Saturday, December 20, 2014

የገዢው መንግስት ወታድሮች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች ላይ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ እንዲቆም የሃይማኖት አባቶች ጠየቁ፡፡


ታኀሳስ ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-በትላንትናው እለት በባህርዳር ከተማ በተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ የገዢው መንግስት ወታደሮች በህዝቡ ላይ እያደረሱ ያለውን ተመጣጣኝ ያልሆነ  እርምጃ የባህርዳር ከተማ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች በአስቸኳይ እንዲያቆም በሰጡት መግለጫ ጠይቀዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ የሃይማኖት አባቶችን ከሁለት ቀን በፊት በመሰብሰብ በመስቀል አደባባይ ላይ ሊሰሩት ያሰቡትን ጉዳይ እንዳወያዩዋቸው የገለጹት የሃይማኖት አባቶች ይህንን ጉዳይም ለሚመለከታቸው የእምነቱ ተከታዮች ለማሳወቅ ቢነጋገሩም የከተማ አስተዳደሩ ኃላፊዎች ግን  በሁለተኛ ቀኑ የአጥር  ማፍረስ ስራ መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡

ይህን ጉዳይ በመያዝ ወደ ምዕመኑ ተወካዮች በቀረቡ ጊዜም ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት እንዳላገኘ ሊቀ አዕላፋት ራዳዊት እንግዳው የገለጹ ሲሆን በተወካዮች የቀረቡት ጥያቄዎችን ሲናገሩ   ́በሚወሰደው መሬት ምትክ የሚሆን ቦታ እንዴት እናገኛለን ? ʼ  ́ለባእለ ጥምቀቱ መሰናክል አይሆንብንም ወይ  ? ʼ የሚል ተቀባይነት ያለው ጥያቄ  በማቅረብ ህዝቡ እየበዛ የባእሉ አከባበር እየሰፋ በመሄዱ የምትክ መሬቱ ጉዳይ መነሳቱን የሃይማኖቱ አባት ተናግረዋል፡፡ ሊቀ አዕላፋት በመግለጫቸው አክለው እንደተናገሩት ሊቀ ጳጳሱ ሳይኖሩ ይህን ለማሰባሰብ ይቻልወታል ወይ? በማለት ሊቀ ጳጳሱ ሳይኖሩ መሰባሰብና ውሳኔ መስጠቱ አግባብ እንዳልሆነ በእርሳቸው ላይ ጥያቄዎች  መቅረባቸውን አልሸሸጉም፡፡

ምእመኑ ይህን ጉዳይ ከሰማ በኋላ የመስቀል አደባባይ ትክ ሳይሰጥና የጥምቀት በአል ሊከበር አንድ ወር ብቻ በቀረበት ጊዜ አጥር ማፍረስና  ቁፋሮ ለመጀመር የከተማ አስተዳደሩ እንቅስቃሴ መጀመሩ የበዓሉን ሂደት ሆን ብሎ ለማበላሸት ነው በሚል ዓርብ ከጠዋቱ በአንድ ሰዓት በፈለገ ጊዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ቅጥር ግቢ በመገናኘት ተቃውሟቸውን ለማሰማት እንደ ተሰባሰቡ የሃይማት አባቱ ተናግረዋል፡፡

የሃይማኖት አባቶች መንግስት እየወሰደ ባለው እርምጃ ችኩልነቱን በመተው እንዲያስብበት ህዝቡም ተጮኸ ሲባል ለወገኑ ፈጥኖ መድረስ ለነገ የሚባል ነገር  አይደለም በማለት ተናግረዋል፡፡

