Saturday, December 19, 2015

‹‹ኃብታሙ አያሌው ላይ በጤንነቱ የተነሳ ለሚደርስ ችግር›› ሐኪሞቹ ‹‹ኃላፊነት አንወስድም›› አሉ

                        ኃብታሙ አያሌው


የቀድሞው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግኑኝነት ሐብታሙ አያሌው ከማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ቆይታ አንስቶ እያሰቃየው የሚገኘውን የኩላሊት ህመሙን ከብዙ ንትርክ በኋላ በዘውዲቱ ሆስፒታል እንዲታከም የተደረገ ቢሆንም የሐብታሙን ህክምና በመከታተል ላይ የሚገኙ ሐኪሞች ኩላሊቶቹ ከፍተኛ ክትትል የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ሐብታሙ በሆስፒታሉ አልጋ በመያዝ አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ እንደሚገባው ያዛሉ፡፡

እንደ ሆስፒታሉ የመረጃ ምንጮች ከሆነም ሐብታሙን ታህሳስ 5 ቀን 2008 በዘውዲቱ ሆስፒታል የመረመሩት ዶክተሮች የምርመራቸውን ውጤት ከተመለከቱ በኋላ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት ከሌሎች ሶስት የኩላሊት ህክምና ስፔሻሊስቶች ጋር በመመካከር ቢሆንም የህሊና እስረኛውን ለህክምና ምርመራ ያመጡት የወህኒ ቤቱ ፖሊሶች ሐብታሙን ‹‹አሳይታችሁ አምጡት››ተብለናል በማለት መልሰው ወስደውታል፡፡


በሆስፒታሎች አልጋ ይዘው እንዲታከሙ በዶክተሮች የሚታዘዙ እስረኞች በፖሊስ እንዲጠበቁ ተደርገው አልጋ የሚይዙ ቢሆንም ሐብታሙ ጤንነቱ አሳሳቢ መሆኑ እየተነገራቸው ህክምናውን አቋርጦ እንዲሄድ አድርገውታል፡፡


በዚህ ወቅት በፖሊሶቹ ውሳኔ የተበሳጩ ዶክተሮች ‹‹በጤንነቱ የተነሳ አንዳች ችግር ቢፈጠርበት እኛ ኃላፊነት አንወስድም፡፡እናንተም የባለሞያ ምክራችንን ትታችሁ ህመምተኛውን መውሰዳችሁን ፈርሙልን››በማለት ጥያቄ ቢያቀርቡላቸው ለመፈረም ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በመግለጽ ወስደውታል፡፡


ሐብታሙ፣አብርሃ፣የሺዋስና ዳንኤል ዛሬ በቀረቡበት ፍርድ ቤት የተሰየሙት የመሐል ዳኛ ጉዳያቸውን የመመልከት ሞያዊም ሆነ ስነ ምግባራዊ ብቃት እንደሌላቸው በመጥቀስ እንዲነሱላቸው መጠየቃቸው ተነግሯል፡፡


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49259

No comments:

Post a Comment