Sunday, September 6, 2015

የዋሽንግተን ዲሲ ግብረሃይል በ13 አርቲስቶች ላይ ማዕቀብ እንዲጣል አሳሰበ


ይህቺን ታሪካዊ አገር ከነኩሩ ህዝቧ ከምድረ ገጽ ሊያጠፋ የተነሳን ጠላት መጥላት ብቻ ሳይሆን ለማጥፋት መነሳትም የሚገባ የትውልዳችን አደራ ነው።ይህን የወያኔ መርዘኛ ስርዓት ለማስወገድና በምትኩም ህዝባዊና ኢትዮጵያዊ መንግስት ለመመስረት ዛሬ ባራቱም ማዕዘናት በትጥቅም፣ በህዝባዊ እምቢተኝነትም፣ በሰላሙም፣ በጸሎትም ዜጋው ሁሉ የአቅሙን ጸረ ወያኔ ትግል እያካሄደ ይገኛል። ታዲያ ጠላቱን በጠላትነት የፈረጀ ህብረተሰብ በጠላቱ ላይ ማዕቀብ መጣሉ ተገቢና ቀላሉ የትግል ስልቱ ነው።

ወያኔ ዛሬ ኢትዮጵያ ላይ እንደ አልቅት ተጣብቆ ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮ እየመጠጣት ይገኛል፤ ይህንንም ለመዘርዘር መነሳት ለቀባሪ ማርዳት ይሆናል።የህዝብን ትግል ለማኮላሸት መለሳለስንም መስበክ ለሞተው ስርዓት እስትንፋስን መለገስ ይሆናል።

በወያኔ እና በአጋሮቹ ላይ ማእቀብ በማድረግ ሳንቲም እንዳያገኙ እንዲሁም የሸቀጣቸውም ማራገፊያ ላለመሆን ይረዳል። የማእቀብ ጥሪ ያልታወጀበት ጊዜ የለም፤ ነገር ግን አብዛኛው አሁንም የበጎ ፈቃድ ሸቀጥ መራገፊያ በመሆን የወያኔን ሸቀጥ ተሰልፎ ሲሸምት መታየትን ቀጥሏል ይህንንም የመሰለ አሳፋሪ ነገር የለም። በሌላም በኩል በሰሜን አሜሪካ የህዝብ ተቋማቶችን ወያኔ እጁን አርዝሞ ለመቆጣጠር ያደረገውን ጥረት እድሜ ለአገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ተቋቁመውት ዛሬ የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌደሬሽን የሕዝብ ተቋም ሆኖ ከቀጠለ ዘንድሮ ፴፪ኛ አመቱን በታላቅ ብሄራዊ ስሜት አክብሮታል። በአንጻሩም በወያኔ በሚዘወረው እና ከወገኖቻችን በግፍ በተዘረፈ የደም ገንዘብ የሚንቀሳቀሰው AESAONE በቱጃሩ ሊስት ላይ ስማቸው የሰፈሩ ጥቂት የኪነጥበብ ባለሙያዎችን ገዝተው አሁንም በያመቱ በባዶ ሜዳ ሲያለፏቸው ይታያል።

እነዚህን ከጠላት እያወቁ ያደሩትን እንዲያውም ህዝብን በመናቅ በዚሁ አጥፊና አሳፋሪ ስራቸውን በመቀጠላቸው በሚሳተፉበት ማንኛውም ዝግጅት ላይ ባለመሳተፍ እና የደረሱበት ባለመድረስ ማእቀብ ይጣልባቸው በማለት ጥሪ እናቀርባለን፤ እንዲሁም ማንኛውም የልማትም ሆነ የሰብአዊ እርዳታ አዘጋጆች ከእነዚህ ማእቀብ ከተደረገባቸው ግለሰቦች ጋር ምንም አይነት ዝግጅት ባለማዘጋጀት የህዝብን ድምጽ ያከብሩ ዘንድ እንጠይቃለን። እነዚህን አፍቃሪ ወያኔዎች አውቀው በድፍረት የሚያደርጉትን እኛም አውቀን በእምነት ይታቀቡ እንላለን፤ በድግሳቸውም ሆነ በሃዘናቸው ጸረ ወያኔ የሆነው ሃይል በሙሉ ያቅብባቸው እንላለን። በተጨማሪ በቀጣይንትም በእንዲህ አይነት አሳፋሪ ሁኔታ የሚሳተፉ ካሉ እያጣራን ማእቀቡ በእነሱም ላይ የሚቀጥል መሆኑን በቅድሚያ እናሳውቃለን። ለአሁኑ በተጨባጭ ማስረጃ ያለንን ስማቸውን እንደሚከተለው እንዘረዝራለን።

፩ ሀይሉ ፈረጃ
፪ ራስ ብሩክ ባርኪ
፫ ታደለ ገመቹ
፬ ኩሪባቸው ወ/ማሪያም
፭ ንዋይ ደበበ
፮ ኤደን ገብረስላሴ
፯ ደረጀ ደገፋው
፰ አብርሃም ገ/መድህን
፱ ሀና ሸንቁጤ
፲ የኔሰው ተፈራ
፲፩ ቴዎድሮስ ብርሃኑ
፲፪ ተክሉ ደምሴ
፲፫ በሱፍቃድ


በመጨረሻም ማእቀባችን በሁሉም ዘርፍ የወያኔን ኤኮኖሚ በሚያንኮታኩት መልኩ እንዲሁም ለወያኔ የሚያደሉ ፕሮፓጋንዲስቶችንም ጭምር ወደፊት ደረጃ በደረጃ እናሳውቃለን።
የጸረ ወያኔው ትግል ተፋፍሞ ይቀጥላል!!! ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!


የዋሽንግተን ዲሲ የጋራ ግብረሃይል dcjointtaskforce@gmail.com

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46449

No comments:

Post a Comment