Wednesday, November 6, 2013

የማዕድን ሙስና በኢትዮጵያ!

  •  ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
    ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ


በዚህ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስናን አስመልክቶ ይሀ ለሰባተኛ ጊዜ ያቀረብኩት ትችት በማዕድኑ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በሙስና ላይ ያቀረብኳቸውን ሌሎችን ትችቶች “Al Mariam’s Commentaries” የሚለውን ድረ ገጽ በማየት ግንዛቤ መውሰድ ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ መዋቅራዊ ባህሪ እየያዘ በመጣው ዘርፈ ብዙ ሙስና ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ነቅቶ እንዲጠብቅ ለማስቻል በጉዳዩ ላይ አሁንም ትችቶቼን ቀጣይነት ባለው መልኩ አቀርባለሁ፡፡ ባለፉት ጥቂት ወራት ገዥው አስተዳደር የሕዝብ ትኩረትንና አድናቆትን ለማግኘት ሲል ጥቂት የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣኖችና ከዚሁ ጋር በተያያዘ ንክኪ አላቸው ባላቸው ጥቂት የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ላይ የሙስና ክስ በመመስረት የጸረ ሙስና ትግሉን በይፋ እንድታይለት ሰብስቦ በእስር ቤት አጉሮአቸዋል፡፡ እነዚህ በሙስና ተጠርጥረው በይስሙላው ፍርድ ቤት ጉዳያቸው ቀርቦ እየተሰራ ያለው ድራማ ዓለም አቀፍ አበዳሪዎችና ለጋሽ ድርጅቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት ግልጽነትና ተጣያቂነት ያለው ስርዓትን እንዲያሰፍን እያደረጉት ባለው ተጽዕኖ ምክንያት ለታይታ ያህል መንግስት የሚተገብረው የፖለቲካ ትወና ነው፡፡ ለአገር ውስጥ ህዝብ ፍጆታ ተብሎ ገዥው አስተዳደር እየተውነ ያለው ይህ የሙስና ድራማ ጥልቅና ስር ሰድዶ በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተዋናይነት ተንሰራፍቶ ያለውን ከፍተኛ የህግ ልዕልና ሂደትን የሚጠይቀውን ያገጠጠና ያፈጠጠ ሙስና አሳንሶ በማቅረብ፤ የማታለል ዘዴ በመጠቀም እርባና የለሽና የጮሌነት ጭንብል በማጥለቅ ዋነኞቹን የሙስና ተዋናዮች ለመደበቅ የተዘየደ ተውኔት ነው፡፡

  Posted By.Dawit Demelash

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/9027

No comments:

Post a Comment