Sunday, March 18, 2018

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሰላማዊ ዜጎችን መግደል እንዲቆም ጠየቁ

ከእስር በቅርቡ የተፈቱት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ወልዲያ ናቸው።  የጉዟቸው ምክንያት ደግሞ ልጆቻቸው በመንግሥት ታጣቂዎች የተገደሉባቸውን ቤተሰቦች ለማፅናናት እንደሆነና በዚህም “መንግሥት ሰላማዊ ዜጎችን ተኩሶ ሊገል አይገባም” የሚል መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ እንደሆነ ለባልደረባችን ለመለስካቸው አምሃ ነግረውታል።መለስካቸው ከአዲስ አበባ ደውሎ ሦስቱንም እንዲሁም አብረዋቸው ያሉትን የ13 ዓመት ዕድሜ ልጃቸው ዮሴፍ እሸቱ የተገደለባቸውን አባት አቶ እሸቱ ጀመረን አነጋግሯል።
 VOA Amharic
http://www.satenaw.com/amharic/archives/53041

No comments:

Post a Comment