Thursday, October 24, 2013

ወያኔ መጥቷልና ወገን ተዘጋጅ !!

oct.24.2013
                    ወያኔን መደገፍ ማለት በወገኖችዎ ላይ የሚደርሰውን ይህን ግፍ መደገፍ መሆኑን ይገንዘቡ!!
Ethiopia 1997
የወያኔን የዘረፋ ጉዞ ተባብረን እንግታ!!
የወያኔ ቁንጮ የነበረው መለስ ዜናዊ ከሚስቱ ጋር በመሆን ከዘረፉት በላይ ለመዝረፍ በነደፉት የአባይ ግድብ እቅድ ሳቢያ በውጭ ሃገር ካለው ወገናችን ጉልበት በዝባዥ የሆነውን የፈረንጅ ሃገር ስራ ተጋትሮ ያገኛትን ለመመንተፍ የመለስ ውሾች የሆኑት ካድሬ ተብዬዎች ላይ ታች ሲንጠራወዙ ሁለት ዓመት ሆናቸው። ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያንም እነዚህን ተላላኪ አሽከሮች በየደረሱበት እያሳደዱ ስብሰባ ብለው የጠሩትን ሲያከሽፉ፣ እግሬ አውጭኝ ሲያስሸመጥጡ፣ የእነርሱን ባንዲራ እያነሱ እውነተኛ የኢትዮጵያ ባንዲራ ሲሰቅሉ፣ ወያኔዎቹ የተከራዩትን አራሽ ተቆጣጥረው የራሳቸውን ስብሰባ ሲያካሄዱ፣ ወዘተ ወዘተ ብዙ ገድል አይተናል። ካድሬዎቹ ውሾች ግን ወትሮም የሰውነት ክብር የላቸውምና በደረሰባቸው ተደጋጋሚ ውርደት ተሸማቀው አርፈው አልተቀመጡም።
እየተሽሎኮለኩና እያደቡ ከዳያስፖራው የውጭ ምንዛሪ ለመንጠቅ ዛሬም የሞት ሞታቸውን ያገኙትን ሁሉ ከመቧጠጥ አላረፉም። በዚህም መሰረት በመጪው ኖቬምበር 02/2013 በጀርመን ሙኒክ በአባይ ቦንድ ስም ዩሮ ለመሰብሰብ እየተጠራሩ መሆኑ ተደርሶበታል። በመሆኑም በሃገሩ ጉዳይ የሚንገበገብ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከቅርብም ከሩቅም ወደ ሙኒክ እንዲከትና የወያኔን ዘረፋ በተለመደው መልኩ እንዲያከሽፍ የተቃውሞ አስተባባሪ ግብረ-ኃይሉ ወገናዊ ጥሪውን ያስተላልፋል።
በእለቱ በሚደረገው ተቃውሞ የተለመደው የወያኔን የዘረፋ ተግባር ከመግታት በተጨማሪ ትናንት የወያኔ መንግስት በደል እንደፈጸመባቸው አመልክተው የስደት ተገን ያገኙና ዛሬ ከወያኔ ጎን ተሰልፈው ለወገኖቻችን ስቃይና ሞት ተባባሪ የሆኑ ለጥቅምና ለሆዳቸው ያደሩ ባንዳዎችን ፎቶ በማንሳትና ቪዲዮ በመቅረጽ ስደት ላመለከቱበት ሃገር መንግስት የማጋለጥ ስራ በሰፊው ይሰራል። ሁላችንም በ02/11/2013 ጀርመን ሙኒክ ተገናኝተን የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ።
    Posted By.Dawit Demelash

No comments:

Post a Comment