Wednesday, July 23, 2014

በሰሜን ሸዋ መርሃቤቴና አካባቢው የተነሳው ውጥረት ተባብሷል፤ ጫካ የገቡ መሪዎች የሕዝቡን አመጽ ተቀላቅለዋል

(በመርሃቤቴ አካባቢ በተነሳው ግጭት ተጎድተው ሆስፒታል ከገቡት መካከል)

ምኒልክ ሳልሳዊዝ እንደዘገበው፦

በሰሜን ሸዋ መርሃቢቴ እና አካባቢው ላይ የተነሳው የህዝብ እምቢተኝነት ከቀድሞው የበለጠ ተባብሶ ያለበት ሁኔታ መኖሩን ከአካባቢው የሚወጡ ዘገባዎች ጠቁመዋል። ሕዝቡ የመብራት ትራንስፎርመር መወሰዱን መሰረዙ ቢነገረውም ልታዘናጉን ነው። የከተሞቻችንን ንብረት የመጠበቅ ሃላፊነት አለብን የፌዴራል ፖሊሶች ከአካባቢያችን ይውጡልን የሚሉ ጥያቄዎችን በማንገብ መሳሪያውን ይዞ ወደ ከተማው በመውጣት አካባቢውን በውጥረት እንደሞላው ታውቋል።

የመርሃቢቴ ህዝብ አሁንም በያለበት እየተጠራራ የተደበቀውን የጦር መሳሪያ በማውጣትበመሰባሰብ መንገዶችን ተራሮችን ሸጦችን ተቆጣጥሮ ለውጊያ እየተዘጋጀ ነው። ጎረቤት ወረዳዎችም ይህንን የመሬን ህዝብ አመፅ በመደገፍ ወገናዊ ድጋፍና ትብብር ለማድረግ እየተዘጋጁና ግንኙነት እያደረጉ መሆኑን ከሚደርሱን መረጃዎች አረጋግጠናል። የየአካባቢው የወያኔ ታጣቂ ሚሊሻዎች፣ አስተዳደሮች፣ ካድሬዎች በሚያስደስት ሁኔታ ከህዝቡ ጎን ተሰልፈዋል።

እንደምኒልክ ዘገባ ከሆነ ወያኔ በከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ወድቋል ወደ ማይችለው አዘቅትም ገብቷል። ህወኃትን ከነ ግሳንግስ አገዛዙ ለማስወገድ ጊዜው አሁን ነው፣ በተለያየ መንገድ ሸፍተው በጫካ የነበሩ መሬዎች ሁሉ የህዝቡን አመፅ ተቀላቅለዋል ሲል ዘገባውን ቁጭቷል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/32848

No comments:

Post a Comment