Sunday, April 24, 2016

በጋምቤላ ሕዝብ ለተቃውሞ ወጣ – “መንግስት ግድያውን ለፖለቲካ ፍጆታና ኦሮሚያን እና ጎንደርን ለማረጋጋት ተጠቅሞበታል” – ጋምቤላ አልተረጋጋችም

በጋምቤላመንግስት የለም ወይ?” ያሉ ነዋሪዎች ሰሞኑን የተፈጸመውን ግድያ በማውገዝና መንግስትም ይህንን የሕዝብ ሞት ለራሱ የፖለቲካ ፍጆታ አዎሎታል በሚል ሕዝቡ በነቂስ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን ሲያሰማ መዋሉን ለዘ-ሐበሻ የደርሰው መረጃ አመለከተ::

ልጆቻችን ይመለሱ…. በሃገራችን ሰላም አጣንመንግስት በኛ ሞት የፖለቲካ ድል ማግኘቱን ያቁም…” እና ሌሎችንም መፈክሮች ሲያሰሙ የነበሩት የጋምቤላ ነዋሪ ሰልፈኞች መንግስትን ሲያወግዙ ውለዋል::

ሕፃናቱን ለማስለቀቅ ከብቤያለሁ እያለ ሲፎክር የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት ወታደር እስካሁን ልጆቹን ባያስለቅቅም የትናንቱን ገድያ ተቃውመው ለሰልፍ የወጡትን ኢትዮጵያውያን ግን ዛሬ ጋምቤላ ላይ ሲቀጠቅጥና ለመበተንም ሲሞክር ታይቷል::
በጋምቤላ የተለያዩ ከተሞች በአሁኑ ወቅት መረጋጋት አለመኖሩን የሚገልጹት የአካባቢው ምንጮች ማን ከየት መጥቶ ገድሎ እንደሚሄድ እንደማይታወቅና ሕዝቡም እርስ በራሱ ተፈራርቶ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል::

በጋምቤላ ጉዳይ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት የታህሳስ 13 መታሰቢያ ንቅናቄ ተወካይ አቶ ኦዶል ኦዶል ለዘ-ሐበሻ በሰጡት አስተያየት የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት የሰሞኑን ግድያ የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ አድርጎታል ብለዋል:: እንደ እርሳቸው አባባል መንግስት እየነገረን ያለው ትንሹን ግድያና በተለይም ሙርሌዎች ያደረሱትን እንጂ ከዛ በፊት 15 ቀናት በፊት ስለሞቱት ሰዎች የነገረን ነገር የለም ብለዋል::: እንደ ኦዶል ገለጻ መንግስት በኦሮሚያና በጎንደር የተነሳበትን ሕዝባዊ ቁጣ ለማብረድና ሃሳብን ለማስቀየር የሙርሌዎችን ግድያ ከመጠቀሙ በላይ ምንም ያደረገው ነገር የለም ብለዋል::

በተለይም በትናንትናው ዕለት በጋምቤላ በአሰቃቂ ሁኔታ ስለተገደሉት 15 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ጠይቀናቸውገዳዮች ናቸው የተባሉት ሰዎች የገደሉት አማሮችን እና ኦሮሞዎችን ብቻ መርጠው ነው; ይህም ማን ከበስተጀርባው እንዳለ ያሳየናልብለውናል::

አቶ ኦዶል ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት የጋምቤላ አክቲቭስቶች ሕዝቡ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ መረጃዎችን ለሕዝብ ቶሎ ቶሎ ማድረስ አለባቸው ብለዋል:: ሕዝቡ መንግስት የሚለውን ብቻ በመስማት መንግስት አሸናፊ እንዳይሆን መረጃዎችን ከፎቶዎች ጋር በማውጣት ማጋለጥ ይገባቸዋል ብለዋል::

ይህ እንዲህ እንዳለ ትናንት ጃዊ በተባለ የስደተኞች ጣቢያ ስለተገደሉት ኢትዮጵያውያን ጉዳይ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሏክ ቱት ኩዃት ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የሞቱትን ቁጥር ወደ 10 አሳንሰውታል:: ለትናንቱ ግድያ መነሻም ሴቭ ዘችልድረን የተባለ የግብረሰናይ ድርጅት መኪና በስደተኞቹ ካምፕ ላይ በደረሰበት አደጋ የሁለት ስደተኞች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ ነው ሲሉ ተናግረዋል:: ስደተኞቹ ከመኪና አደጋው ጋር ተያያዥነት በሌላቸው 10 ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸማቸውንም ገልጸዋል::

ጋምቤላ ተወጥራለች…. -ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን እንዳገኘች ትመለሳለች::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/53659


No comments:

Post a Comment