Thursday, December 10, 2015

የኖርዌይ ኢምባሲ ዜጎቹ ወደ ጎንደርና ኦሮሚያ የተጠቀሱ ከተሞች እንዳይሄዱ መከረ


(ዘ-ሐበሻ) አዲስ አበባ የሚገኘው የኖርዌይ ኢምባሲ በጎንደር እና በኦሮሚያ ባለው አለመረጋጋት የተነሳ ዜጎቹ በሁለቱ ክልሎች በተመረጡ አካባቢዎች እንዳይሄዱ አስታወቀ::

ከኖርዌይ ኢምባሲ የአዲስ አበባ ድረገጽ ዘ-ሐበሻ ያገኘችው መረጃ እንደሚጠቁመው በጎንደር ባለፈው ሳምንት በ እስር ቤት ላይ የደረሰው ቃጠሎን ጉዳይ አንስቶ በአሁኑ ወቅት በታች አርማጭሆ; በም ዕራብ አርማጮና ጭልጋ አካባቢ ጦር የታጠቁ ኃይሎች እንቅስቃሴ እያደረጉ በመሆኑ ወደዚያ አካባቢ ለመሄድ ለደህነነት አስጊ በመሆኑ ዜጎቹ እንዳይሄዱና ከነዚህ አካባቢዎች እንዲርቁ መክሯል::

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተጀመረው ተቃውሞ አደባባይ ከወጣ እና ፖሊስ እና ተማሪዎችም ከተፋጠጡ በኋላ በተለይ በአምቦ እና በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተቃውሞው እጅጉን በማየሉ የኖርዌይ ዜጎች ወደዚያ አካባቢ እንዳሄዱ አስጠንቅቋል::


በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ የተረጋጋና ያልታሰበ ነገር ሊከሰት እንደሚችል ያስታወቀው ኢምባሲው ዜጎቹ ወደዚያው እንዳይሄዱ ከሄዱና አንድ ችግር ካጋጠማቸውም ቶሎ ለኢምባሲው ሪፖርት እንዲያደርጉ አስጠንቅቋል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48924


No comments:

Post a Comment