Sunday, April 5, 2015

የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት ሊያደናቅፍ የሞከረው እና በዋሽንግተን ዲሲ በሰማያዊ እና የአንድነት ድጋፍ ድርጅቶች የተጠራው የሰማያዊ ፓርቲ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ!!

የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት በሰማያዊ እና አንድነት የድጋፍ ድርጅቶች አስተባባሪነት በዋሽንግትን ዲሲ ከተማ የተጠራውን የሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባ ለማደናቀፍ የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ውጭ እንዳይወጣ አገዛዙ በማን አለብኝነት ቢከለክለውም፤ በዛሬው እለት በዋሽንግተን ዲሲ በሽራተን ሆቴል የተጠራው ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጲያውያኖች በዛሬው ዕለት በቦታው በመገኘት በአገዛዙ በኩል እየተወስደ ባለው አስከፊ የውንብድና ድርጊቶች ሠላማዊ ትግላችን ለአንድም ሰኮንድ አይቋረጥም! እንደውም የበለጠ እልህ እንድንገባና ትግላችንን እና ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥል ያደርገናል ብለዋል። በዚሁ እለትም በተደረገው ስብሰባ ላይ ከፍተኛ ለሰማያዊ ፓርቲ በተደርገው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ላይ ከፍተኛ ገንዘብ የተሰበሰበ ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ ለሰላማዊ ፓርቲ እና ደጋፊዎቹ እንዲሁም ለሌሎች የሰላማዊ ትግል ታጋዮች ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት እና አጋርነት ገልጸዋል!!
በዚሁ ስብሰባ ላይ ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በስክይፕ ከአዲስ አበባ በቀጥታ ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ወቅታዊ እንቅቃሴና የምርጫ ሁኔታ ምን ላይ እንድሚገኝ በሰፊው ለተሰብሳቢው በማስረዳት እና ከተሳታፊኢዎች ለቀርበላቸው ጥይቄዎች ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በዚሁ ስብሰባ ላይ ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማሪያም በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተው ለስብሰባው ተሳታፊዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በዚሁ ስብሰባ ላይ የተለያዩ በውጭ አገር የሚገኙ ሚዲያዎች ተጋብዘው የነበረ ሲሆን ከኢትዮቲዩብ እና ከቪኦኤ በስተቀር ኢሳትን ጨምሮ ሌሎች ሚዲያዎች በቦታው አለመገኘታቸው ታውቋል።
ይህው ስብሰባ በነገው እለት በቦስተን ከተማ የሚቀጥል ሲሆን በቀጣይም በሌሎች ከተሞች ስብሰባው በታቀደው መሰረት የሚቀጥል መሆኑን የታወቀ ሲሆን፤ በተለይ የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት በህዝቡ ላይ የሚያደርሰውን ጭቆና እና ስቆቃ፤ እንዲሁም በፓርቲዎች ላይ የሚካሂደው ወከባ እና እንግልት የበለጠ እልህ እና የትግል አጋርነታቸውን አጥናክረው እንድሚቀጥሉ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየገለጹ መሆኑ ታውቋል!!
http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/17735

No comments:

Post a Comment