Monday, February 15, 2016

የኢትዮጵያ የርሀብ ጽጌረዳዎች ‘በሰው መከራ የተመረቱ አበቦች ከአውሮፓ ገበያ ይደርሳሉ’

አዲስ አበባን ሁሪያዋን በመኪና እየዞሩ ቢያይዋት በተርታ የተደረደሩት በፕላስቲ የተሸፈኑት የአውሮፕላን ጋራጅ የመሰሉትን ቤቶች ማንም አያጣቸውም። ቀረብ ብሎ ላያቸው ደግሞ ለምን እንደተሰሩ ምን እንደሚከናውንባቸው መለየት ያስችለዋል። አበባ ተመርቶ ለገበያ የሚቀርብባቸው ናቸው፤ለዚያውም ለአውሮፓ ህብረት ። የአበባው ኢንዱስትሪ ህወሃት መሩ መንግስት ልማት ሰራሁ ብሎ የሚፏልልበት ነው። ዛሬ እንዲህ ያሉ ሰባ ዘጠኝ3 እርሻዎች ይገኛሉ።ከእኒህ ከሩቁ አንጸባራቂ ከሆኑት የአበባ ማምረቻ ቤቶች በተረፈ ሜዳ ላይ የተንሰራፉም ሌሎች እርሻዎች ይገኛሉ።

ህወሃት መሩ መንግስት እያበበ ስላለው የአበባ ኢንዱስትሪ ቢያወራም ተጨባጩ ሁኔታ ሌላ ነው።አጥፊ ውጤቱ ዜጎችን የበደለ፤ አየር ንብረቱንም የበከለ ነው። ይህ ደግሞ ሊደበቅ የማይቻል ነው።ሰዎች ከመሬታቸው ተፈናቅለዋል። የመጠጥ ውሃ በሚጎዱ መርዞች ተበክሏል።ሰዎች ለረጅም ሰዓታት በመስራት ይበዘበዛሉ።ይህ ለጥቂቶች ሲሳይ ለብዙሃን ስቃይ የሆነን አሳዛኝና አፋኝ የፖለቲካ ና የኢኮኖሚ ውጥረት ነው። ዛሬ በኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ የለውም።በቀበሌ፤ባውራጃ፤ባገር አቀፍም ቢሆን በህወሃት ጨቋንኝ መዳፍ ተይዞ ይገኛል።

ጥቂት ኪሎሜትሮች ሄደት ብዬ አንድ በጭቃ ምርጊት የተሰራ የቆርቆሮ ቤት አገኘሁ።ምርጊቱ ገና የደረቀ አልነበረም።ርጥቡን ጭቃ ነካ እያደረግሁ

“እዚህ መቼ አመጣህ እና እንዴት ሰፈርክ ?” ብዬ ባለቤቱን ጠየቅሁ። “አምስት ቀን በፊት ልጄ ረድቶኝ” አለኝ “ከዚህ በፊትስ የት ትኖር ነበር ?”
“እኔና ቤተሰቤ እዚሁ በዚህ ግድም እንኖር ነበር” “የሞላ ቤት ነበረን። እኔና ባለቤቴ ልጆች እናሳድግበት የነበረ”” “ለምን ታዲያ ቦታችሁን ለቀቃችሁ ?” አስከትዬ ጠየቅሁት።

“በግዳጅ ተፈናቅለን” አለኝ
“ምን ማለትህ ነው ተገደን ስትል ማንስ አስገደደህ?” አልኩት
“በዚች አገር ያልወደድከው እንድታደርግ ማድረግ የሚችል መንግስት ነው” “ለምን እንድትፈናቀል ያደርጋሉ? መሬቱስ ያንተ አይደል? “ አልኩት


“መሬቱማ የኔ ነው እነሱ ግን ለአበባ አምራቾች ሊሰጡት ፈልገው ነው። አበባ አምርተው ውጭ አገር ለመሸጥ ለሚፈልጉ” “ስትፈናቀል ካሳ አግኝተሃል?” እዲነግረኝ ገፋፋሁት።

“ትንሽ ምንዛሪ አንድ በግም የማትገዛ ሰጡኝ። አልቀበልም አልኩ” አለኝ ኔዴቱ እንዳዲስ እየተሰማው።
“መላ ቤተሰቤን ይዠ ጎዳና ላይ መውደቁ ይመራል” አለኝ


“ይህ መሬት ካያት ከቅድማያት የወረስነው። እትብታችን የተቀበረበት። ሁለት ዓመታት ጎዳና ተዳዳሪ ሆንን። ሜዳ ላይ እየተኛን። ለምነን እየበላን።ራሳችንን ችለን እንኖር የነበረ ዛሬ በቀን አንዴም አንበላ። ይህ ለውጥ ኑሮአችንን አሰተጓጎለ ህብረተ ሰባችንን ጎዳ።ለማኞች አደረገን።”

