Thursday, September 18, 2014

ነዋይ ደበበ በስዊድን ተቃውሞ እንደሚጠብቀው ተገለጸ

በስቶኮልም ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አና ተውልደ ኢትዮጵያውያን በጋራ “ልማታዊ አርቲሰት” ንዋይ ደበበ ኮንስርት ሊያቀርብ አይደለም ሊያስበው እንደማይገባ አሰታወቁ።

የኢትዮጵያውያን ስቃይ ላይ ጭቆና ላይ ከወያኔው ጋር በመሆን ጮቤ ዳንኪራ የሚረግጠው ንዋይ ደበበ ወደ ስቶክሆልም ሴፕቴምበር 20 ቀን 2014 ዓ.ም ለመዝፈን ስለሚመጣ ውርደቱን ማከናነብ ደግሞ ከሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ይጠበቃል ያሉት በስዊድን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከዓባይ በፊት ዘረኝነት ይገደብ! ከዓባይ በፊት በግፍ የታሰሩት ይፈቱ! ከዓባይ በፊት ሰብዓዊነት ይቅደም! የህዝብ መብት ይከበር! … ድምፃችን ይሰማ! መሪዎቻችን ይፈቱ! ንጹኀንን መግደልና ማሰር ይቁም! መንግሥት ከኃይማኖት ላይ እጁን ያንሳ እንድሁም የዞን ዘጠኝ እና የእስረኛ ጋዜጠኞች ስቃይ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሰቆቃ የጋዜጠኞች ስደት የፖለቲክ መሪዎች እና አጠቃላይ የዜጎች ግድያ ቁስሉ የኛ የዲያስፕራውያንም ስለሆነ ቦይኮቱን በመቅላቀል ንዋይ ደበበን በመጣበት አሳፍረን መመለስ አለብን።” ብለዋል።

“አዲስ ዓመት የአምባገነንነት ዘመን ውጣ የነፃነት ዘመን ግባ ብለን ካለው የተሻለ ነገር የምንፈጥርበት እንዲሆንልን በመመኘት ካለፉት ብዙ አዲስ አመቶች የሚለይበትን እና በሕይወታችን ትርጉም ያለው ለውጥ የምናመጣበት እንዲሆን የህሊና ጥንካሬያችንን ማጎልበት ይጠበቅብናል::” ያሉት ኢትዮጵያውያኑ የነዋይን ዝግጅት ቦይኮት ለማድረግ የተለያዩ ወረቀቶችን እየበተኑ እንደሆነ አስታውቀዋል።


ኢትዮጵያውያኑ በዲያስፖራ ከገዳዩና አሳሪው መንግስት ጎን ቆመው የሚወጉትን አርቲስቶች ቦይኮት ማድረግ ከጀመረ የቆየ ሲሆን በቅርቡ እንኳ ሃመልማል አባተ እንዲሁም በቅርቡ ሸዋፈራው ደሳለኝ ዝግጅቶቻቸው ቦይኮት ተደረገው ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸው አይዘነጋም።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/34659

No comments:

Post a Comment