Sunday, September 22, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ በድምቀት ተካሄደ! (ፖሊስ ከ4 ኪሎ እንዳያልፉ አድርጓል)

september 22.2013

በአሁኑ ሰዓት ሰማያዊ ፓርቲ ከሶሰት ወር በፊት የጠራውን ሰልፍ እያካሄደ ይገኛል:: ሰልፉ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሮ ነበር የሰልፉ መድረሻ መሰቀል አደባባይ ቢሆንም ሕዝቡ አራት ኪሎ አካባቢ ሲደርስ የአዲስ አበባ ፓሊሶች ሰልፈኛውን ወደ መሰቀል አደባባይ እንዳይሄድ ሲያግዱ የፌድራል ፓሊስ ደግሞ በርቀት እየተመለከተ ነው::ሰልፈኞቹ ወደ ስማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዲመለስ ተደርጓል ሕዝቡ ግን ድምጹን ከማሰማት ወደኋላ አላለም::
ርዮት ትፈታ! ውብሽት ይፈታ! እሰክንድር ይፈታ! አንዷለም ይፈታ! አቡበከር ይፈታ! ፍትህን መጠየቅ አሽባሪነት አይደለም!! ነፃነት እንፈልጋለን !! እኛ አሽባሪ አይደልንም! ፍትሕ እንፈልጋለን! የሙሰሊም ኮሚቴ ይፈቱ! ዜጎችን ማፈናቀል አግባብ አይደለም! አንለያይም! አንለያይም! ፍትህን ያሉ ቃልቲ ገቡ!! አሽባሪ አይደለንም! ፍትህ ናፈቀኝ! ድምፃችን ይሰማ!! ፍትሕ እያሉ ቃልቲ ገቡ! ውሽት ሰለቸን! ፍትህ ናፈቀን!
ሰማያዊ ፓርቲ ወያኔ የሚረግጡትን መሬትና የማይረግጡትን ምድር ወስኖ ሰልፈኛውን ከቦ እንዳሰቡት መስቀል አደባባይ መድረስና ከህዝብ መገናኘት እንዳይችሉ በማድረጉ ወደ ቢሮ በመመለስ የሰልፉን በሰላም መጠናቀቅ አብስረዋል፡፡ ይህ ትልቅ የአመራር ብቃትን፤ ሀላፊነትንና ለህዝብ ወገንተኝነትን የሚያሳይ ነዉ፡፡ ወያኔዎች ሰልፉን ለማቆም ባትወስኑ ኖሮ ህዝብ ላይ መተኮስን እንደልማዳቸ ይፈፀሙት ነበር፡፡ብስለት የተሞላው አመራር በማድርጋችሁ አድናቆት ይገባችኀል፡፡ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ ህዝብ ያሸንፋል!









No comments:

Post a Comment