በመግለጫው አሰጣጥ ላይ ከተገኙት በርካታ የሃይማኖት አባቶች መካከል  የፈለገ ጊዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳምን የወከሉት አባት ሲናገሩ  ጥያቄው አግባብ ነው ወይስ አይደለም? የሚለው ሳይጣራ የቅዱሳንን ምስል በመያዝና መንፈሳዊ መዝሙሮችን በማሰማት ተቃውሞውን በሚገልጽ ምዕመን ላይ ድብደባ መካሄድ እና በጥይት እርምጃ መውሰድ አግባብ እንዳልሆነ ገልጸው፤መንግስት ጉዳዩን በተረጋጋ መንፈስ በማየት ስራውን ሊሰራ የሚችልበትን መንገድ እንዲያመቻች መንግስትን ጠይቀዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በትላንትናው እለት  በሰላማዊ ሰልፉ በተሳተፉ ምዕመኖች ላይ እርምጃ ለመውሰድ የሚያደርገው እንቅስቃሴ የቀጠለ ሲሆን የፌደራል ፖሊሶች በመንገድ ዳር ሁለት ወይም ከዛ በላይ ተሰባስበው የሚቆሙ ማንኛውንም የከተማዋ  ነዋሪዎች ያለ ርህራሄ በዱላ በመምታት እንደሚበትኑ የአይን እማኞች ለኢሳት ገልጸዋል፡፡

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባሎች እና የክልሉ ካቢኔ ባደረጉት ምክክር ማምሻውን እንደተነገረው በተገደሉ የተቃውሞ ሰዎች እና መብታችውን በጠየቁ ንፁሃን ላይ የተወሰደው እርማጃ ቀጣዩ ምርጫ አደጋ ነው ሲሉ ርዕሰ መሰተዳድሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለካቢኔው ተናግረዋል፡፡ ምሺቱን በሰላም አርጊው ማርያም ቤተ ክርስቲያ ፆለተ ፍትሃት ተደርጎላቸው ቃብራቸው በተፈፀመው አራት ወጣቶች እና አንድ የቆሎ ተማሪ ላይ እንኳን ተገኝቶ ሃዘኑን የገለፀ አንድም የመንግስት አካል ባለመኖሩ ‹‹ ምሺቱ በቅዱስ ጊዩርጊስ ቅዱስ ሚካኤል እና በቤተክርስቲያን አድባራት እና ገዳማት ምዕመናኑ ተቃውሞውን ሲያሰማ ያመሸ ሲሆን ‹‹ ገዱ አይመራንም›› መንግስት የለንም›› ስርዓቱን ለማፍረስ ምርጫው ጦርነት ነው፡፡ ፖሊሲ እና መከላከያ የኛ አይደሉም የፖለቲካ ፓርቲ ናቸው፡፡ ሲሉ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡  በቀብሩ ላይ የአንዱ ስርዓቱን የጠበቀ ሲሆን የአራት ወጣቶች ግን በቀጥታ እንዲፈፀም የምንዕራብ ዕዝ ጦር  እና የፊድራል ፖሊስ ውሳኔ መሰረት ፍታሀተ ጸሎት ሳይደረግ አፈር ለብሰዋል፡፡

በባር ዳር እና በአማራ ህዝብ ላይ ከባድ ጠባሳ እንደሚሆን የመከረው መድረኩ ልማቱን ካልፈከለጋችሁ ሊቀሩ ይችላል እየተባለ የፊዝ እና ስላቅ መግለጫ መሰጠቱ ህዝቡ እንዳልተቀበለው የኮሚኒኬሺን ጉዳይ ለመድረኩ ገልፆል፡፡ የአመፁ እና መብታቸውን የጠየቁ ህዝቦችን አሸባሪ ሲል የፈረጀው የመንግሰት አካል ፤ሁከቱን የፈጠሩት ማህበረ ቅዱሳን እና የሰንበት ትምህርት ቤት አሰተባባሪዎች ናቸው ሲል ሃሳብ ቢያቀርብም፣  የመንግስት የደህንነት ሰዎች በበኩላቸው በተነሳው ተቃውሞ ማህበረ ቅዱሳን እጃቸው የለበትም ሃሳቦ በመሉ ህዝበ ክርስቲያን የወከለ ነው ብለዋል፡፡

