Monday, September 7, 2015

የህወሓት ካድሬዎች ሰሞኑን ደግሞ በፕሮፍ ላይ እየየየየየ! እያሉ ነው

ጥላቻ የማያውቁትን ሰው በጥላቻ የተመረዙ ናቸው ብለው እየከሰሱ ነው፡፡ ምን ያድርጉ ሰውዬው ለህወሓት ነቀርሳ ሆኑኮ፡፡ ባንዳ አይወዱ፣ ሀገር የሚሸጥ አይወዱ፡፡

ሌላው ይቅርና ትግራይ ውስጥ ርሃብ ሲከሰትኮ የደረሱት እነ መለስ፣ እነ ስብሃት፣ እነ አባይ አይደሉም፡፡ እነሱማ ዓለም ለምስኪኖቹ የላከውን ስንዴ አሸዋ ውስጥ ደበቁት፡፡ የሞተው ሞቶ ዛሬ እነሱ በዛ ገንዘብ ‹‹ኢፈርት›› የሚባል አቋቁመናል ብለው ሲያወሩ እንኳ አያፍሩም፡፡ የሚዘንጡበት፣ የሚበሉትና የሚጠጡት የደም ገንዘብ፣ የወገን አጥንትና ደም አይመስላቸውም፡፡ ፕሮፌሰር ግን ኪሳቸው ውስጥ የነበረቻቸውን አራግፈው ሰጥተው ባዷቸውን ነው የተመለሱት፡፡


ህወሓትና ካድሬዎቹ በልጦ የሚገኝን ሰው ይጠላሉ፡፡ እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ያሉትን፡፡ ቴዲ አፍሮም የዚሁ ሰለባ ነው፡፡ እንደ እነሱ የደም ገንዘብ ያልበላ፣ ለሀገር ያገባኛል ያለ፣ ለእውነት የቆመ ጠላታቸው ነው፡፡ እንደ እነሱ ወርዶ ካልተገኘ የማይሰጠውና የማይለጠፍበት ስም የለም፡፡ እንደ ህወሓት መሆን ከዛም ሲያንስ ከእሱ መውረድ ደግሞ እውነትም ከሰውነት መውረድ ነው፡፡ ቁልቁለት!

http://satenaw.com/amharic/archives/10224

No comments:

Post a Comment