Wednesday, September 30, 2015

አገር የምትኖረው በ3 ነገር ነው በወታደር በገበሬ እና በመምህር!!!

አገር ለማፍረስ ቆርጦ የተነሳው ወያኔ ኢትዮጵያ የምትባለው አገር እንድትኖር በመሰሪ ሃሳቡ ሌት ተቀን የማይቆፍረው ግድጓድ የለም የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም። ነገር ግን እንደ አሳቡ ሊሆንለት አልቻሉም  ዘር  ከዘር ሊያጋጭ ብዙ ጣረ አልተሳካለትም፤ ሐይማኖት ከሃይማኖት ሞከረ ይሄም አልሰራ አለው ሃሳቡ ሁሉ መና  ሲቀርበት  እራሱ ከሳሽ  እራሱ ፈራጅ  በሆነበት ፍርድ ቤት  የብዙሃን ነጽሃን  ሰው መሰቃያ  ወደ ሆነው ወህይኒ እየወረወረ ባልሰራበት ወንጀል ባላደረጉት  ድርጊት ንጽሐኑን ማሰቃየት ከጀመረ ድፍን 24 አመት አለፈ።

መምህር

አንድ አገር ከሚያስፈልጋት ዋናው መሰረታዊ ነገር መምህር ነው። መምህር ከሌለ የተማረን ህብረተሰብ ማግኝት አይቻልም።  መምህር በጠመኔው ለአገር የሚሆን ፍሬ ለህዝብ የሚጠቅም ዘር በሰው አእምሮ  ውስጥ የሚዘራ እና ብዙ ጥበቦች ባለ ብዙ እውቀት  ባለቤት አገርን በጥበብ የሚመራ ላገሩ በእውቀት የሚያገለግል ለአገር የሚጠቅመውን ካመነበት የሚሰራ ካላመነበት ደግሞ እንቢ የሚል  ማንኛውንም ነገር ሰለ ህዝብ ብሎ ስለ አገር  ብሎ ማድረግ የሚቻል ዜጋን የሚቀርጹት መምህራናን ናቸው።  ዛሬ  ወያኔ እያደረገ ያለው እኔ የምላቹሁን አድረጉ እኔ የምላቹሁን አስተምሩ እኔ የምላቹሁን  መመርያ ተቀበሉ  ብሎ አገርን የሚያጠፋ ሆኖ ሰላገኙት የወያኔ ደጋፊ ባለመሆናቸው ብቻ  አገርን የሚያቀኑን መምህራን ትውልድን የሚቀርጹ  መምህራን በካድሬ በመተካት የተማረ እንዳይበቅልባት ያወቀ  እንዳይወጣባት ትምህርት ቤቶችና ዪንቨርስቲዎች ያቃጣሪወች መናህርያ  አድርጓታል። እንግዲህ ወገኔ የመምህራን መነካት የኢትዮጵያ አንዱ መሰረቱ እየተናጋ ነውና  ልትነቃ እና  የወያኔ አገር አጥፊነቱን አውቀን በቃህ ልንለው ይገባል።

ገበሬ

አገር የምትኖረው ገበሬው አምርቶ በሚያበቅለው ምርት ነው ገበሬው ጠንክሮ በማረስ አገርን በመመገቡ ሂደት የአገርን መሰረት ነው። ዛሬ  ገበሬው ከመሬቱ በማፈናቀል ለውጪ ባለሃብት  ለኢንቬስተር በመስጠት እንዲሁም በግድ  ማደበርያ  እንዲወስድ እያደረጉት  ባለ  እዳ በማድረግ እዳውን መክፈል ሳይችል ሲቀር መሬቱን ጥሎ እንዲሄድ በማድረግ ተሳዳጅ አድርገውታል። ገበሬ የለም ማለት አገር የለችም ማለት ነው ።ገበሬው በማሰቃየት እረፍት በመንሳት  እስመርረውት ያሉት ወያኔወች ሃሳባቸውም ራያቸውም ሰለ  ኢትዮጵያ  እና ሰለ ሕዝቧ ስላልሆነ ስለሚያደርጉት ነገር  መጸጸት እንኳን አያሳዩም ስለዚህ ገበሬው ሲነካ የአገር መሰረት  መነካት ነውና ወገኔ እንግዲህ ንቃ።