“ማነው በዚህ የሚጠቀም?” አልኩት

“የመንግስት ባለስልጣኖችና ጓደኞቻቸው” አለኝ የድሮ ቤቱን ምስል እያሳየኝ። አያዳመጥሁት ይህ በኔና ቤተሰቤ ላይ ቢደርስ ምን አደርግ ይሆን እያልኩ ባሳብ ዋዠኩ።ባንዴ ሃዘንም ንዴትም ዋጠኝ። ያየሁት በደል በሚሊዮኖች ቤት ተከስቷል።ሃዘን ብቻ ይበቃል ? አልኩት እራሴን።

ብሩክ በመጀመሪያዎቹ ሃያ አመቶችዋ ላይ የምትገኝ ወጣት ሴት ናት።ለሶስት ዓመታት በአበባው ማምረቻ ቤት ሰርታለች።ከስራ ውጭ አግኝቼ ስለ ስራዋ ሁኔታ እንድት ነግረኝ አደረግሁ።

“በአበባው ማምረቻ ቤት ስራሽን ትወጅዋለሽ?” ስላት
ሳቅ ብላ “ምንስ ምርጫ ኖሮኝ” አለችኝ። “ሌላ ስራ የለ ።ያገኘሁት ይሄው ነው።” አለችን በክሰል ምድጃ ቡና እየቆላች። እጆችዋ ላይ አዲስና የቆዩ ቁስሎችን አያለሁ።

“በስራሽ ላይ ነው እንዲህ የቆሳሰልሽው?” አልኳት ወደ ቁስሎችዋ እየጠቆምሁ። “አደጋ መከላከያም የለሽ?” “እንዲያውም “ አለች
“የጅ ጓንት ሆነ ሌላ እንዲው ምንም የለንምን ?” ብዬ አከታትዬ ጠየቅኋት።


“ጤናማ ነበርኩ። ይሄው ዛሬ ግን መተንፈስ ያስቸግረኛል። ይህ የሆነው ስድስት ወራት በአበባው ማምረቻ ቤት ከሰራሁ በኋላ ነው። ሀኪም ቤት ስሄድ በስራሽ የተነሳ ነው ብለውኛል። መተንፈስ ይጨንቀኛል። ቆዳዬን ያሳክከኛል። ያስለኛል።” አለችን ሀዘን በሞላው ገጥታዋ።

የኢትዮጵያው “የራብ ጽጌረዳዎች” በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ወይም ሴራሊዮን ከሚመረተው “የደም አልማዝ” የተለዩ አይደሉም።ሁለቱም የሰው መከራና ስቃይ ውጤቶች የተፈጥሮ ውድመቶችም ናቸው።ሁለቱም የአምባገነኖች የሃብት ምንጭና መደጎሚያ ናቸው።ባአበባው ሽያጭ የሚገኘው የውጭ ምንዛሪ በዓለምም በአፍሪካ አቻ የማይገኝለት አምባገነን ያነግሳል።ለወያኔ ሲሳይ ነው።ከዚህም በላይ አበባ ማምረቻው መሬት የሚበላ እህል ማምረቻ የነበረ ነው።ስለሆነም ሚሊዮኖች ለራብ ተዳርገዋል።
ጃነዋሪ 26 2016 የተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያን ሁኔታን ሲገልጥ “ቀስ እያ እየቀረበ ያለ ትልቅ አደጋ” ብሎታል። ዛሬ ጦርነት እዳፈራረሳት ሶርያ ያስምስለዋል። “ዛሬ ሁለት ትላልቅ ቅድሚያ የሰጠናችው የአደጋ ቀጠናዎች አሉን።ሶርያ አንደኛ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ናት።” ብለዋል ካሮላይን ማይልስ። ማዳም ማይልስ Save The Children የተባለው ህጻናት አድን የተራድኦ ድርጅት ዋና አስተዳዳሪ ናቸው።የኢትዮጵያ ሁኔታ “ቀስ እያ እየቀረበ ያለ ትልቅ አደጋ” ተብሎ ሲገለጥ ህወሃት “ጥጋብ ነው በምግብ ራሳችንን ችለናል” ብሎ በለፈፈ ማግስት ነው።

በሜይ 28 2014 የህወሃት ሃያ አራተኛው የድል በዓል ሲከበር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ “ከራብ በመላቀቃችን እንኮራለን።ከዚህ ወዲያ በራብና ጠኔ መታወቃችን ቀርቷል” ብሎ ነበር።

