Tuesday, April 29, 2014

ፖሊስ የጣይቱ ልጆችን ለማሸማቀቅ እየጣረ ነው


April 29, 2014

ሚያዝያ 19/2006 . ለተደረገው ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያሉ ፖሊስ ‹‹የእውቅና ደብዳቤው አልደረሰኝም፣ ህገ ወጦች ናችሁ!›› ብሎ ያሰራቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት (የጣይቱ ልጆች) ላይ ፖሊስ የተለያዩ የማሸማቀቂያ ስልቶችን እየወሰደ ይገኛል፡፡ በዛሬው ቀን ፖሊስ ታሳዎቹን በተለይም ሜሮን አለማየሁና ንግስት ወንዲፍራውን ‹‹እስር ቤቱን በመረበሽ›› በሚል ሌላ ክስ ከግቢ አስወጥተው ቃል ተቀብለዋቸዋል፡፡ በወቅቱም ማስፈራራትና ዛቻ እንደደረሰባቸው ታሳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

የጣይቱ ልጆች በታላቁ ሩጫ ላይ በፖሊስ በተያዙበት ወቅት ፖሊስ የተለያዩ በደሎችን ለመፈጸም ሲጥር መብታቸውን ለማስከበር ባደረጉት ጥረት ፖሊሶች ሌሊት ከግቢ አስወጥተው የድብደባና ሌሎች ማስፈራሪዎችን እንዳደረጉባቸው ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው፣ ቤተሰብ እዳይጠይቃቸውና ሌሎችንም መብታቸውን የሚጋፉ በደሎች እየተፈጸሙባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
 
Young semayawi party female activists

http://ecadforum.com/Amharic/archives/12050/

No comments:

Post a Comment