሏል፡፡ ፓርቲው ‹‹ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!›› በሚል በሰጠው መግለጫ ‹‹ገዥው ፓርቲ ችግር ቢከሰት እንኳ በአደጋ ጊዜ ለዜጎች የሚበቃ እርዳታ አቀርባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ለወገኖቻችን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡›› ሲል ወቅሷል፡፡ ‹‹ለዜጎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳይደርሱላቸው የተፈጠረው ረሃብ የራሱ የፖሊሲ ውድቀት መሆኑን የሚያውቀው ስርዓቱ የዜጎቻችን ስቃይና መከራ ሲሸፋፍን እንደቆየና ከአቅሙ በላይ ሲሆን ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልፅም ለዜጎች ተገቢውን እርዳታ በሚያስገኝ መልኩ እርምጃ እየወሰደ አይደለም›› ብሏል መግለጫው፡፡ ለተከሰተው የረሃብ አደጋ ተገቢው ትኩረት መነፈጉም ገዥው ፓርቲ እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ ቢስነቱን የሚያረጋግጥ እንደሆነ አስታውቋል፡፡

ፓርቲው በመግለጫው ‹‹ረሃቡ፣ ርዛቱ፣ ድህነቱ፣ ስደቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎችን በብርቱ እየተፈታተኑ በሚገኝበት ወቅት ገዥው ፓርቲና በስሩ ያሉ ድርጅቶች ተመሰረትንበት የሚሉትን ጊዜ ለወራት በቅንጦት በማክበር በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጉሮሮ ነጥቆ ድግስ ሲደግስና አሸሸ ገዳሜ ሲል በርካታ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኗል፡፡›› ብሏል፡፡ ለተከሰተው ረሃብ ኢህአዴግ ለይስሙላ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደርን ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሰራ አረጋግጧል ያለው መግለጫው ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል ቢልም እስካሁን ግን በየአመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የረሃብ ሰለባ እንደሆነ መቀጠሉን ገልፆአል፡፡ መሬት የመንግስት ነው በሚል ሽፋን አርሶ አደሩን ከቀየው እያፈናቀለ ለስርዓቱና ደጋፊዎችና ለባዕዳን መሬትን እየሸጠ አርሶ አደሩን ለረሃብ ተጋላጭ አድርጎታል ሲልም ለርሃቡ ምክንያት የኢህአዴግን የፖሊሱ ውድቀት እንደሆነ ገልፆአል፡፡


ገዥው ፓርቲ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ የጠየቀው ሰማያዊ ፓርቲ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ በረሃብ ለተጠቁት ዜጎች መፍትሄ እንዲፈለግም ጠይቋል፡፡ ስርዓቱ ደካማና ኃላፊነት የጎደለው እንደሆነ የገለፀው ሰማያዊ ፓርቲ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የዓለም ማህረሰብ ማህበረሰቡ ከተጎጅዎቹ ጎን እንዲቆሙ ጠይቋል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያውያን መከራ የመነጨው ከገዥው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲ፣ የአፈፃፀም ብቃት ችግርና ለኢትዮጵያውያንም ባለው ግድ የለሽነት በመሆኑ ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነ ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል አለብን›› ሲልም ለህዝብ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ፓርቲው ረሃቡ በተከሰተባቸው አካባቢዎች መረጃ በማሰባሰብና በማጣራት ለህዝብ እንደሚያሳውቅም ገልፆል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47264

Tuesday, October 6, 2015

ዘራፊው ሕወሓት ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ ውሳኔ ሰጪ ያልሆኑ ወንበሮችን ለአሽከሮቹ አድሏል::

October 6,2015
- አቶ ሬድዋን ሁሴን በሃስት ሲምሉለት የነበረውን ወንበር አጥተዋል::
- ሃይለማርያም ከኒውዮርክ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ከሰው እንዳይገናኙ ተደርገዋል::
- ጥያቄ የሚያበዙት አቶ አለማየሁ ተገኑ እና አቶ ሶፊያን አህመድ ከአሽከርነት ቦታቸው ተነስተዋል::
- ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::

