Tuesday, September 8, 2015

የሕወሓት መንግስት የታጠቁ ኃይሎቹን እና ካድሬዎቹን በማሰማራት በአርማጭሆ ሕዝብ ላይ ሰቆቃ እየፈጸመበት እንደሚገኝ ተዘገበ

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ እንደዘገበው የህወሓት አገዛዝ የታጠቁ ኃይሎቹን፣ ደህንነቶቹንና ካድሬዎቹን በማሰማራት በላይ አርማጭሆ ህዝብ ላይ እንደዘመተበትና ሰቆቃ እየፈፀመበት እንደሚገኝ ታወቀ፡፡
የህወሓት አገዛዝ በታጠቁ ቡድኖቹ፣ በደህንነቶቹና በካድሬዎቹ ቁም ስቅሉን እያሳየው የሚገኘው በላይ አርማጭሆ ማሂን አቦ፣ ዳዚሆን፣ ገንበራ-አንገረባ፣ ሌዳሆ ማርያም፣ ኩርቢና በሌሎችም በርካታ መንደሮች የሚኖረውን በድህነት የሚማቅቀውን የገበሬ ህዝብ ነው፡፡

የህወሓት አገዛዝ የታጠቁ ኃይሎች፣ ደህንነቶችና ካድሬዎች በጉልበት አልገዛ ያላችውን የአርማጭሆ ህዝብ ‘የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮችን ትቀልባላችሁ’ እና ‘መረጃ ትሰጣላችሁ’ በማለት እየወቀሷቸውና እየከሰሷቸው ሲሆን በተጨማሪም አርበኞች ግንቦት ሰባትን በአካል የተቀላቀሉ ልጆቻቸውን ከበርሃ ካላስመለሱ በእነሱ ላይ ከመቸውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ እርምጃ እንደሚወስድባቸው የአርማጭሆን ነዋሪዎች እያስፈራሯቸው ይገኛሉ፡፡


የህወሓት አገዛዝ የታጠቁ ኃይሎች የአርማጭሆን ገበሬ የሚያረባቸውን ከብቶች፣ በጎችና ፍየሎች በጥይት እየጨፈጨፉ የበቀል እርምጃ በመውሰድ ላይ መሆናቸውም ተገልጿል፡፡


ህዝቡ ደግሞ በበኩሉ በተቃራኒው ምሬቱ አንገቱ ድረስ ደርሶ የበለጠ ዘረኛውን የህወሓት ቡድን ተፋልሞ ነፃነቱን ለመጎናፀፍ ቆርጦ መነሳቱንና እየተዘጋጀ መሆኑን የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ ዜና ምንጮች በላኩልት መረጃ አስታውቀዋል፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46524


No comments:

Post a Comment