Friday, January 23, 2015

አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል! አርማጭሆ ሆይ! ዛሬም እንደትላንቱ ከጎንህ ነን!


ጀግናው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ !

የኢትዮጵያ ሃገርህና የህዝቦቿ ቀደምት ጠላቶች በተደጋጋሚ ያጠመዱብህን እኩዩን በዘር፣ በጎጥና፣ በመንደር የመከፋፈል ሴራ
በማክሸፍ በአንድነትህ አደባይተህ ወደ መጡበት እንደመለስካቸውና ህዝብህን ከውርደት፣ ሃገርህን ከጥፋት እንደታደግክ
ታሪክ ህያው ምስክር ነው፡፡

ዛሬም ባንዳውንና ተላላኪውን የህወሃት ዘራፊ ቡድን ሃገርህ ኢትዮጵያን ሲያፈርስ፣ ወደብና ድንበር አልባ ሲያደርግ፣ ህዝቦቿን
በዘር፣ በጎሳና፣ በጎጥ እየከፋፈለ ሲያተራምስና ሲያጫርስ እያየህ በድንዛዜ የምትቆዝምበት ጊዜ አይደለምና ዛሬ ነገ ሳትል
ለነፃነትህና ለአንድነትህ ቆርጠህ በመነሳት ታሪካዊ ጠላቶቹን በጀግንነት እየተፋለመ ከሚገኘው የጎንደር ህዝብ ጎን ዛሬውኑ
ተሰለፍ!

ጎንደር ሆይ !

ባንዳውና ተላላኪው የትግራይ ወራሪ ሃይል በአለፉት አስርት አመታት ለም መሬቶችህን ለመንጠቅ ተከዜ ድንበርህን በማን
አለብኝነትና በሃይል ተሻግሮ ከመጣ ወዲህ የወልቃይት፣ የጠገዴና፣ የጠለምት ዘርህ ላይ የፈፀመው የማጽዳትና በትግሪያዊነት
የመተካት ወንጀልና ግፍ እንዳለ ሆኖ፤ እነሆ ዛሬም እንደገና በእብሪት አርማጭሆ፣ መተማንና፣ ቋራን በመውረር ወደ ትግራይ
ለመጠቅለልና ዘርህንም በትግሪያዊነት ለመተካት እነሆ በእብሪት ዘምቶብሃል፡፡

ጀግንነት ማንነትህ ነውና ጨርቄን ማቄን ሳትል በጀግንነትና በፅናት እራሱን ከወረራ ለመከላከል እየተፋለመ ከሚገኘው
ከጀግናው የአርማጭሆና አካባቢው ማህበረሰብ ጎን በመሰለፍ ጠላትህ የሆነውን የትግራይ ወራሪ ሃይል በማንበርከክ ወገንህን
ከጥቃት፣ ሃገርህን ከጥፋት፣ ታሪክህን ከውርደት ትታደግ ዘንድ አደራችን ፅኑ ነው! 

የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ወገናችን !

ለአለፉት አራት አስርት አመታት በባንዳውና በተላላኪው የህወሃት እኩይ ቡድን በተከፈተብህ ዕርስትህን፣ ማንነትህንና፣ ዘርህን
ከምድረ-ገፅ የማጥፋት ሁለገብ ዘመቻ ሳትበገር፤ ይልቁንም በገቡበት እየገባህ፣ በሚያሴሩበት እየደረስክ ባንዳዊ ተልዕኳቸውንና
እኩዩን የወረራና የመስፋፋት አባዜያቸውን በአንድትህ የመከትክበትና ያኮላሸህበት ታሪክህ ለትውልድና ለሃገር ታላቅ ኩራት

ሆኖ ለዘለዓለም ሲያበራ ይኖራል

እነሆ ዛሬም ድረስ እራሱን “የትግራይ ነፃ አውጭ” እያለ የሚጠራው የባንዳዎችና የዘራፊዎች ቡድን እንደ ጌቶቹ ወደ
ማይቀርለት የወራሪዎችና የከሃዲያን ታሪካዊ መቃብር ከመውረዱ በፊት በጣረሞት ላይ የምትገኘውን እንጥፍጣፊ እኩይ
እስትንፋሱን አሰባስቦ የአጥፍቶ መጥፋት መርዙን በወገንህ ላይ ሊረጭ በመቃተት ላይ ይገኛል፡፡

ይልቁንም ዛሬ ደጀንህን የአርማጭሆንና የአካባቢውን ማህበረሰብ ማንነቱን ለማጥፋትና በትግሪያዊነት ለመተካት ከፍተኛ የሆነ
ሁለገብ ወረራ ተፈፅሞበታል፡፡ በተለይም ይህ ከትግራይ የዘመተው ወራሪ ሃይል በባዕዳን የወረራ ዘመን እንኳን ታይቶ
በማይታወቅ ሁኔታ አካባቢውን እያመሰ ይገኛል፡፡

አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል ነውና! በቀደመው ማንነትህና አኩሪ ታሪከህ ላይ በፅናትና በአንድነት በመቆም፣ ጠላቶችህ
በደገሱልህ የጎጠኝነትና የመንደርተኝነት ወጥመድ ሳትጠለፍ፣ ይልቁንም በአንድነትህና በኢትዮጵያዊ ማንነትህ እየታገዝክ እኩይ
ሴራቸውን እየበጣጠስክ፣ ዛሬ ነገ ሳትል በህብረት በመነሳት ታላቅና ታሪካዊ ተጋድሎን እያደረገ ከሚገኘው የአርማጭሆና
አካባቢው ወገንህ ጎን በመሰለፍ ጥንተ ጠላትህን ዛሬም እንደ ትላንቱ ታደባዬው ዘንድ ታሪካዊ ጥሪ አቅርበንልሃል!

እኛም በኢትዮጵያና በመላው ዓለም የምንገኝ የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ተወላጆች ዛሬም እንደ ትላንቱ በአንድነትና በፅናት
ከጎንህ መሰለፋችንን ስናረጋግጥልህ በታላቅ ኩራት ነው !

ድል ለኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች !


ታህሳስ 2007 ዓ.ም

http://ethiolion.com/Pdf/01092015Support_Armacheho.pdf



No comments:

Post a Comment