 ምንሊክ ሳልሳዊ:- የሕወሓት አሻንጉሊት የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ በዛሬው እለት ባቀረበው የቸብ ቸብ ካቢኔ መሰረት ሕወሓት የጦር ሃይሉን የውጪ ጉዳዩን የደህንነቱን የኮሚኒኬሽን እና አስፈላጊ ቀልፍ ጉዳዮችን በመቆጣጠር ውሳኔ ሰጪ የማይባሉ ተራ ቦታዎችን ለአሽከሮቹ በማደል የተዋቀረ ሲሆን አለማየሁ ተገኑ እና ሶፍያን አህመድ ምን እንደዋጣቸው አይታወቅም::ከኒውዮርክ ስብሰባ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያ ቤቱ እንዳይወጣ እና ከሰው እንዳይገናኝ የታገደው ሃይለማርያም ደሳለኝ ራሱን ፈልጎ አለማግኘቱ እና በአሽከርነት መኖሩን ቤተሰቦቹን እያበሳጨ መሆኑ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ይናገራሉ::
ቁልፍ የሆኑ ስልጣኖቹን የተቆጣጠረው እና በዘመድ አዝማድ ተሞልቶ በከፍተኛ የሃገር እና ሕዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የተሰማራው ሕወሓት ባለፈው የኢሕአዲግ ስብሰባ ወቅት አንዳንድ አመራሮቹ ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ ከስልጣን እንደሚባረሩ ሲነገር ነበር:: የወያኔና አሽከሮቹ ሹመት እንደሚከተለው ነው:-
አቶ ደመቀ መኮንን – ም/ጠቅላይ ሚኒስትር እና የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ
ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል –በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
ወይዘሮ አስቴር ማሞ – በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ሲራጅ ፈጌሳ – የመከላከያ ሚኒስትር
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አቶ ካሳ ተክለብርሃን – የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር
አቶ ጌታቸው አምባዬ – የፍትህ ሚኒስትር
አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ – የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
አቶ ተፈራ ደርበው – የእርሻ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ስለሺ ጌታሁን – የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ አህመድ አብተው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
አቶ ያዕቆብ ያላ – የንግድ ሚኒስትር
አቶ አብይ አህመድ – የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
አቶ ወርቅነህ ገበየሁ – የትራንስፖርት ሚኒስትር
አቶ ሙኩሪያ ሀይሌ – የከተማ ልማት እና ቤቶች ሚኒስትር
ዶክተር አምባቸው መኮንን – የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
አቶ ሞቱማ መቃሳ – የውሃ፣ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ – የትምህርት ሚኒስትር
አቶ ቶሎሳ ሻጊ – የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ – የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ – የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
ኢንጂነር አይሻ መሀመድ – የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ -የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም – የአካባቢ ደን ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን – የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስትር
ወይዘሮ ደሚቱ ሀምቢሳ – የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
አቶ በከር ሻሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬከተር
አቶ ጌታቸው ረዳ – የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
ዶክተር ይናገር ደሴ – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::በአንድነት በመቆም ሃገራችንን ከጅቦች እናድናት:

http://www.satenaw.com/amharic/archives/10659

Thursday, October 1, 2015

ለሰብዓዊ መብት ስብሰባ ወደስዊዘርላንድ የተጓዙ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች ስብሰባ ረግጠው ወጡ

የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30 ጉባኤ ጋር ተያይዞ በተጠራ መድረክ ላይ የተጋበዙት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ስብሰባ ረግጠው ወጡ።
ስኞ እለት የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብት በተመለከተ በተጠራው ስብሰባ ላይ የተገኙትና በኋላ በቀረበው ሪፖርት ሳይደሰቱ ስብሰባውን ረግጠው የወጡት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ወደ ስብሰባው አልተመለሱም።
የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተወካዮች ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ግለሰቦች በጄኔቭ ስዊዘርላንድ በመገኘት በወቅታዊ የኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት አያያዞች ዙሪያ መወያየታቸውን እማኞች አስታውቀዋል።
ይሁንና የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች በመድረኩ ሊነሱ በሚችሉ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ከጉባኤው ረግጠው መውጣታቸው ታውቋል።
ሂውማን ራይትስ ዎችን ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣና አፈና ተባብሶ መቀጠሉን ገልፀዋል።
ሁሉንም የፓርላማ ወንበሮች በብቸኝነት ተቆጣጥሮ የሚገኘው ገዢው የኢህአዴግ መንግስት፣ የዜጎችን ሃሳብን የመግለጽ መብት ከማስፋፋቱ በተጨማሪ በነጻ የመገናኛ ብዙሃን ላይ የሚወስደው እርምጃ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ድርጅቱ አመልክቷል።
ከትናንት በስቲያ ሰኞ የተካሄደውን የሰብዓዊ መብት መድረክ ያዘጋጀው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን በተለያዩ ጊዜያት በኢትዮጵያ ስላለው የሰብኣዊ መብት አያያዝ ስጋቶችን ሲገልፅ መቆየቱ ይታወሳል።
በጄኔብ በተካሄደው በዚሁ ልዩ መድረክ የተሳተፉ በርካታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ረፖርት ማቅረባቸውንም በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ገልፅዋል።
የእንግሊዝ የፓርላማ አባላትን ጨምሮ በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጀቶች ኮሚሽኑ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝን ጨምሮ በተለያዩ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ክትትልን እንዲያደርግ ጥያቄ አቅርበው እንደሚገኙም ተችሏል።

የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች መድረኩን ረግጠው ስለወጡበት ምክንያት የሰጡት ምላሽ የለም።
http://ethsat.com/amharic/%E1%88%88%E1%88%B0%E1%89%A5%E1%8B%93%E1%8B%8A-%E1%88%98%E1%89%A5%E1%89%B5-%E1%88%B5%E1%89%A5%E1%88%B0%E1%89%A3-%E1%8B%88%E1%8B%B0%E1%88%B5%E1%8B%8A%E1%8B%98%E1%88%AD%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%8B%B5/

ወያኔዎች ሂሳብ የምታወራርዱበት ግዜ መጣ!!!

ሳሙኤል አሊ ከ- ኖርዌይ
አንድ ድርጅት በአመት 2 ጊዜ ወይም አንድ ጊዜ የድርጅቱን ጠቅላላ ሂሳብ ይፈትሻል ። ወጪው ምን ያህል ነው? ገቢውስ ምን ያህል ነው? ከወጪ ቀሪ  ምን ያህል አስገባ? እያለ ድርጅቱ ማትረፉን እና  ማክሰሩን ያውቅበታል። እንዲሁም ሃላፊ ቦታ ያሉትም ሰወች የሚገመገሙበት ነው። የታማኝነት ስራ፤የታማኝነት እድገት፤ የታማኝነት አገልግሎት፤ ለአገራችንም ይገባል።

ወያኔወች አገሪቱን ከተቆጣጠራቹሁበት  ግዜ ጀምሮ እንደፈለጋቹ ስትዘርፉ እንዳሻቹሁ ስታዙ ከርማቹሃል። ባንኮችን የሃገሪቷ ህግ ከሚያዘው ውጪ ቢሮአቹሁ ቁጭ ብላቹሁ በቀጭን ትእዛዝ ብቻ ወደ ውጪ አገር በምትሄዱበት ግዜ የፈለጋቹሁን  ያህል ዶላር በማን አለብኝነት  እየዘረፋቹ እንደሆነ  እናውቃለን። የህዝብ ንብረት የሆነውን ሁሉ  በመዝረፍ ለራሳቹሁ በጣም ብዙ ድርጅቶች እንደከፈታቹ  እናውቃለን። የህዝብ  ሃብት በመንጠቅ ትልልቅ ፎቆችንም እንደገነባቹ እናውቃለን።  በህዝብ ስም ከውጪ እርዳት በመለመን  እንዲሁም ለጋስ አገሮች ለህዝብ እንዲደርስ የሚሰጡትን የእርዳታ ገንዘብ   በልጆቻቹህ ስምና በተለያዩ  ስሞች በተለያዪ አለም አቀፍ ባንኮች እንደምታከማቹ እናውቃለን። አሁን ግን ግዜው ሂሳብ የምታወራርዱበት ግዜ ነውና ተዘጋጁ።

