Saturday, December 6, 2014

(አሁን የደረሰን ዜና) ፖሊስ ለሰልፍ የሚወጣውን መደብደብ ጀመረ; ሰልፉን አስቁሞ መንገድ እየዘጋ ነው (የኦዲዬ ድምፅ ይዘናል )




(ዘ-ሐበሻ) በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ እንደወደቀ የሚነገርለት የሕወሓት/ኢሕአዴግ አስተዳደር ፖሊሶችን በማስመራት ከሰማያዊ ፓርቲ ተነስተው ወደ መስቀል አደባባይ የሚያመሩትን ሰልፈኞች በመደብደብና መንገድ በመዝጋት ላይ እንደሚገኝ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታወቁ:: በሌላ በኩል በደረሰን መረጃ ሰላማዊ ሰልፉ ከሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ጀምሮ መፈክር እያሰማ ወደ አብዮት አደባባይ እየሄደ ቢገኝም የጀመረመው ሰልፍ እንደራሴ ሆቴል ላይ ፖሊስ አስቆሞታል::

ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በደህንነቶች እና በፖሊስ መከበቡን ያስታወቁት ዘጋቢዎቻችን ፖሊስ የሃይል እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ገልጸዋል::

በሌላ በኩል ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ አሁን ባደረሰን መረጃ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ አለሳ መንገሻ የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ኮንግረንስ ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ፣ ወሮታው ዋሴ፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ እየሩስ ተስፋው፣ ጋዜጠኛ በላይ ማናየ፣ ወይንሸት ሞላ፣ ሳሙኤል አበበ፣ እያስፔድ ተስፋዬ፣ሜሮን አለማየሁ፣ ንግስት ወንዲፍራው፣ ወይንሸት ንጉሴ፣ ምኞት መኮንን፣ አቤል ኤፍሬም፣ ኤፍሬም ደግፌ፣ ኃይለማሪያም፣ ሜሮን፣ ኢብራሂም አብዱልሰላም፣ እና ሌሎችም የትብብሩ አመራሮችና አባላት ከፍተኛ ቁጥር ባለው ፌደራል ፖሊስ ተይዘዋል፡፡ ነዋሪውን ወደየቤቱ እንዲገባ በማድረግና መኪና መንገድ በመዝጋትሜዳ ላይ እየደበደቧቸው ነው፡፡ የትብብሩን አመራሮች፣ አባላትና የሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊ ለመደብደብ ወደየ ቤታቸው እንዲገቡ ሲታዘዙ አልገባም ያሉ፣ መንገድ ላይ የተገኙና ሌሎችም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አልፎ ሂያጆች በፖሊስ እየተደበደቡ ነው፡፡

40 ያህል አመራሮችን ፌደራል ፖሊስ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን ከሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ጀምረው ወደ አብዮት አደባባይ በማቅናት ላይ ከነበሩት መካከል 40 ያህሉ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸዋል፡፡ አቤል ኤፍሬምን ጨምሮ በርካታ የሰልፉ አስተባባሪዎች እራሳቸውን እስኪስቱ ተደብድበዋል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ
አሁንም ዘ-ሐበሻ አዳዲስ መረጃዎችን እንዳገኘች ትመለሳለች




No comments:

Post a Comment