Saturday, August 16, 2014

ወያኔ ለተቃዋሚዎች የሚያወጣው ታርጋ

17.08.2014
አምባገነኑ የወያኔ  መንግስት 1997 ዓ/ም ወጣቶችን እያፈሰ አደገኛ ቦዘኔ፣ ወንጀል ሊፈፅሙ ሲመክሩ ፣አመፅ ለመቀስቀስ ሲሞክሩ፣ ባንክ ሲዘርፉ ደረስንባቸው እያለ ሲያስር ሲገድል አይተናል::እውነት የ 11 ዓመቱ  ነብዩ ሳሙኤል  በየትኛው ጉልበቱ ነው ባንክ ሊዘርፍ ሲል ተገኝቶ ነው ተብሎ በጠራራ ፀሀይ በአረመኔዎቹ የአጋዚ ወታደሮች ልጅነቱን ዘሎ ሳይጨርስ በአጭር ያስቀሩት ??

1997 ተሻግረን ደግሞ 2002 ዓ/ም ላይ ስንደርስ አደገኛ ቦዘኔ የምትለዋን ስም በመቀየር ህገ መንግስቱን በሀይል ለመናድ ሲሞክሩ ተያዙ አያለ ሲያስር ሲያሰቃይና ሲገድል አይተናል::

አሁን ደግሞ ምርጫ 2007 ደረሰና ከወዲሁ እንዴት አድርጌ 2007 ልሻገር ብሎ እንቅልፍ አጥቶ ሲመክር የሰነበተው የሰው በላውና አረመኔው የወያኔ መንግስት  አሸባሪ የምትለዋን ቋንቋ አሻሽሎና ፈብርኮ በማምጣት ወጣት ጀግኖች የፖለቲካ መሪዎችን ማስር ማሰቃየት ማንገላታቱን ይዞታል :::

እኛም ደግሞ ለህዝብ ሁሉ የሚጠቅም ቀና አስተሳሰብ ይዞ ክፉ አሳቢ አምባገነኖችን ማሸበር እንደሚቻል በታሰሩ ወጣት ጀግኖቻችን እያየን ትግላችንን ቀጥለናል ፣፣
 
ድል ለሰፊው ጭቁን የኢትዮጵያ ህዝብ!!

 Posted By Dawit Demelash

No comments:

Post a Comment