Friday, August 5, 2016

“በህወሀት ሽብር፣ ትጥቁን አይፈታም ጎንደር” – በሰሜን አሜሪካ ከሚኖሩ የአርማጭሆ ተወላጆች የተሰጠ የአቋም መግለጫ

በዚህ ወር፣ በታሪካዊ መዲናችን በጎንደር ከተማ፣ ሁለት ታላላቅ ክስተቶች ተፈጽመዋል። ሀምሌ 24 2008 ዓም ጎንደር ላይ የታየው ታሪካዊ ሰላማዊ ሰልፍ አለምን አስደንቋል። ይህ ግማሽ ሚሊዮን ህዝብ የተሳተፈበት፣ በላቀ ስነምግባርና ቆራጥነት የተመራው ሰልፍ፣ የአማራውን ህዝብ ታላቅነትና ደግነት አስመስክሯል። በዚህ ታሪካዊ ሰልፍ፣ ከመላው የአማራ ክልሎች የተሰባሰው ህዝብ፣ ለወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ብቻ ሳይሆን፣ በመላው ኢትዮጵያ በሚኖረው የአማራው ህዝብ ላይ ህወሀት የሚፈጽመውን የዘር ማጽዳት ዘመቻ በአንድ ድምጽ በማውገዝ፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ እውነተኛ የዜጎችን እኩልነት የሚያስከብር፣ የሀገራችን ሉዓላዊነት የሚረጋግጥ፣ የእምነት ነጻነትን የሚንከባከብ ሥርዓት እንዲመሰረት በአንድ ድምጽ ጥሪ አድርጓል። ይህን አዲስ ትግል መዕራፍ የከፈተልን፣ ጀግናው የጎንደር ህዝብ፣ ህወሀት የከፈተበትን ጥቃት ለመከላከል ሀምሌ 5 ቀን፣ የፈጸመው ተጋድሎና የከፈለው መስዋዕትነት ነው። የጎንደር ህዝብ ጀግኖች ልጆቹን ገብሮ ያቀጣጠለው ትግል እንዲሳካ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በህብረት ልንነሳ ይገባል።

እኛም በሰሜን አሜሪካ የምንገኛ የአርማጭሆ ተወላጆች፣ በጎንደር ጀግኖች መስዋዕትነት የተቀጣጠለው የነጻነት ፋና እውን እንዲሆን፣ ታሪካዊ ጥሪውን ተቀብለው፣ የነጻነት ልሳኑን አንግበን በአጋርነት የተነሳን መሆኑን በዚህ መግለጫ ይፋ እናደርጋለን። ሀምሌ 5 2008 . የጎንደር ከተማ የተከሰተው ህዝባዊ አመጽ ታሪካዊ ነው። ይህ እለት፣ የህወሀት የሽብር ግብረኃይል በጎንደር ከተማ ህዝብ ላይ የሽብር ጥቃት የከፈተበት ቀን ነው። ህወሀት የዚህ አይነት ጸረ አማራ አፈና እና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ላለፉት 30 ዓመታት በአማራው ማህበረሰብ ላይ ሲፈጽም ቆይቷል። በአማራው ክልል የተሾሙ የብአዴን አመራሮች ህወሀት እንደፈጣሪ ስለሚመለከቱት የወያኔ አፋኞች በክልሉ ያለ ምንም ጠያቂ ሰርገው እየገቡ ሰላማዊ ኗሪዎችን እያፈነ ሲወስድ ህዝቡን መከላከል አልሞከሩም። ይህም ወያኔ የሾማቸውን የክልሉም ባለስልጣኖች ምን ያህል እንደሚንቃቸው በይፋ ያሳያል።

ህወሀት የከፈተው የሽብር አፈና ያነጣጠረው ሰላማዊ የአማራ ማንነት ጥያቄ አንስተው የሚንቀሳቀሱ የወልቃይት ጠገዴ ሽማግሌዎችን አፍኖ ለመውሰድ የታቀደጸረ አማራ፣ ጸረ ጎንደር የሽብር ዘመቻ ሲሆን፣ ጀግናው የጎንደር ህዝብ ግን ወገኖቼን አሳልፌ አልሰጥም ብሎ ህዝባዊ አመጽ አነሳ። የጎንደር ህዝብ ግን ተቆርቋሪ መንግስት የሌለለው መሆኑን በመረዳት፣ ከህዝብ አብራክ የተፈጠሩ ህዝባዊ አርበኛች፣ ከቆላና ከደጋ አሰባስበው፣ የወያኔን የሽብር ግብረኃይል ሰብረው በመግባት በህዝብና በንብረት ላይ ከባድ ጥፋት ከማድረሱ በፊት ጥቃቱን አክሽፈውታል። ይህን የሽብር ጥቃት ለመከላከል በተካሄደው ህዝባዊ አመጽ ከወያኔ በኩል የዘመተው 21 የሽብር ግብረኃይል ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/63861

No comments:

Post a Comment