በዘረፋቹሁት የህዝብ ንብረት የተለያዩ  ድርጅቶችን  በስማቹሁ ከፍታቹሁ   የወያኔ  መንግስት ስልጣን ከያዘ በሃላ እንዚህን ሁሉ ድርጅቶች ተከፍቷል ብላቹ  ለኢትዮጵያ ለህዝብ እንደምትሰሩ ለማስመሰል የምትሞክሩትን እና የምትቀልዱትን ቀልድ መለወጥ አልተቻላቹሁም። ብዙ ህንጻወች ተሰርተው ከተሞች አድገዋል ብላቹ በናንተ ስምና በልጆቻቹ ስም እንዲሁም  ለሆዳቸው ሲሉ በሰገዱ ጥቅመኞች የተገነባ እንደሆነ  ስለምናውቅ ከተማዋ  ፎቅ በፎቅ ሆነች የምትሉትን ቀልድ  ሰሚ ጆሮ የለም። አሁን ግን እንዲዚህ አይነት የድናቁርት ወሬ የምንሰማበት ግዜው አልቋል እና ሂሳባቹሁን ልናወራርድላቹ ከዳር እስከዳር ተነስተን እየመጣንላቹሁ ነው ።

ልማት ላይ ነን እድገት ላይ ነን እያላቹሁ  በሕዝብ ስም የምታሾፉ ልማት ማለት እህል እንደማያውቅ አንበጣ በሁሉም የኢትዮጵያ ወሳኝ ቦታወች ላይ ሰፍራቹሁ መብላታቹሁን ነው ልማት የምትሉን ? ልማት ላይ ነን የምትሉን ብቃት ያላቸውን ሰራተኞች በማባረር የራሳቹሁን ደናቁርት  ካድሬን መሰግሰግ ነው ?  ልማት የምትሉን  አየር መንገዱን 90%፤ መከላከያ 95%  ፤ሚኒስትሮች 85%፤ ጉምሩክ 90% ፤ኢምግሬሽን 90% ፤አየር ሃይል 90% ፤የአገር ውስጥ ተቆጣጣሪ 90% ፤የውጪ  ንግድን ተቆጣጣሪ 90%፤ የስልጣኑን  ቦታ ይዛችሁት  አውቃቹሁ ወይም ቦታው መጥናቹህ ቢሆን መልካም ነበር  ነገር ግን ደናቁርቶች እራሳቹሁ ተደናቁረው ሌላውን የሚደናቁሩትን  ሰብስባቹ በበላይ መቀመጣቹሁን ነው ልማት የምትሉን ?  የትምህርት ውጤታቹህም  እንደዚሁ በ 90% ቢሆን ኖር ምነኛ ባማረ ነበረ ። እኛም የቀልድ ጊዜው  ማብቃቱን የወያኔ ደናቁርቶች የሚናገሩትን የምንሰማበት ሰዓት ማብቃቱን ነግረናቸሁ ሂሳባቹሁን ለማወራረድ ሰለመጣን ለዛ ተዘጋጁ።