ምሺቱን ቤት ለቤት ወጣቶች እየታሰሱ ተይዘዋል።  ምሽተና ሌሊቱን በየመንደሩ ጩህት እና ልመና ይሰማ ነበር።  በርካቶች በግዳጅ ቤቶችን እየበረገዱ በሚገቡ የፊድራል ፖሊሶች በሰደፍ እና በዱላ  ተደብድበዋል። 36 የሚሆኑ ወጣቶች በሁለተኛ እና በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ሌሊቱን ታስረዋል፡፡

ባበንዴ,ራው እና በኢትዩጵያ አምላክ ሲለምኑ ያደሩት እናቶች  እየተደበደቡ ልጆቻቸውን ከጉያቸው ሲነጠቁ ማመሸታቸውን ያይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ ልጆቻቸውን ከገዳይ የፖሊስ ቅጥረኛ ሃይሎች ለመታደግ ወላጆች በአልጋ ስር እና በጣራ ሲደብቁ ያደሩት እናቶች የልጆቻውን መደብደብ እና በደል በእሪታ ሲያሰተጋቡ ሌሊቱን ማሳለፋቸውን  ወኪላችን ገልጻለች፡፡

ደርግ ተመልሶ መጠዋል ያሉት ያይን እማኞች መንግሰት  እና እኛ በቅቶናል ተለያይተናል ብለዋል፡፡ የእምነት አባቶች ከምንግሰት ጋር በመወገን በሰጡት መግለጫ ምሺቱን ህዝቡ ቤታቸውን ከቦ በማደሩ እና እርማጃ እንወስዳላን ማለቱን ተከትሎ በመግለጫው የተሳተፉ የሃይማኖት አባቶች በፖሊስ እና በደህንንት እየተጠበቁ ነው፡፡

በሌላ በኩል በርካታ አስተያየቶች በኢሳት ፌስ ቡክ ላይ ቀርበዋል። የተወሰኑት እንደሚከተለው ቀርበዋል።ወያኔዎች የአላህን ፍርድ ታዩታላችው እንደዚህ እንደጠገባችሁ አትኖሩም!! መቸ ትፈርዳለህ አምላክ ለልጆችህ!!ለሞቱት አባቶቻችንና ወድሞቻችን የሰማታትን በረከት ይስጥልን።ግን መገፋታችን እስከ መቼ……………………?

እኒን የሚገርመኝ በባዶ እጁ የወጣ ሕዝብ ላይ ይሄን ሁሉ ጥይት መተኮስ ምን አመጣዉ ??

እረ ጎበዝ እኔ ሙሥሊም ነኝ ግን የማንኛውም እምነት መነካት የለበትም ግን አንድ ጥያቄ ለኢትዬጲያ ህዝብ መጀመሪያ ሙሥሊሙን ሲያጠቃ ዝም አልን አሁን ደግሞ እምነት የለሹ ኢህአዴግ አፈሙዙን ወደ ኦርቶዶክሥ እሺ ከዚህ በላይ ምንድን ነው ምንጠብቀው አሁን ሙሥሊም ክርሥቲያን ሳትል ሁልህም በአንድ ካልቆምክ ውርደቱ የሀገር ነው ልብ ያለው ልብ ይበል