ወታደር

አገር የምትጠበቀው በወታደር ነው አንድ አገር ጠንካራ የወታደር ከሌላት  ጠላት በቀላሉ ይዳፈራታል። ስለዚህ ጠንካር የወታደር ተቋም  ለአገር አጥርም መሰረት ነው። ዛሬ ግን ወያኔ እየሰራ ያለው የወታደር ተቋም  በወታደራዊ ስልጠና  እንዲሁም ትምርት በብቃት  የሚበልጣቸው እያሉ  ትግሬ በመሆኑ ብቻ  አዛዥ ቦታ ላይ እንዲቀመጥ ይደረጋል  ይሄ አካሄድ ለወያኔወች የአገር ማፍረስ አላማቸው ስለሆነ  ምንም አይሰማቸው  ለትግሬወች ግን  ጊዚያዊ ሹመት ሲሰጣቸው ሁሉንም ቦታ ያለ እውቀታቸው ቦታውን እንዲይዙት ሲደረግ ለምን ብላቹ መጠየቅ  ሲገባቹሁ የተሰጣችሁን ስልጣን ተቀብላቹ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ላይ  በደልና ጫና የምትፈጥሩ እንግዲህ እዳው በእጃቹ ነው። የወያኔ ባለስልጣን ባንተ ስም የአገርን ንብረት እየዘረፉ  እያሸሹ ይገኛሉ አንተ ግን  ከህብረተሰቡ ጋር የትም አትሄድም  ያኔ  በሰፈሩት መስፈርያ  እንዳይሆንባቹሁ የትግሬ ተወላጆች  በወታደር  ላይ የምታደርጉትን በደል ታቆሙ ዘንድ ያስፈልጋል። እንተም ከጥቂት የአገር አጥፊ እና ዘረፊ ጋር ባለመወገን አንድነታቹሁን የምታሳዩበት ጊዜ በጣም አጭር ነውና ይታሰብበት። ካለበለዚያ ግን  ወደ የኢትዮጵያ  የመከላከያ ሰራዊት ደምና ጉልበት እንዲሁም በኢትዮጵያ ሕዝብና  ሃብት እንደፈለጋቹ እየሆናቹ የምትኖሩበት ጊዜ ማብቂያው ይመጣል።

ወታደሩም እራሱንና  አገሩን ሕዝቡን የመጠበቅ ነጻ የማውጣት ሃላፊነት እንዳለበት ወያኔ የሚያውቅበት ጊዜ  ቅርብ ነው።  ወያኔወች የመከላከያ  ሰራዊት የሃገር መሰረት ስለሆነ ይህንም ለማፍረስ  እና ለመበተን ሌት ተቀን እየሰሩ ነው።  እውነት ነው መምህሩም ወደቀድሞ ቦታቸው  ተመልሰው ባላቸው እውቀት ጠመኔን ይዘው ያለምንም ተጽእኖ ዜጋን የሚያፈሩበት ጊዜ ቅርብ ነው። እውነት ነው ገበሬው ሞፈሩን አንስቶ  እርሻውን አስፍቶ  በትራክተር አርሶ  ሕዝቡን የሚመግብበት ቅርብ ነው ። እውነት ነው ወታደሩ ወያኔን የተባለ ወንበዴን አጥፍቶ ለሕዝቡና ለአገሩ ዘብ የሚቆምበት ጊዜ ቅርብ ነው ።


ሞት ለወያኔ!!!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47026

No comments:

Post a Comment