Sunday, November 24, 2013

በጎንደር ዩንቨርስቲ ውጥረቱ እንደቀጠለ ነው ተባለ


የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማርኬቲንግ ማኔጅመንት 3 ዓመት የዲግሪ ተማሪ የሆነው ወጣት አንተነህ አስፋው ለገሰ በፅንፈኛው ወያኔ አባላት በጩቤ ተገድሎ መገኘቱን ተከትሎ ሟች ወጣቱ ያነሳቸው የነበሩ ጥያቄወች በስፋት መነሳት ጀምረዋል ሲል አወጋን ለዘ-ሐበሽ በላከው መረጃ አስታወቀ።
ሟች አንተነህ ዘረኛው የወያኔ ወራሪ ቡድን በንፁሃን አማራ ተወላጆች ላይ የሚያደርሰውን ግፍ እና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ዉስጥ አየተፈፀመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ያለፍርሃት ይቃወም የነበረ ሲሆን ደካማው የወያኔ ቡድን የለመደውን ደም ማፍሰስ ተግባሩን ፈፅሞበታልያለው አወጋንወጣቱ የተገደለው በጩቤ ተወግቶ ሲሆን እሬሳው ከዳሽን ብራ ፋብሪካ በስተጀርባ ተጥሎ ተገኝቷልሲል ዘግቧል።
የአማራ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ እሄን አስከፊ የሆነ የጠባቦች ድርጊት አጥብቆ የሚቃወም ሲሆን ወነጀለኞችን በተገኙበት ለመቅጣት ያለ እረፍት ይሰራል ወጣቱ ከዚህ መማር ያለበት ነገር ቢኖር የወንድማቺን የአንተነህ እጣ ሳይደርሰው ወያኔን ለማስወገድ የምናደርገውን ትግል በመቀላቀል የወገኖቻችን የስቃይ አመታት እናሳጥር በማለት መልክቱን ያስተላልፋልያለው አወጋንለሟች ቤተሰቦች መጥናናቱን ይስጥሲል ሐዘኑን ገልጧል።

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አሁንም ውጥረቱ እንዳየለ ነው ቢባልም የመንግስት ሚድያዎች አንዳችም መረጃ አልሰጡን።

  Posted By.Dawit Demelash

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/9859

No comments:

Post a Comment