Sunday, August 4, 2013

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በደባርቅ አካባቢ ጥቃት ፈጸመ

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በቅርቡ በወያኔ ላይ በከፈተው ድንገተኛ የማጥቃት እንቅስቃሴው 65 የሥርዓቱ ታማኝ ታጣቂ ሐይሎችን ከጥቅም ውጭ አደረጋቸው።
አርበኛው የጦርነት ፍልሚያውን ግብግብ ከወያኔው ታጣቂ ሃይሎች ጋር የተካፈለው በጎንደር ደባርቅ ወረዳ የሥፍራው ልዩ ስያሜ በደዊ በመባል በሚታወቀው ሥፍራ ላይ ነው።
ከአርበኛው ሐይል ጋር በዕለቱ በተጠቀሰው ሥፍራ ተገኝተው ውጊያውን የተካፈሉ የወያኔ ታጣቂ ሐይላት የፈጥኖ ደራሽ አባላት ሲሆኑ በአውደ-ውጊያው መጨረሻም 28 አባሎቻቸውን በሞት ያጡት የወያኔ ታጣቂዎች ተጨማሪ ሌሎች 37 የፈጥኖ ደራሽ አባሎቻቸውም ላይ ከፈተኛ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።

Posted By.Dawit Demelash

No comments:

Post a Comment