Saturday, May 10, 2014

በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ፤ የአጋዚ ጦር አካባቢውን ወሮታል

አሁን ለዘ-ሐበሻ በደረሰ መረጃ መሠረት፦

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወምና ሰሞኑን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በአጋዚ ወታደሮች የተገደሉ ወገኖችን ለማሰብና ገዳዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ እየጠየቁ ያሉ ሰዎች አደባባይ የወጡ ሲሆን ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ባሉበት ወቅት በአጋዚ እና በፌደራል ፖሊስ መከበባቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ።

የአጋዚ ጦር በጊምቢ ወረዳ የተከሰተውን የተቃውሞ ሰልፍ ለማብረድ የኃይል እርምጃ እንደወሰደ የገለጹት የዘ-ሐበሻ ሰዎች ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ ያረጋገጥነው ነገር የለም ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን።


http://www.zehabesha.com/amharic/archives/30124

No comments:

Post a Comment