Saturday, January 3, 2015

ወያኔ የጉራጌ ማህበረሰብ ከሌላው የህብረተሠብ ክፍል ለማጋጨት በወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ እየፈጸመው ያለው ደባ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገነዘበው ይገባል

ከላይ በርዕሱ ላይ የጉራጌ ማህበረስብ ከሌላው የህብረተሰብ ክፍል ብዬ የተጠቀምኩት ወያኔ/ኢህአዴግ በጉራጌ ዞን በቸሃ ወረዳ ጉብሬ ከተማ ላይ በህዝብ ድጋፍና እርብርቦሽ የተመሠረተችው ወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ ውሥጥ በተግባር እያደረገ ያለውን ጉዳይ ነጠል አድርጌ ለማሣየት እንጂ ወያኔ በሁሉም የሐገራችን ክፍል የተሠማራበት እኩይ ተግባር ጠፍቶኝ እንዳልሆነ ልትረዱልኝ እፈልጋለሁ። ባጠቃላይ ወያኔ ኢትዮጵያ ሐገራችን ለማጥፍት ግቡ አድርጎ የሚንቀሳቀስ የትኛውንም ህዝብ ሊወክል የማይችል በጥቂት ማፍያ ወንበዴዎች የሚመራ የሆዳሞች ድርጅት ነው። የመጨረሻ የሆነውን ሐገር የማፍረሥ አላማቸው እውን እሥኪሆን ድረሥ ሀገሪቷን መምራት ስለ ሚፈልጉ ህዝቡ አንድ እንዳይሆን የተቻላቸውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኻላ እንደሚያደርጉ ልንገነዘብ ይገባል።
ከፋፍለህ ግዛ (በዘር) መርህ የሚከተለው ወያኔ ላለፉት 23 ዓመታት ህዝቡን እርስ በርስ እንዳይተማመን፤ እርስ በርስ እንዲተላለቅ፤ እርስ በርስ እንዲጥላላ አያሌ ሥራዎችን ሠርቷል። ህዝቡን በዘር፣ በሐይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት፣ በእምነትና በሌሎችም ተመሣሣይ ጉዳዮች ለመከፍፈል በፖሊሲ ደረጃ ተቀርጾ ሲመሩበት የነበረና አሁንም ያለ ህዝብ ፍቃድ የገፉበት ጉዳይና ፖሊሲ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ከ3000 አመት በላይ ተከባብሮና ተቻችሎ፣ ያሉትን ልዩነቶች አጥብቦ የኖረባት ሐገር ዛሬ የዘር ፖለቲካን በማራመድ በህዝብ ዘንድ ጥላቻን በማሥፈንና ልዩነቶችን በማስፋት የኢትዮጵያ ህዝብ ሆድና ጀርባ ለማድረግ ተግተው እየሠሩ ነው። ወያኔ በዚህም ተግባሩ ከልማት መንገድ ይልቅ የጥፍት መንገድ መምረጡን ያመለክታል።

ወያኔ በዚህም መሠሪ ተግባሩ ሙሉ በሙሉ ተሳክቶለታል ማለት ባይቻልም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ግን የዚህ ተግባር እርዝራዦች፣ አደር ባዮች፣ አጎብዳጆችና ሆዳሞች ግን አልጠፉም። አንዳንዶቻችን የወያኔ መሠሪ ተግባርና አላማ ጠንቅቀን የምናውቅ ብንሆንም ከወጥመዱ ማለፍ ያልቻልን ደካሞችም መኖራችን ግን አልቀረም። ወያኔ ሁላችንም ጠባብና ትምክተኛ እንድንሆን እንደሚፈልግ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠንቅቆ የሚያውቀው ይመስለኛል። ይህ ከሆነ ደግሞ ሁላችንም ወጥመዱ ውስጥ እንዳንደናቀፍ አስፈላጊ ጥንቃቄ መውሠድ ይጠበቅብናል። ያ ሳይሆን ሲቀር ግን እራሣችን ወያኔ ባዘጋጀው መረብ ውስጥ ተጠልፈን ትክክለኛ መሥመር እየተከተሉ ያሉትን ማደናቀፋችን ወይም እየተከተሉት ላለው የለውጥ ጎዳና እንቅፍት መሆናችን አይቀሬ ነው። በዚህ ጊዜ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የወያኔ መሣሪያ ሆነናል ማለት ነው።

ወደ ዋናው ጽሁፌ መለ ወያኔ በወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ እያደረገ ያለውን ነገር አሣሣቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ምክንያት ነው። ይህም ዩኒቨርሥቲው ውጥ ወያኔ የራሱን ሠዎች በማዘጋጀት ፍራሽ ከተደረደረበት ክፍል እስከ የተማሪ ማደሪያ የሆኑትን ዶርሚተሪዎችን በማቃጠል ከሌላ ክልል የመጡት ተማሪዎች ድርጊቱን እንደፈጸሙት በማድረግ የጉራጌ ማህበረሰብ ከሌላ ክልል ለመጡትን ተማሪዎችም ሆነ ስለ ሌላው ማህበረሰብ የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖረው ለማድረግና እርስ በርስ ለማጋጨት ነው። 

በመሠረቱ የጉራጌ ማህበረሰብ በሁሉም የሐገራችን ክፍል በተለያዩ የግልና የመንግሥት መሥሪያ ቤት በተለይ የንግድ ሥራ ላይ ተሠማርቶ የሚሠራ ህዝብ እንደመሆኑ መጠን ከሁሉም የሐገራችን ክፍል የሚመጡ ሰዎች ጋር በደንብ የመገናኘት አጋጣሚ ስላለው የኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል ጨዋ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። በዚህም ምክንያት ወያኔ የሚፈጸማቸው ድርጊቴች ወይም የወያኔ ሴራዎች ጠንቅቆ የሚያውቅ ሕዝብ ነው።

ባሳለፍነው ሳምንት ታህሳስ 25, 2014 እ፣ኤ፣አ ጠዋት በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሁለት ተማሪዎች (አንደኛው ከአማራ ክልል የመጣ, ሁለተኛው ከኦሮምያ ክልል) መጣላታቸውን ተከትሎ ከኦሮምያ ክልል የመጡት ተማሪዎች የግቢው ህንጻዎች ላይ በሌሊት አደረሱት የተባለውን ጉዳት ተከትሎ የአካባቢው ማህበረሰብ ላይ የፈጠረው መጥፎ ስሜት ነው። እዚህ ላይ ሁሉም የጉራጌ ማህበረሰብ ማወቅ ያለበት ነገር ቢኖር የዚህ ሁሉ ተጠያቂው ወያኔ መሆኑን ነው። ምክንያቱም የኦሮሞ ህዝብ ለብዙ አመታት ከጉራጌ ማህበረሰብ አብሮ የኖረና ተጋብቶ የተዋለደ እንደመሆኑ መጠን ምንም አይነት ችግር እንደሌለባቸው ነው። ስለዚህ የተፈጠረው ድርጊት በማንም ይሁን በማን ወያኔ ህዝቡን ለማጋጨት ሆን ብሎ የፈጸመው እንጂ ከኦሮሞ ማህበረሰብም ሆነ ተማሪዎች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው ነው። ለወደፊትም ቢሆን ጥንቃቄ ልንወስድ ይገባል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/37720

No comments:

Post a Comment