ጊዜው ለወያኔዎች የምጥ ግዜ እንደሆነ እናውቃለን። ውስጣቸው በከፍተኛ  ሁኔታ መባላት ውስጥ እንዳሉም እናውቃለን። የዘረፉትን  የሕዝብ ሃብት ኪሳቸውን ሞልቶ  አስጨንቆአቸዋል። እንደዚህ እየዘረፉ እና ህዝቡን እየገደሉ ለሁል ግዜ ስልጣናቸው ላይ ተቀምጠው መኖርን ቢመኙም ይህንን ምኞታቸውን አጨልሞ ለኢትዮጵያን የብርሃን ጊዜ ሊያመጣ የሚችል እራይ ይዘው በአርበኞች ግንቦት ሰባት በሌሎችም የኢትዮጵያ  ታጋዮች በመዋህድ ከኤርትራ ምድር አልፎ  ከጫፍ እስከጫፍ  ባለችው ኢትዮጵያ  የትግሉ አላማ እና ትግሉን የማቀጣጠሉ ስራ  በሚገባ ተሰርቶ  ህዝባችን በሚገርም  ፍጥነት ወደ ትግሉ በመቀላቀል የተዘረፈውን ንብረት ለማስመለስ የተነጠቀውንም ሰላም ለመመለስ  ወያኔ ላይ የሰላ ብረት ደግኖ ሂሳቡን ሊያወራርድ መጥቷል።

ይሄኔ ነው ወያኔ በሻንጣ ብር ይዘው መሰወር የጀመሩት። ያላቸውን ንብረት ወደተለያዩ የውጪ ባንኮች ማስገባት ልጆቻቸውንና የቅርብ ዘመዶቻቸውን በማሸሽ  እውን እነሱ እንዳሰቡት የኢትዮጵያንን  ሃብትና ንብረት ማሸሽ ይችላሉን ?

ትግሉ የተቀጣጠለው በአገር ቤትም በውጪም ነው ለውያኔዎች ውስጡም  እሳት ውጪውም እሳት ሆኖ ነው የሚጠብቃቸው።  የኢትዮጵያንን ሃብት ዘርፈው  የኢትዮጵያን ህዝብ ገድለው ወዴት ሊሰወሩ ወድዬትም መሰወር አይችሉም። በውጪ ያለው ኢትዮጵያዊ  ዘርፌ እና ገድዬ አመልጣለው  ብሎ ያሰበውን የወያኔ ሰወችን ነቅቶ  በመጠበቅ ላይ ነው። አሁን ሂሳብ የምታወራርዱበት  ስለሆነ በአለም ላይ ያሉት ባንኮች በሙሉ ከኢትዮጵያን  ህዝብ የተዘረፉ ንብረት መሆኑን በማሳወቅ አገርን ለማጥፋት ህዝብን ከህዝብ ለማጫረስ የሰራቹሁት ስራ ለአለም በማሳወቅ በይፋ የሚነገርበት  ግዜ ከፊታቹ በቆረጦቹ የኢትዮጵያ ልጆች ስለመጣ ሂሳባቹሁን  እናወራርዳለን።

1 የዘር ማጥፋት ወንጀል የሰራቹሁ ወንጀለኞች

2 አገሪቷን ለባእዳን ቆርሳቹሁ የሸጣቹሁ ወንጀለኞች

3 ዘርን ከዘር ሃይማኖትን ከሃይማኖት ለማጠፋፋት የተነሳቹ ወንጀለኞች

4 ንጹሃንን በማሰር በማሰቃየት እስርና መከራ በማብዛት ወንጀል

5 የአገሪቷን ሃብት ያለአግባብ ለግል ጥቅማቹሁ በማዋል ወንጀል

6 ስልጣንን ለአፈና  ስራ በመጠቀም ወንጀል.

7 ስልጣንን አለአግባብ በማን አለብኝነት በቦታው ለማይመጥን ሰው በመስጠት ወንጀል
ኢትዮጵያኑን በማግለል  በመስሪያቤቱ የአንድ ብሄር ተናጋሪ ሰዎችን  ብቻ  በመቅጠር ወንጀል…… እያሉ የሰራቹሁትን ወንጀሎቻቹሁን የምናወራርድበት  ሰዓት አሁን ነው። የትም ማምለጥ የለም። የትም መደበቅም የለም። በሁላቹሁም በራፍ አንኳኩተን እንመጣለን። ያኔ ሂሳባቹሁን ታወራርዳላቹሁ።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

ሳሙኤል አሊ ከ-ኖርዌይ

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47069