Wednesday, March 19, 2014

በቦስተን እና አካባቢዋ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፤ የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የውደሳ እና የምስጋና ቀን በቦስተን

March 19th, 2014

በቦስተን እና አካባቢዋ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የውደሳ እና የምስጋና ቀን በቦስተን
እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2006 / Sunday, March 30, 2014
ከቀኑ 2፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት ድረስ/From 2:00 PM to 6:00 PM
በካምብሪጅ፤ ዋልደን የኮሚኒቲ አዳራሽ፣ 21 ዋልደን ስኩዬር ሮድ፤ ካምብሪጅ፤ ማሳቹሴትስ 02140፣
(Walden Square Community Rm, 21 Walden Sq. Rd., Cambridge, MA 02140)
በእለቱ የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበር እና በወቅቱ ላለፉት 30 ወራቶች በእስር የሚማቅቀውን የሰብአዊ መብት ታጋይ፤ የፖለቲካ መሪ እንዲሁም የሕሊና እስረኛ የሆነውን የአንዱአለም አራጌን የውደሳ እና የምስጋና ቀን በካምብሪጅ፤ ዋልደን የኮሚኒቲ አዳራሽ፣ 21 ዋልደን ስኩዬር ሮድ፤ ካምብሪጅ፤ ማሳቹሴትስ 02140፣ (Walden Square Community Rm, 21 Walden Sq. Rd., Cambridge, MA 02140) ተዘጋጅቷል፤
በእለቱ

• የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የሕይወት ታሪክ እና በኢትዮጵያ ውስጥ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር በሚደረገው የሰላማዊ ትግል ያደረገውን አስተዋጻኦ በተመለከተ የተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ይቀርባል፤
• የአንዱአለም አራጌ “ያልተኬደበት መንገድ” በሚል ርዕስ በእስር ቤት የጻፈው እና በጉጉት የሚጠበቀው መጽሀፍ በቦስተን አካባቢ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በይፋ ይመረቃል፤ ይሸጣል፤ የመጽሀፉ ሽያጭ ገቢም፤ ሙሉ በሙሉ በችግር ላይ ላሉት ለአንዱአለም አራጌ ቤተሰብ መርጃ ይውላል፤
• በእለቱ ሌሎች የሕሊና እስረኞችም ይዘከራሉ፤ ይታወሳሉ፤ ይወደሳሉ፤
በእለቱ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ ለማስወገድ እና የሰው ልጅ መብት እንዲከበር እንዲሁም ሁሉም ኢትዮጵያውያን በመከባበር የሚኖሩባት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው የሰላማዊ ትግል የአንድ ፓርቲ ወይም ግለሰብ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚመለከት በመሆኑ በቦስተን አክባቢ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዝግጅቱ ላይ በመገኘት አንዱአለም አራጌን እና መሰል የሕሊና እስረኞችን በማወደስ ኢትዮጵያዊ ግደታችንን እንድንወጣ በክብር ተጠርተዋል!!
አይርሱ ያስታውሱ!! የአገርዎ ጉዳይ ለግለስቦች ወይም ለፓርቲዎች የሚተው አይደለም፤ ተባብረን ዲሞክራስያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ትግል የበኩሉዎትን ድርሻ ለመወጣት ለራስዎ ቃል ይግቡ!!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
በቦስተን የአንድነት ድጋፍ ድርጅት





http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/13590#more-13590

No comments:

Post a Comment