Monday, January 5, 2015

ዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ለአስራ አምስተኛ ጊዜ ተቀጠሩ


በዛሬው እለት በካንጋሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ከዚህ ሁሉ ኢ-ፍትሃዊ እስር በኋላም ቢሆን ከፊታቸው ላይ ሳቅና ፈገግታን ሊነጠቁ ያልቻሉ መሆኑ በግልጽ ለአምባገነኖች እና አሽከሮቻቸው አሳይተዋል:: በሙሉ ራስ መተማመን ስሜት እና በታየው ብሩህ መንፈሳቸውን ተላብሰው ካንጋሮ ፍርድ ቤት ይደረሱት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የአሸናፊነት ስሜት በፊታቸው ይነበባል::ፖሊስ ጉዳዩን የሚከታተሉ እና በፍርድ ቤቱ የተገኙትን ስልካቸውን እንዲያጠፉ ያደረገ ሲሆን በችሎት ክተሰየሙት ዳኛ አንዱ መቀየራቸውም ታውቋል:;እንዲሁም ፖሊስ ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጉዳዩን ሊክታተሉ የመጡትን በአይን እንኳን እንዳይነጋገሩ ሲያዋክብ ታይቷል::


በኢሕአዴግ አቃቢ ህግ የተፈበረኩ የሃሰት ክሶች ላይ ቡድን ድርጅት የተባሉት፣የተከሳሾች የሥራ ድርሻ እንዲሁም የ48ሺህ ብር ጉዳይ አልተሻሻሉም ከተባሉት ክሶች ውስጥ ተካተዋል።በተጨማራም የተለያዩ ስልጠናዎችን ወስደዋል የተባለው በዝርዝር እንዲቀርብ አዟል። ከዚህ ውጪ ያሉ የክስ ማሻሻያዎች ተቀባይነት አግኝተዋል። ፍርድ ቤቱ አልተሻሻሉም ብሎ የጠቀሳቸው አራት ነጥቦች በድጋሚ ተሻሽሎ እንዲቀርብ ለጥር 6 ቀጠሮ ሰጥቷል። (ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው)

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/37770

No comments:

Post a Comment