Thursday, April 3, 2014

ሚሊዮኖች ድምጽ- በኩታበር (ደሴ አካባቢ) ሕዝቡን ፈርተው ፖሊሶች ከማሰር ተቆጠቡ

April 3rd, 2014 
በመኪና እየተዘዋወሩ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች የደሴን ሕዝብ ሲቀሰቅሱ ዉለዋል። ከደሴ 12 ኪሎሚዕት ርቃ በትምገኘዋ የኩታበር ከተማ ተመሳሳይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ ዜጎችን ፖሊሲ አስቆሞ ለማሰር ሞክሮ የነበረ ሲሆን በአካባቢው የነበረ ሕዝቡ ፖሊስን ከቦ « አታስሯቸዉም» ምንም አይነት ችግር ሳይፈጠር ፖሊሶች ገለል እንዳሉ ከደሴ የደረሰን መረጃ ይጥቁማል።

የአንድነት አመራሮች ወደ ደሴ ነገ ጠዋት ያመራሉ :: የአንድነት ከፍተኛ አመራር አባላት ነገ መጋቢት 26 በጠዋቱ ወደ ደሴ የሚያመሩ ሲሆን፣ ከሰዓት በኋላና ቅዳሜ ሙሉ ቀን በከተማ እየተዘዋወሩ ከአካባቢዉ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ጋር እንደሚቀሰቅሱም ለማወቅ ችለናል። ወደ ደሴ የሚያመሩት የአመራር አባላት ቡድን፣ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመነበሩ አቶ ተክሌ በቀለን ፣ የሥራ አስፈጻሚ አባል እና የዉጭ ጉዳይ ሃላፊው የሆኑት ኢንጂነር ዘለቀ ረዲንና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊዉ አቶ ሃብታሙ አያሌዉን ያካተተ ነው።
http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/13798

No comments:

Post a Comment