Thursday, February 27, 2014

አብርሃ ደስታ… ታስሮ ተፈታ!!


EMF – በትግራይ ውስጥ የሚደረጉ ግፍ እና በደሎችን ያለመሰለስ በማጋለጡ ይታወቃል:: ለሰብአዊ መብቶች መከበር በመቆሙ ከህወሃት ሰዎች ተደጋጋሚ ማስፈራሪያ እና ዛቻዎች ሲደርሱበት ነበር:: ባለፈው ሳምንት ቃሊቲን ለመጎብኘት የፖለቲካ እስረኞችንም ለመጠየቅ ወደ አዲስ አበባ ሄዶ በነበረበት ወቅት “እንዴት የፖለቲካ እስረኛ ለመጠየቅ ከትግራይ ድረስ መጣህ?” በሚልም ለእስር ዳርገውታል:: ሁኔታውን እራሱ አብርሃ ደስታ እንዲህ በማለት ገልጾታል::
አዲስ አበባ ነበርኩ። ሰኞ ጧት ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ርእዮት አለሙ ለመጠየቅ ቃሊቲ ማረምያቤት ሄድኩኝ። ጥበቃዎቹ ወደ ማረምያቤቱ አስተዳዳሪ ወሰዱኝ። አስተዳዳሪው ምርመራ ይሁን ዛቻ በማይታወቅ መልኩ ካስፈራራኝና ከሰደበኝ በኋላ ከማረምያ ቤቱ ተባረርኩ። አስተዳዳሪው “አንተ ከትግራይ አክራሪ አማራዎችን ለመጠየቅ ስትመጣ አታፍርም?!” አለኝ። ከፈለኩ ብሄር ብመጣም የፈለኩትን ሰው የመጠየቅ መብት አለኝ። የታሰረ ሰው መጠየቅ አያሳፍርም” መለስኩለት። ካሁን በኋላ “ወደ ቃሊቲ የምትገባው ታስረህ ካልሆነ በቀር እነ አንዱኣለምን ለማየት ድርስ አትላትም!” ብሎ ፖሊሶችን እንዲያስወጡኝ አዘዘ።
ወደ ቂሊንጦ ማረምያ ቤት ተጓዝኩ፤ ኡስታዝ አቡበክር አህመድን ለመጠየቅ። “አሸባሪ ለመጠየቅ መጣ” ተብዬ ለሦስት ሰዓታት ታሰርኩ። የቂሊንጦ ማረምያቤት ዋና አስተዳዳሪ እምባዬ ህቡዕ “አሸባሪዎችን ለማበረታታት መጣህ፣ ማረምያቤቱን ለመበጥበጥ ነው የመጣኸው። እንዳውም አሁን በማረምያቤቱ ረብሻ ተነስቷል። ስለዚህ ይታሰር” ብሎ በማዘዙ ወህኒቤት ዉስጥ ቆየሁ።
 ዝርዝር ጉዳዩን ለመፃፍ እሞክራለሁ። አንዱኣለም አራጌና ርእዮት አለሙን አላየኋቸውም። አቡበክር አህመድ (ና ሌሎች ጉደኞቹ) ግን አግኝቻቸዋለሁኝ። እነ አቡበክር አህመድን በማግኘቴ ደስ ብሎኛል።



 http://ethioforum.org/%E1%8A%A0%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83-%E1%8B%B0%E1%88%B5%E1%89%B3-%E1%89%B3%E1%88%B5%E1%88%AE-%E1%89%B0%E1%8D%88%E1%89%B3/

No comments:

Post a Comment