Thursday, January 21, 2016

የአጋዚ ሠራዊት የወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን መኝታ ክፍል ሰባብሮ ገባ


በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ሕዝባዊ ቁጣ እንደቀጠለ ባለበት በዚህ ሰዓት ሕወሓት የሚመራው መንግስት አጋዚ ሰራዊት በነቀምት ወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን መኝታ ቤቶች ሰባብሮ በመግባት በንብረት ላይ ጉዳት ከማደርሱም በላይ የተማሪዎችን ውድ እቃዎች መዝረፉንም የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከስፍራው አስታወቁ::

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት በወታደሮች መከበቡን ያስታወቁት ምንጮቻችን የሴቶችም ሆነ የወንዶች መኝታ ክፍሎች ተሰባብረዋል:: ብዙ ዋጋ ያላቸው ንብረቶችም በነዚሁ ፖሊሶች ተወስዷል:: ከዚም በተጨማሪ ተማሪዎች ከመቀጥቀጣቸውም በላይ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ተማሪዎች ወደ እስር ቤት ተወስደዋል::

ፖሊሶቹ አሁንም ጊቢውን በመቆጣጠር ተማሪዎቹን በማሸበር ላይ ናቸው::

በኦሮሚያ ክልል የተነሳው የሕዝብ ቁጣ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች የቀጠለ ሲሆን በዚህ ሳምንት ብቻ ከ6 የማያንሱ ተማሪዎች መገደላቸው ተዘግቧል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/50148


No comments:

Post a Comment