Saturday, November 7, 2015

ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት ዓለሙ የምትወዳትን ሀገሯን ጥላ አሜሪካ ገባች


በቅርቡ ከሕወሓት መንግስት እስር ቤት የተለቀቀችው ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት ዓለሙ ዛሬ አሜሪካ ገባች::
ዛሬ ኖቬምበር 7, 2015 ዋሽንግተን ዲሲ ዱልስ ኤርፖርት የደረሰችው ርዕዮት በዲሲና አካባቢዋ በሚኖሩ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ደማቅ የሆነ የ እንኳን ደህና መጣሽ አቀባበል አድርገውላታል::

በሕወሓት መንግስት እስር ቤት ውስጥ ስቃይ ሲደርስባት የቆየችው ጠንካራ ሴት በበቀል ተነሳስተው ህክምና ሁሉ ሳይቀር ከልክለዋት ሲበቀሏት እንደነበር በተደጋጋሚ ሲዘገብ ቆይቷል:: ዓለም አቀፍ ተቋማት በታሰረችበት ጊዜ ሲሸልሟት የቆየችው ር ዕዮት ለበርካታ ሴቶች ተምሳሌት በመሆን ትጠቀሳለች::


ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት ዓለሙ ምናልባትም በሰሜን አሜሪካ ቆይታዋ ትምህርቷን ልትቀጥል እንደምትችል ይገመታል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48066

No comments:

Post a Comment