Wednesday, May 6, 2015

የሰሜን ጎንደር ሕዝብ አመጽ በርትቷል * በድንበር ከተሞች አሁንም ችግሩ እየሰፋ ነው

የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እና ካድሬዎቻቸው በሕወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ተወካዮች መሪነት በባህር ዳር ስብሰባ መቀመጣቸው በታወቀበት በዚህ ሳምንት በአማራ ክልል ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ሕዝባዊ እምቢተኝነት መከሰቱን እና የፌዴራል ፖሊሶች ከሕዝቡ ጋር እየተጋጩ መሆኑ ሲጠቆም በጎጃም ገበሬው በብጡ ደጃፍ እና በቤቱ ውስጥ የእያኔን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት እንዲለጥፍ እየትገደደ እና እምቢ ያለ በመታሰር ላይ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል::

ሕወሓቶች በሚመሩት እና በባህር ዳር እየተካሄደ ያለው የብአዴን ስብሰባ ላይ ከምርጫው ጋር ተያይዞ የሚመጥውን ችግር እና ሕዝቡ ሊመርጠን ስለማይችል በድምጽ መስጫ ካርዶች ዙሪያ መወሰድ ስላለባቸው እርምጃዎች እንዲሁም ትጥቅ ያልፈቱ መሳሪያ የቀበሩ ሰዎች ካሉ አስቸኳይ ክትትል ተደርጎ እርምጃ እንዲወሰድ የሚሸፍቱ ሰዎች የሚተረጠሩ ካሉ እንዲታሰሩ የሚሉ ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከትግራይ ክልል አማራ አዋሳኝ በሆኑ ቦታዎች ያሉ የሕወሓት ሚሊሻዎች እና ካድሬዎች ወደ አማራ ክልል በማምጣት ድምጽ ሰጥተው እደ አከባቢያቸው እንዲመለሱ እንዲሁም በተለያየ ወረዳ የተለያያ የመራጭ ካርድ ዬሰዱ ሰዎች አስቸኳይ የትራንስፖርት አቅርቦት እየተደረገላቸው በየወረዳው እየሄዱ እንዲመርጡ ሲባል ከምርጫው በኋላ ሊነሱ የሚችሉ የአመጽ ስጋቶችን ለመቆጣጠር የመከላከያ ሰራዊት አባላይ የፌዴራል ፖሊስ ልብሶችን በመልበስ ተክተው እንደሚሰሩ እና ካድሬዎች እና የጸጥታ ሰራተኞች አስፈላጊዉን ትብብር በማድረግ የሚፈጠረው ችግር በቁጥጥር ስር እንዲውል እንዲያደርጉ ከሕወሓት ሹሞች መመሪያ ተሰቷቸዋል::


በሰሜን ጎንደር የላይ እና የታች አርማጮ ጨምሮ በአብድራፊ በሁመራ በመተማ በሸዲ በጭልጋ አክባቢዎች በከፍተኛ ደረጃ ሕዝቡ እና የወያኔ ፖሊሶች ውጊያ የገጠሙ ሲሆን በርካቶች ሲቆስሉ በአከባቢው የተነሳው የህዝብ እምቢተኝነት እየሰፋ መምጣቱን እና ጥያቄዎች ምላሽ አለማግኘታቸው ሲከፋ የመኖሪያ ቤታችውን በማፍረስ ሕዝቡን ለጎዳና ተዳዳሪነት መዳረጉ በመተማ እና አከባቢው የሚኖሩ ሕዝቦችን ቁጣ ቀስቅሶ እስከ ዛሬ ድረስ ሊበርድ ያልቻለ ከፍተኛ ግጭት በአከባቢው እየተደረገ እንደሆነ የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::በአጠገባችን መጥቶ የሚያግዘን ማጣታችን ነው እንጂ ወያኔን ከጎንደር ክፍለሃገር ጠራርገን እናወጣው ነበር ያሉ ወጣቶች ባለው ስርአት መማረራቸውን በቁጣ ይናገራሉ::ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎጃም ክፍለሃገር የሚኖሩ ገበሬዎች የወያኔን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት በቤታቸው እስጥ እና በቤታቸው ደጃፍ ላይ በግዳጅ እንዲለጥፉ የተደረገ ሲሆን ለመለጠፍ ፍቃደኛ ያልሆኑ ገበሬዎች በመታሰር ላይ እንደሚገኙ አንድ የደብረማርቆስ ወጣት በላከው መረጃ ገልጿል:: ሕዝቡ አስተባባሪ እና አደራጅ ነው ያጣው ቢባልም በራሱ መሪነት ብሶቱን እየገነፈለ እየወታ የሚገኘው ሕዝብ ለነጻነቱ በጋራ ሆኖ መታገሉን እንደቀጠለ ነው::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41142

No comments:

Post a Comment