Thursday, April 3, 2014

የሕወሓቱ ልሳን ወይን ጋዜጣ አዘጋጅ ደብዛው ጠፋ


አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

የወይን ጋዜጣ አዘጋጅ በመሆን ህወሓትን ለረጅም ግዜ ሲያገለግል የነበረው ጋዜጠኛ ሐገዞም መኮነን አዲስ አበባ ከሚገኝ ቤቱ ከጠፋ ሁለት ሳምንታት አለፉ። ጋዜጠኛ ሐገዞም መኮነን ወይን ጋዜጣ ሲያዘጋጅ ቆይቶ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የህወሓት የዓፈና ተግባራትና አካሄድ በግልፅ መቃወም ከጀመረ ወራት አስቆጥሯል።

ከወይን ጋዜጣ አዘጋጅነት ለቆ የወይን ጋዜጣና የህወሓት የዓፈና ስትራተጂዎች የሚያጋልጥ መፅሓፍ ፅፎ ሊያስመርቅ በዝግጅት ላይ እያለ ያልታወቁ የፀጥታ አካላት በሌሊት ከቤቱ እንደወሰዱትና እስካሁን ያለበት እንደማይታወቅ ተገልፀዋል። ከወራት በፊት ማህተመስላሴ ገብረእግዚአብሄር የተባለ የሰሜን የፌደራል ፖሊስ የሎጂስቲክስና ፋይናንስ ሓላፊ በመቐለ ከተማ 16 ቀበሌ በፀጥታ ሃይሎች መገደሉ ይታወሳል።


በፀጥታ ሃይሎች የተፈፀመ ሙስና እንዳያጋልጥ በሚል ምክንያት ነው የተገደለው። በህወሓት አባላት ላይ ተደጋጋሚ ዓፈናና ግድያ ይፈፀማል፤ ግን አይጋለጥም። የማይጋለጥበት ምክንያት ግልፅ ነው።

https://www.zehabesha.com/amharic/archives/14098

No comments:

Post a Comment