በጣም ያሳዝናል:ወያኔ ህግ አለ ዲሞክራሲ ከደርግ በተሻለ አምጥተናል እያሉ ወሪያቸው በጎተራ የሚላካ አረመኔዎች የሰው ደም እንደውሃ የሚጠጡ ጅቦች : የደሃዎች ነብስ እግዚአብሔር ይማር ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ኢትዮጲያዬ! ሙስሊም ክርስቲያኑ ተፋቅሮ ተዋዶ፣ ተሳስቦ ሚኖርባት፣ የጥቁር ህዝብ መመኪያ፣ ያኩሪ ድንቅ ባህል ባለቤት፣ ጥንት ጠላት እሳት ለብሶ፣ እሳት ጎርሶ ቢመጣ መለኮታዊ እሳትን (ታቦተ ጊዮርጊስን) ተሸክማ ወራሪ ፋሺስት ጣሊያንን ያሳፈረች የእነ ጴጥሮስ ሀገር ዛሬ ምነው ሀሞቷ ፈሰሰ? የአባት የእናቶቿ የጀግንነት መንፈስ ከወዴት ተለያት? ስንቱ ጀግና እንዳልተፈጠረባት የወላድ መካን ይመስል ዛሬ በቀኝ አገዛዝ ስር ወድቃ እንዲህ ነጻነቷን ትጣ፣ አሁን ወዴት ይኬዳል? ወደማንስ አቤት ይባላል? አልበዛም እንዴ ወገን? ከእግዚአብሔር ህዝብ ጋር መገዳደር ለማንስ ጠቀመ? ለፈርኦን ወይስ ለጎልያድ? ዛሬ የመሸ ቢመስል ሊነጋ ሲል እንዲጨልም ማን በነገረው።

አፎይ ኣረ ውስጤ ተቃጠለ መተማንም ሸጠ የጤና ሳይንስ ኮሌጆችን ክፍያ አቁኣርጦ የተማሪዎችን ስነልቦና ሲጎዳ ቆየ የሰውን ጤና ደግሞ ከጣውላ ጋር መደበ ስለዚ ኢሀዲግ ከስሩ ካልተነቀለ አማራ ክልል ሰላም የለንም!!!!ለማነኛውም ሁሉን የሚገዛ ጌታ እግዚኣብሄር ይጠብቀን።አሜን!!

ይህ መንግስት ህዝብን ሊበላ ሊገድል ሀገርን ሊያወድም የቆመ አረመኔ ወንበዴ ስብስብ ነው ይህን ሰላማዊ ህዝብ ምን አድርግ ብለው ነው ይህን ሁሉ ሲቃይ ሚያወርዱበት መብቱን ፍላጎቱን የመግለፅ ነፃነቱን ለምን ይገፈዋል  እውን እውነት ለሃገሪቱ ያሚያስብ መሪ ቢኖርር ይህ ይደርስ ነበር

ይህ መንግስት ለዜጎች እንደማይጨነቅ አሳይቶናል የእምነታችን ነፃነት ገፎናል ስለዚህ የአንዱ መብት ሲጣስ ሌላው ዝም ማለት የለበትም ሁላችንም አንድ ወገኖች ነንና ስለዚህ ለመብትህ ማስከበር ሁልህም ተነስ። እንደዚህ ተባለ ብቻ ምንም ዋጋ የለዉም

ማሰር፣ መደብደብ፣ማሳደድ፣ ማሸማቀቅ፣መግደል፣ እና የሕዝብ ንብረትና ሀብት መንጠቅ አንድን መንግስት ስልጣን ላይ የሚያቆይ ብሆን ኖሮ ደርግ አይወድቅ ነበር። ኢህአዴግ ኢትዬጵያን በቀጣይ ዓመታትም እኔ ብቻ አስተዳድራለሁ ብሎ ከማሰብ ቢቆጠብ ጥሩ ነው።

መዉረጃዉ የደረሠ ተሳፋሪ ያንቀዠቅዠዋልም አይደል የሚባለዉ

http://ethsat.com/amharic/%E1%8B%A8%E1%8C%88%E1%8B%A2%E1%8B%8D-%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B5-%E1%8B%88%E1%89%B3%E1%8B%B5%E1%88%AE%E1%89%BD-%E1%89%A0%E1%8A%A6%E1%88%AD%E1%89%B6%E1%8B%B6%E1%8A%AD%E1%88%B5/

No comments:

Post a Comment