በአፍሪካ ለዘለቄታው የቅኝ አገዛዝ የእርሻ ስራን አመሳቅሎአል።ነፍስ ወከፍ ራሳቸውን የቻሉ ገበሬዎች ተፈናቅለው በትላልቅ ገንዘብ አምንጭ ሰብሎች ለምሳሌ ቡና፤ኮካዎ፤ትንባሆ፤ስኳር፤ጥጥና ጎማ ተተክተዋል።እኒህ ለውጭ ንግድ የሚመረቱ ናቸው። ከበርቴዎችን ቅኝ ገዥዎችን የሚያከብሩ ማለት ነው።በዚህ ሂደት ታዲያ ሚሊዮኖች ደህይተዋል።ካባታቸው መሬት ተፈናቅለዋል። ታሪካቸው ጠፍቷል።ኢትዮጵያ የሚካሄደውም የአበባ እርሻ ምርት ከቅኝ አገዛዙ ልዩነት የለውም።ያው ቅኝ አገዛዝ ያደረገው እየተደገመ ነው። የጥንቱ ቅኝ “አገዛዝ ኋላ ቀር ህዝቦችን ለማሰልጠን” ይባልም ነበር።በ21 ኛው ክፍለ ዘመን ይህን ማለት ያዳግታልና የአሁኑ “ኢንቬትሜንት፤አምራችነት ። ስራ ፈጠራ። ውጭ ባለ ሃብቶች ጋር መስራት” የሚል ስም ይሰጠዋል። ስም እንጂ ልዪነት የላቸውም። ዘመን አመጣሽ ባርነት እንጂ ከዚያ ከጥንቱ ቅኝ አገዛዝ የሚለይ አደለም።

በቅርቡ አንድ ጓደኛዬ እንዲህ ብላ ጠየቀችኝ። ይህን እስቲ መልስልኝ አለችኝ። “እንዴት ሁኖ ነው አንድ በባዛት አምሮበት የተመረተ የአበባ ምርት ለአውሮፓ ገበያ ሊያቀርብ የቻለ አገር የራሱን ህዝብ መመገብ ያልቻለበት ?” በተጨማሪ “እንዴት ብሎ ነው በኢኮኖሚ እድገት ክ10 እስክ 11 እጅ ለተከታታይ ዓመታት ውጤት አምጥቻለሁ የሚል መንግስት ከዓለማቀፍ ተራድኦ ህዝቡን ለማብላት እርጥባን ጠያቂ የሚሆነው?” እኒህ ማንም ጤናማ አእምሮ ያለው ሰው የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች ናቸው። በተለይ የዜና ስርጭቱ ሁሉ በራብና ድርቁ ላይ ሲሆን። የኒህ ጥያቄዎች መልስ ከተራበውና ከተጠማው አርሶ አደር ስቃይ ይገኛል። ከወጣትዋ የአበባ ማምረቻ ሰራተኛ ይገኛል።ከመክረኛውም ህዝብ ሁሉ። ጭብጡ ሁኔታ ይህ “እድገት” ይህ “አምራችነት” የህዝብ ኑሮ ጨርሶ እያወደመ፤በጣም ተፈላጊ የሆነው ውሃ ለአበባ ማምረቻ ይውላል።ተፈጥሮም በመርዘኛ ጸረተባይ ዲ ዲ ቲ እና ሌላ መዳኒት ይበከላል።

የዛሬውን የቫላንታይን ቀን በትኩሱ በተቆረጡ አባቦች ስታከብሩ በግፍ ከኖሩበት ቀዬ የተፈናቀሉትን ገበሬዎች አስቧቸው። ወጣትዋን ብሩክን አስቧት።በመርዝ የሾቀ ቦታ ሰርታ የምትኖረውን አስቧት።ከሁሉም በላይ 10 ሚሊዮን ራብተኞችን ከዚህም 400000 ህጻናት ለጠኔ ተዳርገው ለም መሬታቸው እህል ሳይሆን አበባ የሚመረትበት መሆኑን እናስብ። እራሳችሁን ደግማችሁ ጠይቁ እንዴት አበባ ለአውሮፓ አቅራቢዋ አገር ራብተኛ ልትሆን ቻለች ብላችሁ።እንዲያው ምን ህሊና ይፈርዳል እንዲህ የመረተውን አበባን መግዛት ? ከበርቴ ትርፉን ሲል ሚሊዮኖች የለት ጉር ያጣሉ። ይህ ወንጀል ነው።ተባባሪም ደጋፊም አትሁኑ። ክዚህ ይልቅ ለኢኮኖሚም ለፖለቲካም ፍትህ የምትታገሉ ሁኑ።

ደራሲውን ለማግኘት

alem6711@gmail.com

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/50970


No comments:

Post a Comment