Tuesday, March 24, 2015

(ዜና ፎቶ) የኦሮሞን ሕዝብ “ልክ እናስገባዋለን” ያሉት አባይ ጸሐዬ በኦህዴድ ስብሰባ ላይ እንቅልፋቸውን ተኙ

በቅርቡ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ማስፋፋት ተከትሎ የኦሮሞ ተማሪዎች ያነሱትን ተቃውሞና መንግስታቸው ሕዝቡን በመግደል ጭምር እርምጃ በመውሰድ ተቃውሞውን ለማርገብ የሞከሩት የሕወሓቱ ቁልፍ ሰው አባይ ጸሐዬ ካሁን በኋላ የኦሮሞ ሕዝብ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ጥያቄ ቢያነሳ “ልክ እናስገባዋለን; ያሰብነውንም እናደርጋለን” ማለታቸው በድምጽ ወጥቶ በዘ-ሐበሻ ድረገጽ እና በተለያዩ ድረገጾች ላይ መውጣቱ አይዘነጋም:: ሕወሓቱ አባይ ጸሀዬ ከኦህዴድ አመራሮች ጀርባ ሆነው የኦሮሚያ ክልልን የሚያሽከረክር ሲሆን ሰሞኑን ኦህዴድ 25ኛ ዓመቱን በሚያከብርበት በዓል ተገኝተው ነበር:: አባይ ጸሐዬ ሕዝቡን ልክ እናስገባዋለን ማለታቸው ሳያንስ የንቀታቸው ንቀት በስብሰባው ላይ የኦህዴድ አመራሮች ንግግር ሲያደርጉ እንቅልፋቸውን ለጥጠውታል:: ይህም በፎቶ ግራፍ ተደግፎ ለዘ-ሐበሻ ደርሷል:: ተካፈሏቸው

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39987


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39987


No comments:

Post a Comment