Tuesday, January 13, 2015

ኢህአዴግ ከምርጫ ቦርድ ጋር “የምርጫ ግብረ ኃይል” ጥርነፋ እያካሄደ ነው

"ሰማያዊ፣ አንድነትና መኢአድ ከፓርቲነት ተሰርዘዋል" የብአዴን ካድሬዎች

January 13, 2015 06

ብአዴን/ኢህአዴግ በምስራቅ ጎጃም ዞንየምርጫ ግብረ ኃይልበሚል አደረጃጀት የምርጫ ቦርድን ስራ እየሰራ መሆኑን የምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ፀኃፊ አቶ ሳሙኤል አወቀ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ የብአዴን ካድሬዎች በምስራቅ ጎጃም በተለይም ደብረማርቆስ ከተማ ላይ ቤት ለቤት እየዞሩ ህዝቡ ካርድ እንዲያወጣ በሚቀሰቅሱበት ወቅት የምርጫ ካርድ አልወስድም የሚሉ ዜጎችንአልወስድም ስትል ፈርምእያሉ እያወከቡ እንደሚገኙ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪየምርጫ ግብረ ኃይልበተሰኘው መዋቅር የምርጫ ካርድ እንደማይወስዱና እንደማይፈርሙ ስለሚገልጹት ዜጎች ከሌሎች መረጃ በመጠየቅ ለማስፈራራት እየሞከሩ መሆንን ገልጸውልናል፡፡

ከዚህም ባሻገር ካድሬዎቹ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለምርጫ /ቤት አቅጣጫ እንደሚሰጡ፣ የምዝገባ ሰነዶችም በእነሱ እጅ እንደሆኑና የምዝገባ ሂደቱን እያከናወኑ እንደሚገኙ ተግልጾአል፡፡ ካርድ የማቅረብና የመመዝገብ ኃላፊነት የምርጫ ቦርድ ስራ ሆኖ እያለ ሞጣ አካባቢ የምርጫ ካርድ አለቀ ሲባል በብአዴን ካድሬዎች ትዕዛዝ ከጎዛመን ወረዳ የምርጫ ካርድ ወደ ሞጣ መላኩን በመጥቀስ ብአዴን/ኢህአዴግ ምርጫ ቦርድን ተክቶ እየሰራ መሆኑን ኃላፊ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል የብአዴን ካድሬዎች ሰማያዊ፣ አንድነትና መኢአድ ከፓርቲነት ተሰርዘዋል እያሉ እያስወሩ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን በተለይ በየገጠሩሰማያዊ ፓርቲ እውቅና የለውም፡፡ እውቅና ከሌላቸው ሌሎች ፓርቲዎች ጋርም ህገ-ወጥ ትብብር ፈጥሮ እየሰራ ነው፡፡ በመሆኑም ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ከመስራታችሁ በፊት ህገ-ወጥ መሆኑን ልታውቁት ይገባል፡፡ ራሳችሁን ችግር ላይ እንዳትጥሉእያሉ እየቀሰቀሱ መሆኑን አቶ ሳሙኤል አወቀ ገልጸዋል፡፡ በተለይ በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ዘመቻ ተከፍቷል ያሉት ፀኃፊው ብአዴኖች በከተማና በገጠር በሚኖረው ህዝብ ውዥንብር ለመንዛት እየጣሩ እንደሆነ ታዝበናል ብለዋል፡፡

http://www.goolgule.com/eprdf-and-election-board-combined-their-forces-for-the-upcoming-election/

No comments:

Post a Comment