Monday, December 9, 2013

አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ማእከላዊ እስር ቤት ዉስጥ በደረሰባቸው ድብደባ ህይወታቸዉ ማለፉ፤ ሆድ-እቃቸዉ ተከፍቶ ኩላሊታቸዉ መሰረቁ ታወቀ

አስክሬን ምንሊክ ሆስፒታል ሄደን እንድንወስድ ስልክ ተደወለልን፤ ለሞቱ ከደነገጥነዉ በላይ አስክሬኑን ስንመለከት ፍጹም ተረብሸናል፤ ከአዉሬ አፍ የተረፈ አስክሬን ነበር ሚመስለዉሰዉነቱ ተቦጫጭቋል!”  ጓደኞች
     አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም 
ዋሽንግተን ዲሲ ህዳር 30/2006 (ቢቢኤን) በአዲስ አበባ ዉስጥ በቦሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የነበሩት አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ቀደም ሲል በጥቅምት 4/2006 በአካባቢዉ ላይ ፈንድቶ ከነበረዉ ቦንብ ጋር በተያያዘ መልኩ ለምርመራ ማእከላዊ እስር ቤት መግባታቸዉ እና በማእከላዊ ቆይታቸዉ ምግብ እንዳይገባላቸዉ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መከልከሉም ለማወቅ ተችሏል።
እንደ አቶ ሙሐመድ ጓደኛ አገላለጽ ግለሰቡ ለተጠረጠሩበት ወንጅል የሚያበቃቸዉ ጉዳይ ባይኖርም፤ከገቡበት ማእከላዊ እስር ቤት በደረሰባቸዉ ከፍተኛ ድብደባ በህይወት መዉጣት አልቻሉም።
ለሐያ ዘጠኝ ቀናት ማእከላዊ እስር ቤት የታሰሩት አቶ ሙሐመድ ምን ያህል ድብደባ እንደደረሰባቸዉ ባይታወቅም ጭንቅላታቸዉ በጣም መጎዳቱን፣ሰዉታቸዉ እንደበለዘ፣ብዙ ሰንበሮች መታየታቸዉ፣ሆድ እቃቸዉ ተከፍቶ ኩላሊታቸዉ መሰረቁን ለአስራ ሁለትአመታት የሚያዉቋቸዉ ጓደኛቸዉ በሐዘን ይገልጻሉ።የዱር አዉሬ ቦጫጭቆ የገደለው ይመስላል በማለት ሁናቴዉን የሚገልጹት ጓደኛ ከመንግስት አካላትም ይሁን አስክሬኑ ከመጣበት የሚኒሊክ ሆስፒታል ስል አቶ ሙሐመድ አሟሟት የተሰጠ መረጃ አለመኖሩን፤ በደም በተጨማለቀ ከፈን የተከፈነ አስክሬን ብቻ  መመለሱን ገልጸዋል።
ቤተሰቡ ጉዳዩን ለሰብአዊመብት ተሟጋች ለሆኑ ድርጆቶች እንዳያመለክት ከፍተኛ ዛቻ ደርሶበታል፤በቅርበት የሚያዉቋቸዉ እንኳ በሞታቸዉ ከማዘን በስተቀር ስለ አሟሟታቸዉ ከፍርሃት የተነሳ መናገር አይችሉም በማለት የሚያስረዱት ጓደኛቸዉ ሁሉም ለሞቱ ከደነገጠዉ በላይ አስክሬኑን በማየት ተሸማቋል ይላሉ።
በጥሩ ስነምግባራቸዉ የሚታወቁት አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ሐማኖትን ተግባሪ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ከመሆን በስተቀር አገርን ወገንን ሊጎዳ በሚችል የአሸባሪ ተግባር የሚጠረጠሩ አይደልም በማለት በሐዘን የሚናገሩት ጓደኛ ሟቹ የሰባት ልጆች አባት እንደነበሩ ቤተሰቡም ለአደጋ መጋለጹንም አስረድተዋል።
በጥቅምት 4/2006 መንግስት በቂ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ ባልቻለበት፤ የመንግስት ደህነነቶች አለም አቀፋዊ ትኩረትን ለመሳብና ፖለቲካዊ ጥቅምን ለመጎናጸፍ በቦሌ ክፍሌ ከተማ አደርሰዉታል ተብሎ በሚነገረዉ የቦንብ ፍንዳታ፤ ማመካኛን ለማግኘት የሱማሌ ብሔር ተወላጅ የሆኑትን የአቶ ሙሐመድ ህይወትን መንግስት መስዋዕት አድርጓል  በማለት አስተያያት የሚሰጡ ወገኖች አሉ።በትላንትና እለትዉ የብሔር ብሔረሰቦችን ቀን በጅጅጋ ከተማ ድረስ ባሸበረቀ መልኩ አከበርኩ ለሚለዉ መንግስት፤ የአገሩን ዜጋ በብሔር ነጥሎ ማእከላዊ እስር ቤት አስገብቶ መግደሉ ለመንግስቱ አሳፋሪ ከመሆኑም ባሻገር የስርዓቱን መላሸቅ አመላካች ነዉ የሚሉም አሉ።
የአቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ታስሮ ለህልፈት መብቃት፤ የሆድ እቃቸዉ ተቀዶ የኩላሊታቸዉ መሰረቅ ከፍተኛ ምርመራ የሚያሻዉ ቢሆንም፤በሟች አስክሬን ላይ የተፈጸመው ወንጀል ስርዓቱ በህይወት ባሉ ብቻ ሳሆን በሙታንም ላይ ግፍ እንደሚፈጽም የሚያረጋግጥ ነዉ፤ በሐሰት አስሮ በመደብደብ፣በመግረፍ፣እስር ቤት ዉስጥ ከማሰቃየት አልፎ፤ ታሳሪዎች እስር ቤት ዉስጥ ሲሞቱ ሆድ እቃ ተከፍቶ የሰዉነት አካል መቸርቸር ተጀምሯልና!.. ኢትዮጵያ ወዴት እያመራች ነዉ? የሚለዉ ጥያቄ የብዙሐኑ ነዉ።

Posted By.Dawit Demelash

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/10666

No comments:

Post a Comment