Saturday, June 6, 2015

በደራሸ ወረዳ 15 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታሰሩ (ዝርዝራቸውን ይዘናል)

በደቡብ ክልል ደራሸ ወረዳ አርጎባጠና ቀበሌ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ የሆኑት አቶ ከተማ ካሳን ጨምሮ በርካታ ወጣቶች መታሰራቸውን የወረዳው አስተባባሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን እያደነ እያሰረ መሆኑን የገለጹት አስተባባሪዎቹ ከ27 በላይ ወጣቶች የደረሱበት እንዳልታወቀ ገልጸዋል፡፡ ዛሬ ግንቦት 29/2007 ዓ.ም በደራሸ ወረዳ አርጎባጠና ቀበሌ በፖሊስ ተይዘው በደራሸ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ከሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. አቶ ከተማ ካሳ (ዕጩ ተወዳዳሪ)
2. ወጣት ሙሉጌታ ሙንጣዮ
3. ወጣት ይበልጣል አቡሽ
4. ወጣት ኢሳሞ ሽብሩ
5. ወጣት ጨንቄ ሻንቆ
6. ተማሪ ገብሬ ኩሴ
7. ተማሪ ደረቡ ካሳ
8. ወጣት ደግነት ደነቀ
9. ወጣት የኋላሸት
10. ወጣት ሙሉጌታ ጢኖ
11. ወጣት አርቢኖ ታየ
12. ወጣት ታሪካ ጭንጌ
13. ወጣት ጥጋቢ ጭልጌ
14. አቶ ጭንቃዮ ካሳሁን
15. አቶ ሙሉቃ በርበሶ ናቸው
በደራሸ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ከሚገኙት በተጨማሪ በሌሎች የወረዳው አካባቢዎችም በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ እንደሚገኙ አስተባባሪዎቹ ገልጸዋል፡፡


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44092

No comments:

Post a Comment